• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን

December 25, 2013 10:18 am by Editor Leave a Comment

ለርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አባላትና ወዳጆች፤ እንዲሁም በመላው UKየምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ሁሉ።

በስደት ላይ በሚገኘው ኢትዮጵያዊ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታይ ጥረት፤ ድካምና ተጋድሎ አማካኝነት ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በዘረጋው የጎሳ ፖለቲካ ተጽዕኖ ሥር ሳትወድቅ በአስተዳደር ራሷን ችላ በመመራት ለከፍተኛ የዕድገት ደረጃ የበቃችው አንጋፋዋ የለንደን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በአሁኑ ወቅት ለወያኔ ባደሩ ጥቂት ባንዳ ካህናትና ተከታዮቻቸው አማካኝነት ገንዘብና ጉልበታቸውን አስተባብረው፤ ጥረውና ግረው የሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ባለቤት ካደረጓት አባላቷ ተነጥቃ የወያኔ አገዛዝ ሹመኞችና ደጋፊዎች ንብረት እንድትሆን የሚካሄደው ጥረት ቀጥሎ ይገኛል።

london 1ቀደም ሲል እነዚሁ ከሃዲ ካህናትና ተከታዮቻቸው ወያኔ ከጎሳው መርጦ ከሾማቸው ከአቡነ እንጦስና ከነ መጋቢ ተወልደ ጋር ግንባር በመፍጠር በ12 October 2013 ሁለት ጳጳሳትን ከኢትዮጵያ በማስመጣት ቤተ ክርስቲያኗን በወያኔ አገዛዝ ሹመኞችና ደጋፊዎች ቁጥጥር ሥር ለማዋል ሙከራ ያደረጉ ሲሆን ይህ ሙከራቸው ግን ስደተኛው ኢትዮጵያዊ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ኢትዮጵያ ውስጥ በሕዝቤ ላይ የምትፈጽሙት ግፍ፤ በደልና ፍትሕ አልባነት አልበቃ ብሏችሁ በዚህ ነጻነትና ፍትሕ በሰፈነበት ሃገር ደግሞ ተመሳሳይ ድርጊት እፈጽማለሁ ብላችሁ አታስቡ በማለት ሰላማዊና ሕጋዊ ተቃውሞ በማድረግ ሙከራቸውን ሊያከሽፈው ችሏል።

ከዛም በመቀጠል የከሃዲዎቹ መሪ የሆኑት አባ ግርማ ከበደ አዲስ አበባ ድረስ በመሔድ ከወያኔ አገዛዝ ባለሥልጣኖችና የደህንነት ሰዎች ጋር በመምከር ለንደን በሚገኘው የወያኔ ኤምባሲና ሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ሕ.ወ.ሃ.ት) ጽሕፈት ቤት እየተረዱ የጀመሩትን ተግባር እንዲያጠናቀቁ መመሪያ ተቀብለው ተመለሱ።

አባ ግርማ ከበደም ለወያኔ አገዛዝ ያላቸውን ታማኝነት ለማረጋገጥ ሲሉ ዜና ቤተ ክርስቲያን ለተሰኘው መጽሄት ለንደን ላይ የሚያስቸግሩኝ ግንቦት ሰባትና ቅንጅት ናቸው የሚል ክስ በማቅረብ ከነዚህ ሁለት ድርጅቶች ጋር ለሚያደርጉት ትግል ወያኔ ከጎናቸው እንዲቆምላቸው መጠየቃቸውን መጽሄቱ በእትሙ ላይ ካሰፈረው ለመረዳት ተችሏል።

በዚህ ድጋፍና መበረታታት በመታገዝ በአሁኑ ወቅት ደግሞ እነዚህ ባንዳ ካህናትና ተከታዮቻቸው የሃገሪቱን ሕግም ሆነ የቻሪቲን ሕግና መመሪያ አንቀበልም በማለት በኤምባሲ ተወካዮችና ለንደን ከደረሱ ካለፈው 7 ጀምሮ ማርያም ቤተ ክርስቲያንን ደጃፏን ረግጠው በማያውቁት አቡነ እንጦስ አማካኝነት በ29/12/2013 ቤተ ክርስቲያኗን ከፍተው ለማስረከብ መዘጋጀታቸውን ይፋ ማስታወቂያ በማሰራጨት ላይ ይገኛሉ።london 2

ከዚሁ ጋርም በኤምባሲና በወያኔ ጽ/ቤት አስተባባሪነት በለንደን ያሉና ከለንደን ውጪ ያሉ የሌላ ቤተ ክርስቲያን አባላት ተጓጉዘው መጥተው ማርያም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በብዛት በመገኘት ቤተ ክርስቲያኗን በወያኔ አገዛዝ ሹመኞችና በኤምባሲ ተወካዮች ቁጥጥር ሥር ለማዋል ኃይልና ጉልበት እንዲሆኗቸው ለማድረግ እየሰሩ መሆኑን አቡነ እንጦስ በሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለጸሎት ለተሰበሰበው ሕዝብ ይፋ ቅስቀሳ አድርገዋል።

ይህንን በሚያደርጉበት ጊዜ ግን ለአካባቢው ፖሊስ የተሰጠው ምክንያት የጸሎትና የአምልኮት መብታችንን ይከበርልን ዘንድ ቤተ ክርስቲያኑን ስንከፍት አስፈላጊው ትብብር ይደረግልን የሚል በመሆኑ ፖሊስ ያሉትን አምኖ ተቀብሎ ትብብር ሊያደርግላቸው እንደሚችል ይገመታል።

በለንደንና በመላው UK የምትገኙ ውድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታዮችና የማርያም ወዳጆች ሁሉ፡

መብትና ነጻነት ያለትግል፤ ድካምና መስዋዕትነት አይገኝምና ዛሬ የእምነትና የነጻነት ምልክታችን የሆነችውን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስደተኛው ኢትዮጵያዊ ሃብትና ጉልበቱን አስተባብሮ የንብረት ባለቤት ባደረጋት ማግስት የወያኔ ሹመኞች የውስጥ ባንዳዎችን በመሣሪያነት ተጠቅመው የሃይማኖቱን ማዕከል፤ ሃብትና ንብረቱን ነጠቁት ማለት ነገ በስደቱ ዓለም ነጻ የኮሚኒቲ ማዕከል፤ የፖለቲካ ተቋም፤ መኖር ቀርቶ በቤተሰብ ደረጃም ሆነ በግል ሰብ ሳይቀር በነጻነት ሃገር መብትና ነጻነትን አሳልፎ ለመስጠት ትለቁ በር ከፋች ስለሆነ ሁሉም የማርያም ወዳጅና ነጻነት ወዳድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ በ29/12/2013 ከ0800 ሰዓት ጀምሮ በርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ በመገኘት ቤተ ክርስቲያኑን እንዲከላከልና በስደት ሃገር የተጎናጸፈውን መብትና ነጻነቱን እንዲያስከብር በእመቤታችን በቅድስት ማርያም ስም ጥሪአችንን እናቀርባለን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!

በ http://londondebretsion.org/ ተከታተሉን

በ ourchurchdebretsion@gmail.com ኢ-ሚየል መረጃ ማግኘት ይችላሉ።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule