• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን

December 25, 2013 10:18 am by Editor Leave a Comment

ለርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አባላትና ወዳጆች፤ እንዲሁም በመላው UKየምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ሁሉ።

በስደት ላይ በሚገኘው ኢትዮጵያዊ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታይ ጥረት፤ ድካምና ተጋድሎ አማካኝነት ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በዘረጋው የጎሳ ፖለቲካ ተጽዕኖ ሥር ሳትወድቅ በአስተዳደር ራሷን ችላ በመመራት ለከፍተኛ የዕድገት ደረጃ የበቃችው አንጋፋዋ የለንደን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በአሁኑ ወቅት ለወያኔ ባደሩ ጥቂት ባንዳ ካህናትና ተከታዮቻቸው አማካኝነት ገንዘብና ጉልበታቸውን አስተባብረው፤ ጥረውና ግረው የሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ባለቤት ካደረጓት አባላቷ ተነጥቃ የወያኔ አገዛዝ ሹመኞችና ደጋፊዎች ንብረት እንድትሆን የሚካሄደው ጥረት ቀጥሎ ይገኛል።

london 1ቀደም ሲል እነዚሁ ከሃዲ ካህናትና ተከታዮቻቸው ወያኔ ከጎሳው መርጦ ከሾማቸው ከአቡነ እንጦስና ከነ መጋቢ ተወልደ ጋር ግንባር በመፍጠር በ12 October 2013 ሁለት ጳጳሳትን ከኢትዮጵያ በማስመጣት ቤተ ክርስቲያኗን በወያኔ አገዛዝ ሹመኞችና ደጋፊዎች ቁጥጥር ሥር ለማዋል ሙከራ ያደረጉ ሲሆን ይህ ሙከራቸው ግን ስደተኛው ኢትዮጵያዊ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ኢትዮጵያ ውስጥ በሕዝቤ ላይ የምትፈጽሙት ግፍ፤ በደልና ፍትሕ አልባነት አልበቃ ብሏችሁ በዚህ ነጻነትና ፍትሕ በሰፈነበት ሃገር ደግሞ ተመሳሳይ ድርጊት እፈጽማለሁ ብላችሁ አታስቡ በማለት ሰላማዊና ሕጋዊ ተቃውሞ በማድረግ ሙከራቸውን ሊያከሽፈው ችሏል።

ከዛም በመቀጠል የከሃዲዎቹ መሪ የሆኑት አባ ግርማ ከበደ አዲስ አበባ ድረስ በመሔድ ከወያኔ አገዛዝ ባለሥልጣኖችና የደህንነት ሰዎች ጋር በመምከር ለንደን በሚገኘው የወያኔ ኤምባሲና ሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ሕ.ወ.ሃ.ት) ጽሕፈት ቤት እየተረዱ የጀመሩትን ተግባር እንዲያጠናቀቁ መመሪያ ተቀብለው ተመለሱ።

አባ ግርማ ከበደም ለወያኔ አገዛዝ ያላቸውን ታማኝነት ለማረጋገጥ ሲሉ ዜና ቤተ ክርስቲያን ለተሰኘው መጽሄት ለንደን ላይ የሚያስቸግሩኝ ግንቦት ሰባትና ቅንጅት ናቸው የሚል ክስ በማቅረብ ከነዚህ ሁለት ድርጅቶች ጋር ለሚያደርጉት ትግል ወያኔ ከጎናቸው እንዲቆምላቸው መጠየቃቸውን መጽሄቱ በእትሙ ላይ ካሰፈረው ለመረዳት ተችሏል።

በዚህ ድጋፍና መበረታታት በመታገዝ በአሁኑ ወቅት ደግሞ እነዚህ ባንዳ ካህናትና ተከታዮቻቸው የሃገሪቱን ሕግም ሆነ የቻሪቲን ሕግና መመሪያ አንቀበልም በማለት በኤምባሲ ተወካዮችና ለንደን ከደረሱ ካለፈው 7 ጀምሮ ማርያም ቤተ ክርስቲያንን ደጃፏን ረግጠው በማያውቁት አቡነ እንጦስ አማካኝነት በ29/12/2013 ቤተ ክርስቲያኗን ከፍተው ለማስረከብ መዘጋጀታቸውን ይፋ ማስታወቂያ በማሰራጨት ላይ ይገኛሉ።london 2

ከዚሁ ጋርም በኤምባሲና በወያኔ ጽ/ቤት አስተባባሪነት በለንደን ያሉና ከለንደን ውጪ ያሉ የሌላ ቤተ ክርስቲያን አባላት ተጓጉዘው መጥተው ማርያም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በብዛት በመገኘት ቤተ ክርስቲያኗን በወያኔ አገዛዝ ሹመኞችና በኤምባሲ ተወካዮች ቁጥጥር ሥር ለማዋል ኃይልና ጉልበት እንዲሆኗቸው ለማድረግ እየሰሩ መሆኑን አቡነ እንጦስ በሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለጸሎት ለተሰበሰበው ሕዝብ ይፋ ቅስቀሳ አድርገዋል።

ይህንን በሚያደርጉበት ጊዜ ግን ለአካባቢው ፖሊስ የተሰጠው ምክንያት የጸሎትና የአምልኮት መብታችንን ይከበርልን ዘንድ ቤተ ክርስቲያኑን ስንከፍት አስፈላጊው ትብብር ይደረግልን የሚል በመሆኑ ፖሊስ ያሉትን አምኖ ተቀብሎ ትብብር ሊያደርግላቸው እንደሚችል ይገመታል።

በለንደንና በመላው UK የምትገኙ ውድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታዮችና የማርያም ወዳጆች ሁሉ፡

መብትና ነጻነት ያለትግል፤ ድካምና መስዋዕትነት አይገኝምና ዛሬ የእምነትና የነጻነት ምልክታችን የሆነችውን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስደተኛው ኢትዮጵያዊ ሃብትና ጉልበቱን አስተባብሮ የንብረት ባለቤት ባደረጋት ማግስት የወያኔ ሹመኞች የውስጥ ባንዳዎችን በመሣሪያነት ተጠቅመው የሃይማኖቱን ማዕከል፤ ሃብትና ንብረቱን ነጠቁት ማለት ነገ በስደቱ ዓለም ነጻ የኮሚኒቲ ማዕከል፤ የፖለቲካ ተቋም፤ መኖር ቀርቶ በቤተሰብ ደረጃም ሆነ በግል ሰብ ሳይቀር በነጻነት ሃገር መብትና ነጻነትን አሳልፎ ለመስጠት ትለቁ በር ከፋች ስለሆነ ሁሉም የማርያም ወዳጅና ነጻነት ወዳድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ በ29/12/2013 ከ0800 ሰዓት ጀምሮ በርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ በመገኘት ቤተ ክርስቲያኑን እንዲከላከልና በስደት ሃገር የተጎናጸፈውን መብትና ነጻነቱን እንዲያስከብር በእመቤታችን በቅድስት ማርያም ስም ጥሪአችንን እናቀርባለን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!

በ http://londondebretsion.org/ ተከታተሉን

በ ourchurchdebretsion@gmail.com ኢ-ሚየል መረጃ ማግኘት ይችላሉ።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule