
የቀድሞውን ጠ/ሚኒስትር የአቶ መለስን ሞት አስመልክቶ ሕዝባዊ ግንባር ሓርነት ኤርትራም (ሻዕቢያ) ሆነ መሪው አቶ ኢሳይያስ የሚያስተዳድሩዋቸው መገናኛዎች ዝምታን መምረጣቸው እያነጋገረ መሆኑ ተገለጸ። በአገር ውስጥና በውጪ ለሚኖሩ የተለያዩ ኅብረተሰብ ክፍሎች መጠይቅ በመበተን ባሰባሰብነው መረጃ የኤርትራ ዝምታ የአቶ መለሰንና የኤርትራን ቁርኝት አደባባይ ያወጣ እንደሆነ የሚስማሙት ቁጥር አብላጫ ነው።
“አቶ መለስ ቀድሞውንም ለኤርትራና ለኤርትራ ተወላጆች ሽንጣቸውን ገትረው ሲከራከሩ የነበሩ መሪ መሆናቸውን ለምንረዳ የሻእቢያ ዝምታ አያስገርምም” የሚሉት አስተያየት ሰጪ “አቶ መለስ ለኤርትራ ያሳዩትን ከልብ የመነጨ ፍቅርና የተቆርቋሪነት ስሜት ለሚመሩት ህዝብና አገር አሳይተው አያውቁም። የኤርትራ ተወላጆችም ሆኑ ፕሬዚዳንት ኢሳይያስ አፈወርቂ ሃዘን ቢቀመጡ ከኢትዮጵያዊያን በላይ አግባብነት አላቸው” ብለዋል።
አቶ አዲሱ ለገሰ በአስከሬን ስንብት ስነ ስርዓት ላይ ስለ አቶ መለስ ባነበቡት ሰፊ ጽሁፍ የኤርትራን ጉዳይ አንስተው መለስን አወድሰው ነበር። “መለስ የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት መካሄድ የለበትም” የሚል የጸና እምነት እንደነበራቸው ከገለጹ በኋላ “በድምጽ ብልጫ ተሸንፎ የገባበትን ጦርነት በብቃት መርቷል” በማለት የኤርትራና የመለስን ወዳጅነት ስንብቱ ላይም ህዝብ ልብ እንዲል አሳስበዋል።
ከበረሃ ጀምሮ ችግር ያልተለየው የወያኔና የሻዕቢያ ወዳጅነት ተበጠሰ ሲባል እየተቀጠለ እዚህ የደረሰው በአቶ መለስ ወገንተኛነት እንደሆነ የሚጠቁሙ የቀድሞ የህወሓት አባል የኤርትራን ዝምታ ከዚሁ ከቆየው የመለስ ውለታ አንፃር እንደሆነ አመልክተው የአቶ ኢሳይያስ አገዛዝ ፍርሃት ውስጥ እንዳለ ይጠቁማሉ። በአቶ መለስ ትዕዛዝ በቅርቡ ሁለት ከፍተኛ የተባለ ጥቃት ሲሰነዘረበት እጁን አጣጥፎ የተቀመጠው ሻዕቢያ ኢትዮጵያ ላይ የሚከተለው አቋሙ ዝምታ እንዲመርጥ እንደሚያስገድደው የቀድሞ የህወሃት ሰው ያስረዳሉ።
በበረሃው ትግል ወቅት “ሻዕቢያ ከደርግ በላይ ቀንደኛና ቁልፍ ጠላታችን ነው፤ ከሻዕቢያ ጋር ያለን ግንኙነት ሊበጠስ ይገባል” በሚል የከረረ አለመግባባት ተፈጥሮ ሶስት ወራት የፈጀ ስብሰባ መደረጉን ያወሱት እኚሁ የቀድሞ የህወሃት ሰው “አሁን የቀረው የህወሃት አመራር የሻዕቢያን ጉዳይ በጥብቅ ስለሚመለከተውና በመካከላቸው የሃሳብ ልዩነት ስለሌለ ሻዕቢያን የሚያስታምመው የለም፤ በዚህም ድንጋጤ ውስጥ ነው” ብለዋል።
በዓለምአቀፍ ጫና ሰበብ በ1991 ያከተመለትን የአቶ ኢሳይያስ አገዛዝ እንዲያንሰራራ ያደረጉት አቶ መለስ በባድመ ጦርነት ያለ ምንም ፋይዳ ለሞቱት የኢትዮጵያ ልጆች ደም ተጠያቂ ሊሆኑ እንደሚገባ እግረ መንገዳቸውን የጠቆሙት ሌላ አስተያየት ሰጪ አቶ መለስ በኤርትራ ላይ ይከተሉት የነበረው የተንሸዋረረ ፖሊሲ ኢትዮጵያዊያንን እጅግ ከፍተኛ የሞራልና የቁስ ዋጋ አስከፍሏቸዋል። የዚያኑ ያህል ሻዕቢያ በአገራችንና በኢኮኖሚው ላይ እንዲፈነጭና ልዩ ተጠቃሚ እንዲሆን አድርጎታል። ሃዘኔታው የሚመነጨው በበርካታ ምክንያቶች ነው።
ፕሬዚዳንት ኢሳይያስን “አጉራ ዘለል፣ ያበደ ውሻ፣ ጋጠወጥ፣ ዱርዬ…” በማለት እሳቸው በፈጠሩት ፓርላማ፣ በአፍሪካና በተለያዩ የዓለም ክፍሎች መሳቂያና መሳለቂያ አደርገው ከዓለም የዲፕሎማሲ መድረክ ያሽቀነጠሩዋቸው መለስ ሲሞቱ ኤርትራ በአገር ደረጃ ዲፕሎማት በመላክ ለቅሶ መድረሷ እንዳስገረማቸው አብዛኞች ተናግረዋል።
መለስ የኤርትራን ተቃዋሚዎች በማደራጀት ኢሳያስን ጥለው የሚፈልጉትን መንግስት ለማቋቋም በግልፅ እንደሚሰሩ ሻዕቢያ ጠንቅቆ ያውቃል፣ ኢሳያስ ሞቱ በተባለበት ወቅት ስልጣን ለመረከብ ኢትዮጵያ ውስጥ የተቋቋመውና በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የቅስቀሳ ሰዓት ተፈቅዶለት ኢሳያስን እያወገዘ ያለው የተቃዋሚዎች ህብረት የመለስን ይሁንታ አግኝቶ መሆኑ ሚስጥር አይደለም። ኢሳያስ የተደገሰላቸውን ድግስ ቢያውቁም በመለስ ህልፈት የተፈጠረውን ቀዳዳ ለመጠቀም አለመሞከራቸው ለኢትዮጵያዊን ተቃዋሚዎች የማንቂያ ደወል ስለሆነ አጋጣሚው ጥንቃቄ እንዲያደርጉ የሚጋብዝ ነው። በጽሁፍ ከአውስትራሊያ መልዕክታቸውን ያደረሱን አስተያየት ሰጪ በጥቅሉ ኤርትራ የመሸጉ ተቃዋሚዎችን ከማሳሰብ በስተቀር በስም አልጠሯቸውም።
በአደራዳሪነት ሽምግልና ሰበብ የኦነግን ሰራዊት በሰላም ስምምነት አግባብቶ የተለያዩ የማሰልጠኛ ካምፖች በመክተት በወያኔ ሰራዊት እንዲከበቡና ትጥቃቸውን እንዲፈቱ ያደረገው ሻዕቢያ መሆኑን ያመለከቱት አስተያየት ሰጪ፣ በተመሳሳይ መሰረታቸውን ኤርትራ አድርገው ለዓመታት የሚንቀሳቀሱ ወገኖች ሂደቱን ሊመረመሩት እንደሚገባ ጠቁመዋል። ሻዕቢያ የተረጋጋችና አንድነቷን የጠበቀች ኢትዮጵያ እንድትኖር ከእውነተኛ ኢትዮጵያኖች ጋር ሊሰራ ይችላል? የሚለውን መሰረታዊ ጉዳይ እነዚሁ ክፍሎች በጥንቃቄ በማገናዘብ እንዲገመግሙ መክረዋል። ኤርትራን ማመን ከቶውን እንደማይቻል አሳስበዋል። ከኤርትራ መውጣት የተከለከሉ የነጻነት ታጋዮች መኖራቸውንም አመልክተዋል።በአደራዳሪነት ሽምግልና ሰበብ የኦነግን ሰራዊት በሰላም ስምምነት አግባብቶ የተለያዩ የማሰልጠኛ ካምፖች በመክተት በወያኔ ሰራዊት እንዲከበቡና ትጥቃቸውን እንዲፈቱ ያደረገው ሻዕቢያ መሆኑን ያመለከቱት አስተያየት ሰጪ፣ በተመሳሳይ መሰረታቸውን ኤርትራ አድርገው ለዓመታት የሚንቀሳቀሱ ወገኖች ሂደቱን ሊመረመሩት እንደሚገባ ጠቁመዋል። ሻዕቢያ የተረጋጋችና አንድነቷን የጠበቀች ኢትዮጵያ እንድትኖር ከእውነተኛ ኢትዮጵያኖች ጋር ሊሰራ ይችላል? የሚለውን መሰረታዊ ጉዳይ እነዚሁ ክፍሎች በጥንቃቄ በማገናዘብ እንዲገመግሙ መክረዋል። ኤርትራን ማመን ከቶውን እንደማይቻል አሳስበዋል። ከኤርትራ መውጣት የተከለከሉ የነጻነት ታጋዮች መኖራቸውንም አመልክተዋል።
በሌላ ተመሳሳይ ዜና የኢትዮጵያ ወቅታዊ ገዳዮች መወያያ መድረክ ድረገጽ ላይ “አስገራሚው መግለጫ እንደሚከተለው ተተርጉሟል” በሚል በህይወት የሌሉት የአቶ መለስ ወላጅ እናት ወ/ሮ አለማሽ ገብረልዑል የስጋ ዘመዶች ከኤርትራ በአይጋ ፎረም አማካይነት የላኩትን የሃዘን መግለጫ አስነብቧል። ትርጉሙን ያቀናበሩት ኢየሩሳሌም አርአያ መሆናቸውን አስታውቋል። “የሃዘን ማፅናኛ መግለጫ” ደብዳቤው እንደሚከተለው ይነበባል።
“በኤርትራ ምድር እና በመላው አለም የምንገኝ የደጃዝማች ገብረልኡል ተስፋማርያም እና የአቶ ካህሱ መላ ቤተሰቦች የሆንን፤ በሞት በተለየን በምናፈቅረው፣ ልጃችን እና ወንድማችን፣ የኢ.ፌ.ድ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ሞት የተሰማን መሪር ሃዘን እየገለጽን፤ ለዘመዶቹ ለቤተሰቡ እንዲሁም ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ጽናቱን ይስጠን እንላለን። አቶ መለስ ዜናዊ በኢትዮጵያ እና አፍሪካ ታሪክ ረሃብን ከሰፊው ህዝብ ለመንቀል፣ የታመመው እንዲፈወስ፣ መሃይሙ እንዲማር፣ መብቱ የተገሰሰው ፍትህ እና ነጻነት እንዲከበርለት እና እንዲረጋገጥለት፣ ለአንድ ቀን እና ሰአት ሳያርፍ እና እፎይ ሳይል፣ ተወዳዳሪ የሌለው ዘላለማዊ የታሪክ ሃውልት ማኖሩ፣ ለህዝቡ እና ለቤተሰቡ የማይረሳ የድል ችቦ፣ የማይናድ ቅርስ፣ የማይጠፋ መብራት፣ ተጠብቆ የሚኖር ዘላለማዊ ክብር፣ … ትቶ በማለፉ፣ የተሰማንን ትልቅ ኩራት እየገለጽን፤ በተለይ ለኢትዮጵያ እና ኤርትራ ህዝብ በተለይም ደግሞ ለመላው ቤተሰቡ የጀመረውን ስራ ሳይጨርስ፣ ገና በ57 አመት እድሜው ማለፉ ሃዘናችንን ጥልቅ መሪር እና በጣም ከባድ ሸክም አድርጎታል። አቶ መለስ ዜናዊ እድሜውን ሙሉ ሲያከናውነው የቆየው ፣መልካም እና የተቀደሰ ተግባራት ባይኖር ያለምንም ማጋነን እና አድሎ የኢትዮጵያ ህዝብ እና መንግስት አሁን ላለበት ደረጃ ሊበቃ እንደማይችል በማመን፣ እርሱ የጀመረው ወደር የሌለው የአገር እና ህዝብ ግንባታ አጠናክረው እንደሚገፉበት እና እንደሚያጎለብቱት ያለንን እምነት እና ተስፋ በዚህ አጋጣሚ እንገልጻለን። ለአቶ መለስ ደግሞ ያንን ሁሉ የህዝብ እና ቤተሰቡ ጸሎት እና መሪር ሃዘን ፈጣሪ አምላክ ሰምቶለት በመንግስተ ሰማያት ያኑረው ።”
በሌላም በኩል ነሐሴ 20/2004 የታተመው ሪፖርተር ጋዜጣ በፖለቲካ አምዱ “ሳያርፍ ያረፈ መሪ በሚል ርዕስ” “ በአቶ መለስ ሞት የፈነጠዙ ኢትዮጵያዊያን ብቻም አይደሉም፡፡ በርካታ ኢትዮጵያዊያን በኤርትራ ውስጥ ሲሰቃዩ፣ ኤርትራውያን በኢትዮጵያ የተለየ መብት በመስጠት፣ ኤርትራን በማስገንጠልና ኢትዮጵያን ወደብን በማሳጣት የሚተቹት አቶ መለስ መሞታቸውን ተከትሎ፣ በውጭ እየጨፈሩና መንግሥት ለመመሥረት እየተሯሯጡ ካሉት ጋር ኤርትራዊያን እንዳሉበት መስማቱ የበለጠ አሳዛኝ አድርጎታል፡፡ ምንጮች እንደሚጠቁሙት፣ በኢትዮጵያ መንግሥት አማካይነት ወደ ውጭ አገሮች የወጡ ኤርትራዊያን ወጣቶች የዚሁ እንቅስቃሴ አካል መሆናቸው እየተሰማ ነው፡፡ ብስራት የተባለ የአዲስ አበባ ነዋሪ ወጣት፣ መንግሥት አሁንም በኤርትራና በኤርትራዊያን ላይ የሚከተለውን ፖሊሲ እንደገና እንዲገመግም የሚጠይቀው ይህንን ከሰማ ወዲህ ነው” ሲል አስነብቧል። ከሪፖርተር ወገናዊነት አንጻር በመለስ ሞት ማግስት ይህ መጻፉ መለስ ሲጫኑት የኖረው ህወሃት/ኢህአዴግ ኤርትራ ላይ የሚከተለውን ፖሊሲ ይቀይራል የሚሉትን ክፍሎች ሃሳብ ያጠናክራል። በዚሁ መሰረት የኤርትራ ዝምታ ይህንኑ የፖሊሲ ለውጥ ፍርሃቻ ሳይሆን እንደማይቀር ግምታቸውን ሪፖርቱ አስፍቶታል። ይህ ዜና አስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ በአቶ መለስ ህልፈት ዙሪያ ኤርትራ በገሃድ የተነፈሰችው ባሉታዊ መልኩ የሚጠቀስ ዜና የለም።
ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ ለሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡
It is true that Eritrea lost a dedicated son who has been leading Ethiopia for over two decades doing ground work for the break up of Ethiopia into several small ethnic states so no powerful entity remains that can reclaim Assab, etc and challenge Eritrea for ever. No wonder Eritreans and their govt are in secret mourning while we Ethiopians are relieved of bottomless hopelessness and insecurity as a state. But God came to the rescue of Ethiopia even though its people are still in deep sleep. However, there are still a bunch of Eritreans (who pose as Tigray) still left in EPRDF govt. We still have long long way to go.
Wake up people. Wake up the people of Tigray from deep sleep. Wake up the people of Ethiopia from half death. Wake up oppositions working with Eritrean govt from excessive naivety and madness.
Thanks
Congratulations!
What a great news! Welcome to the world of media!
I also like to say “የሚወጣ እንጀራ ከምጣዱ ያስታውቃል” b/s I at least scanned the articles and it is a very professional start! Specially I have read this one and is very balanced with a lots of truth in it.
Very well said. Eritreans have so many reasons to mourn for the death of PM Melles. My mother used to say ” until you go blind you don’t realize how your eyes are important ”. This is to say that I don’t know if Eritreans knew the late PM was concerned for Eritrea and Eritreans as much as he concerned for Ethiopia if not more, but I’m sure that today Isayas and his people are worried to their death, and they now know how important the PM was for Eritrea. They know after Melles there’s no one in Ethiopia who holds umbrella over Eritrea like Melles did.