
…. ከለለ ማለት፦ ቆረጠ፡ ጋረደ፡ አጠረ፡ ለየ፡ ከፈለ ማለት ነው። (በባህርዩ ምድራዊ ቆሳቁስ የማይካፈለውን አምላክ ከፍጡራን ለመለየት ብቻ ለመግለጽ ክልል የምትለውን እንጠቀማለን) ለኢትዮጵያ ዘበኛና ቤዛ የነበረው አርበኝነት የሚመነጭበትን አብራክ ለማድረቅ፤ የሚጸነሰበትን ማህጸን ለማምከን በምዕራቡ ትምህርት የተመለመሉ ወገኖች ህዝቡን አካለሉት፡ አቆራረጡት፡ ጋረዱት፡ አጠሩት፡ ለዩት፡ ከፈሉት። ከላይ የተዘረዘሩት እሴቶች የትግራይ ነጻ አውጭ ቡድን ትርጉማቸውን ገልብጦ በወጣቱ ትውልድ እስከደፋው ድረስ፤ በሥጋና በደም ላልተቀላቀሉባቸው፤ በእለታዊ፤ ሳምንታዊና አመታውያን በዓላት የማይገናኙባቸው፤ ፤ ከነሱም ያልተረከብናቸው፤ እንደ ኬንያውያን ሱዳናውያን የመሳሰሉት ጎረቤት በመባል የሚታወቁ ዜጎች የሚኖሩባቸው አርበኞች አባቶቻችን ያልተዋጉላቸው አገሮች ብቻ ነበሩ። በተዘረዘሩት እሴቶች ከተቆላለፈው ህብረተ ሰብ አብራክና ማህጸን የፈለቀውን አርበኝነትንና በአርበኝነት ውስጥ የጠናቀሩትን እሴቶች ከዚህ በታች ለማሳየት እሞክራለሁ።
(ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)
“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።
Leave a Reply