• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን

December 25, 2013 10:18 am by Editor Leave a Comment

ለርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አባላትና ወዳጆች፤ እንዲሁም በመላው UKየምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ሁሉ።

በስደት ላይ በሚገኘው ኢትዮጵያዊ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታይ ጥረት፤ ድካምና ተጋድሎ አማካኝነት ዘረኛው የወያኔ አገዛዝ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በዘረጋው የጎሳ ፖለቲካ ተጽዕኖ ሥር ሳትወድቅ በአስተዳደር ራሷን ችላ በመመራት ለከፍተኛ የዕድገት ደረጃ የበቃችው አንጋፋዋ የለንደን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን በአሁኑ ወቅት ለወያኔ ባደሩ ጥቂት ባንዳ ካህናትና ተከታዮቻቸው አማካኝነት ገንዘብና ጉልበታቸውን አስተባብረው፤ ጥረውና ግረው የሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ባለቤት ካደረጓት አባላቷ ተነጥቃ የወያኔ አገዛዝ ሹመኞችና ደጋፊዎች ንብረት እንድትሆን የሚካሄደው ጥረት ቀጥሎ ይገኛል።

london 1ቀደም ሲል እነዚሁ ከሃዲ ካህናትና ተከታዮቻቸው ወያኔ ከጎሳው መርጦ ከሾማቸው ከአቡነ እንጦስና ከነ መጋቢ ተወልደ ጋር ግንባር በመፍጠር በ12 October 2013 ሁለት ጳጳሳትን ከኢትዮጵያ በማስመጣት ቤተ ክርስቲያኗን በወያኔ አገዛዝ ሹመኞችና ደጋፊዎች ቁጥጥር ሥር ለማዋል ሙከራ ያደረጉ ሲሆን ይህ ሙከራቸው ግን ስደተኛው ኢትዮጵያዊ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ኢትዮጵያ ውስጥ በሕዝቤ ላይ የምትፈጽሙት ግፍ፤ በደልና ፍትሕ አልባነት አልበቃ ብሏችሁ በዚህ ነጻነትና ፍትሕ በሰፈነበት ሃገር ደግሞ ተመሳሳይ ድርጊት እፈጽማለሁ ብላችሁ አታስቡ በማለት ሰላማዊና ሕጋዊ ተቃውሞ በማድረግ ሙከራቸውን ሊያከሽፈው ችሏል።

ከዛም በመቀጠል የከሃዲዎቹ መሪ የሆኑት አባ ግርማ ከበደ አዲስ አበባ ድረስ በመሔድ ከወያኔ አገዛዝ ባለሥልጣኖችና የደህንነት ሰዎች ጋር በመምከር ለንደን በሚገኘው የወያኔ ኤምባሲና ሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ሕ.ወ.ሃ.ት) ጽሕፈት ቤት እየተረዱ የጀመሩትን ተግባር እንዲያጠናቀቁ መመሪያ ተቀብለው ተመለሱ።

አባ ግርማ ከበደም ለወያኔ አገዛዝ ያላቸውን ታማኝነት ለማረጋገጥ ሲሉ ዜና ቤተ ክርስቲያን ለተሰኘው መጽሄት ለንደን ላይ የሚያስቸግሩኝ ግንቦት ሰባትና ቅንጅት ናቸው የሚል ክስ በማቅረብ ከነዚህ ሁለት ድርጅቶች ጋር ለሚያደርጉት ትግል ወያኔ ከጎናቸው እንዲቆምላቸው መጠየቃቸውን መጽሄቱ በእትሙ ላይ ካሰፈረው ለመረዳት ተችሏል።

በዚህ ድጋፍና መበረታታት በመታገዝ በአሁኑ ወቅት ደግሞ እነዚህ ባንዳ ካህናትና ተከታዮቻቸው የሃገሪቱን ሕግም ሆነ የቻሪቲን ሕግና መመሪያ አንቀበልም በማለት በኤምባሲ ተወካዮችና ለንደን ከደረሱ ካለፈው 7 ጀምሮ ማርያም ቤተ ክርስቲያንን ደጃፏን ረግጠው በማያውቁት አቡነ እንጦስ አማካኝነት በ29/12/2013 ቤተ ክርስቲያኗን ከፍተው ለማስረከብ መዘጋጀታቸውን ይፋ ማስታወቂያ በማሰራጨት ላይ ይገኛሉ።london 2

ከዚሁ ጋርም በኤምባሲና በወያኔ ጽ/ቤት አስተባባሪነት በለንደን ያሉና ከለንደን ውጪ ያሉ የሌላ ቤተ ክርስቲያን አባላት ተጓጉዘው መጥተው ማርያም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በብዛት በመገኘት ቤተ ክርስቲያኗን በወያኔ አገዛዝ ሹመኞችና በኤምባሲ ተወካዮች ቁጥጥር ሥር ለማዋል ኃይልና ጉልበት እንዲሆኗቸው ለማድረግ እየሰሩ መሆኑን አቡነ እንጦስ በሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለጸሎት ለተሰበሰበው ሕዝብ ይፋ ቅስቀሳ አድርገዋል።

ይህንን በሚያደርጉበት ጊዜ ግን ለአካባቢው ፖሊስ የተሰጠው ምክንያት የጸሎትና የአምልኮት መብታችንን ይከበርልን ዘንድ ቤተ ክርስቲያኑን ስንከፍት አስፈላጊው ትብብር ይደረግልን የሚል በመሆኑ ፖሊስ ያሉትን አምኖ ተቀብሎ ትብብር ሊያደርግላቸው እንደሚችል ይገመታል።

በለንደንና በመላው UK የምትገኙ ውድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተከታዮችና የማርያም ወዳጆች ሁሉ፡

መብትና ነጻነት ያለትግል፤ ድካምና መስዋዕትነት አይገኝምና ዛሬ የእምነትና የነጻነት ምልክታችን የሆነችውን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስደተኛው ኢትዮጵያዊ ሃብትና ጉልበቱን አስተባብሮ የንብረት ባለቤት ባደረጋት ማግስት የወያኔ ሹመኞች የውስጥ ባንዳዎችን በመሣሪያነት ተጠቅመው የሃይማኖቱን ማዕከል፤ ሃብትና ንብረቱን ነጠቁት ማለት ነገ በስደቱ ዓለም ነጻ የኮሚኒቲ ማዕከል፤ የፖለቲካ ተቋም፤ መኖር ቀርቶ በቤተሰብ ደረጃም ሆነ በግል ሰብ ሳይቀር በነጻነት ሃገር መብትና ነጻነትን አሳልፎ ለመስጠት ትለቁ በር ከፋች ስለሆነ ሁሉም የማርያም ወዳጅና ነጻነት ወዳድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ በ29/12/2013 ከ0800 ሰዓት ጀምሮ በርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢ ውስጥ በመገኘት ቤተ ክርስቲያኑን እንዲከላከልና በስደት ሃገር የተጎናጸፈውን መብትና ነጻነቱን እንዲያስከብር በእመቤታችን በቅድስት ማርያም ስም ጥሪአችንን እናቀርባለን።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!

በ http://londondebretsion.org/ ተከታተሉን

በ ourchurchdebretsion@gmail.com ኢ-ሚየል መረጃ ማግኘት ይችላሉ።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule