• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የዶ/ር መሠረት ቸኮል አዲስ መጽሐፍ ለንባብ በቃ

June 13, 2013 08:05 am by Editor Leave a Comment

በቅርቡ ያረፉት ዶ/ር መሠረት ቸኮል ላለፉት 8 ዓመታት ሲለፉባት የነበረውና የኢትዮጵያን የ100 የፕሬስ ታሪክ የሚያሳይ መጽሐፍ ለገበያ መቅረቡን ቤተሰቦቹ ገለጹ። ጥልቀት ባላቸው ትንታኔዎቹና ቀላል አቀራረቡ የሚታቀው ጋዜጠኛና መምህር ዶ/ር መሠረት ቸኮል የጻፈው ታሪካዊው መጽሐፍ “The Quest for Press Freedom: One Hundred Years of History of the Media in Ethiopia” የሚሰኝ ሲሆን በamazon.com እንዲሁም በባርነስ ኤንድ ኖብል የመጽሐፍት መሸጫ መደብሮች እንደሚገኙ ቤተሰቦቹ ገልጸዋል።

ይህ መጽሐፍ ለማስተማሪያነት ሁሉ ታስቦ እንደተጻፈ የገለጹት የዶ/ር መሠረት ባለቤት ወ/ሮ በልዩ ወደፊት መጽሐፉን በአማርኛ ለማሳተም እንደተዘጋጁም ገልጸዋል። “ዶ/ር መሠረት ይህን መጽሐፍ በአማርኛም ጀምሮት ነበር። ሆኖም ግን በድንገት ሳጨርሰው በማረፉ ወደፊት አስተርጉመን ለማቅረብ እንሞክራለን” ያሉት ወ/ሮ በልዩ ይህን መጽሐፍ ኢትዮጵያውያን ሁሉ እንዲያነቡት ጋብዘዋል።

የዶ/ር መሠረት ቸኮልን መጽሐፍ ከኢንተርኔት ላይ ለመግዛት እዚህ ይጫኑ በመጽሐፉ ዙሪያ ተጨማሪ መረጃ ለምትፈልጉ ወ/ሮ በልዩን በስልክ ቁጥር 651-983-2052 በመደወል ማነጋገር ትችላላችሁ።

ዶ/ር መሠረት ቸኮል ማን ነበር?

ከአባቱ ከአቶ ቸኮል ረታ እና ከ እናቱ ወ/ሮ የእናት ፋንታ አስረስ በ1950 ዓ.ም በደብረ ማርቆስ ከተማ ተወለደ። በአምስተኛው ዓመቱ በፈንጣጣ በሽታ ተጠቂ በመሆኑ በተደረገለት ህክምና ሕይወቱን ለማትረፍ ቢቻልም የዓይን ብርሃኑን የማጣት አደጋ በስምንት ዓመት ዕድሜው ደረሰበት። በሰበታ የዓይነ ስውራን ትምህርት ቤት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ተከታትሏል። በተማሪነት ዘመኑ ለመዝሙርና ለሙዚቃ እንዲሁም ለመጽሐፍ የነበረው ፍቅር ከፍተኛ ነበር። በዕድገት በህብረት ዘመቻ በባህር ዳር ከተማ በመምህርነት ተመድቦ ግዴታውን ለመውጣት ችሏል። በ1971 በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቋንቋዎች ጥናት ኢንስቲቱት በ እንግሊሽ ዲፓርትመንት ገብቶ በ1974 ዓ.ም ከጠቅላላው ተማሪ በላቀ ውጤት የዓመቱ ኮከብ ተማሪ ሆኖ ከወቅቱ የሃገሪቱ ፕሬዚዳንት እጅ የወርቅ ተሸላሚ በሆን የመጀመሪያውን ዲግሪ አገኘ።

ከዚያም Ethiopian External Service ተብሎ በሚታወቀው መስሪያ ቤት በጋዜጠኝነት ተቀጥሮ በሪድዮ ጣቢያው በየሳምንቱ የሚደረገውን የባህልና የሙዚቃ እንዲሁም ታዋቂ ግለሰቦች የሚጋበዙበት የውይይት ፕሮግራም አዘጋጅና አቅራቢ በመሆን ያገለገለ ሲሆን ማዘር ትሬዛን በፕሮግራሙ ላይ ለማቅረብ የቻለ፤ በአነባበቡ፣ በፕሮግራሙ ጥልቀት፣ ታማናዊ በሆነ አቀራቡ የብዙ አድማጮችን ቀልብ የሳበ ነበር። በተለያዩ ሃጉሮች የተለያዩ ስልጠናዎችን ያገኘ ሲሆን ከቀይ ጨረቃ አፍሪካ አቀፍ የሬድዮ ፕሮግራም አምስት ጊዜ እውቅና አግኝቷል።

በ1982 ዓ.ም ከባለቤቱ ወ/ሮ በልዩ በላይ ጋር ህጋዊ ጋብቻ በመፈጸም በ1983 ዓ.ም የትምህርት ዕድል በማግኘቱ ወደ ሜኔሶታ በማቅናት የማስትሬት ዲግሪውን ጀምሮ በ1986ና በ1989 ዓ.ም የኮምዩኒከሽንና በፖለቲካል ሳይንስ የማስተርስ ዲግሪውን፣ በ1991 እንዲሁም የዶክትሬት ዲግሪውን (PHD) በመገናኛ ብዙሃን ትምህርት ከዩኒቨሪሲቲ ሚኒሶታ አግኝቷል።

ትምህርቱን ከጨረሰ በኋላ በከፍተኛ ተምህርት ተቋሞች በማስተማር ሥራ ተሰማርቶ በዩኒቨርሲቲ ሚኒሶታ፣ በዊስካንሰን ሪቨል ፎል ዩኒቨርሲቲ፣ በኦሃዮ በሚገኘው አሽላንድ ዩኒቨርስቲቲ፣ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ሚቺጋን ከመምህርነት እስከ ተባባሪ ፕሮፌሰርነት አገልግሏል።

ከማስተማሩና ከምርምሩ ተጨማሪ የተለያየ ኮሚቴዎች አባልና ስብሳቢ በመሆን ሙያዊ ግልጋሎት ሰጥቷል። በተጨማሪም በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ ጥናታዊ ጽሁፊችን በተለያዩ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች አቅርቧል። እንዲሁም ከአካዳሚ ጋር ያልተያያዙ ሁለት መፅፎችን ለአንባብያን አበርክቷል።

The quest for press freedom በኢትዮጵያ የ100 ዓመታት ሜዲያ ታሪክ ላይ ያተኮረ መጽሐፍ አዘጋጅቶ ሰጥቷል። ይህ መጽሐፉ በቅርብ ጊዜ በገበያ ላይ እንደሚውል ሕይወቱ ከማለፉ በፉት ለጓደኞቹና ለዘመድ አዝማድ አብስሯል። እንዲሁም ሁለት ለመጨረስ ያልታደላቸው ያሬድ ገብረሚካኤልና የዛሪኤይቱ ኢትዮጵያ ጽሁፎችን ለ Encyclopedia Aethiopica Vol.5 አዘጋጅቶ እንደነበር ይታወቃል።

ዶክተር መሠረት ከመምህርነትና ከምርምር ሥራዎቹ ባልተናነሰ መልኩ የሚታወቀው በሰባዊ መብት ተሟጋችነቱ፤ ለሃገሩ ባለው ቅናቂ አስተሳሰብና በተለይም ወቅታዊ ሁኔታዎች ላይ በሚሰጠው ትንታኔ ነበር። በዚህ በሚኒሶታ የሚገኘው የኢትዮጵያ ድምጽ ሬድዮ የ እንግሊዘኛ ዜና በማዘጋጀት፤ በአሜሪካ ሬድዮ ጣቢአ የዘወትር ተባባሪ በመሆን፤ በ1995 ምርጫ ዘመን ድምጽ ላጡ ድምጽ በመሆን ጊዜውን፣ ገንዘቡን፣ ዕውቀቱን በመለገስ፣በተለይዩ ከተሞች በተናጋሪነት በመጋበዝ አስተዋጽሆ አድርጓል።
በ2007 በሜሪላንድ ተቀማጭ የሆነ የታዋቂ ግልሰቦችን ታሪክ የሚያጠናቅር ድርጅት በማቁቋምና የድርጅቱም ሊቀመንበር በመሆን አገልግሏል። በሕይወት ዘመኑ ብዙ ልጆችን የትምህርት ዕድል እንዲያገኙ አድርጓል።

መሠረት በሥራው ላይ የማይኩራራ፣ ይህን አደረኩ ብሎ የማይናገር፣ እራሱን ዝቅ አድርጎ ከማንኛውም ሰው ጋር ተግባብቶ የሚኖር፣ ለ እውነት ራሱን አሳልፎ የሚሰጥ እንደነበር በቅርብ የሚያውቁት ጓደኞቹ ይናገራሉ።

ባለፉት ሁለት ወራት የጉበት ካንሰር በሽተኛ መሆኑን ካወቀ በኋላ ከእራሱ ይቅል ለወገኖቹ በማሰብ ሌሎች ተገቢውን ምርመራ እንዲያከናውኑ ያሳስብ ነበር። ዶ/ር መሠረት ቸኮል በተወለደ 55 ዓመቱ ቅዳሜ ሕዳር ስምንት ቀን 2005 ከጠዋቱ 5am ላይ ህክምና ሲደረግለት በነበረው በፓርክ ኒክለት ሜተዲስት ሆስፒታል ባለቤቱን ወ/ሮ በልዩ በላይን፣ ልጁን ኤደን መሠረትን፣ ቤተሰቡን እና ጓደኞቹን በመለየት ከዚህ ዓለም አልፏል። (ፎቶ: በአሁኑ ወቅት የጋዜጠኝነት ትምህርቷን እየተከታተለች የምትገኘው የዶ/ር መሠረት ቸኮል ልጅ ኤዶን የአባቷን መጽሐፍ ይዛ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule