• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በማወቅና በማድረግ እውነትን መኖር?

January 3, 2017 01:54 am by Editor 3 Comments

የሕይወትን እውነትና ትክክለኛ ትርጉም ተረድተን በሰላምና በፍቅር ለመኖር የሚያስችል የአእምሮ መታደስ ለማድረግ የሚከተለውን ላካፍላችሁ፡

ከሁሉ አስቀድሜ ልረሳው የማልችለውን መልካም ባህላችንን ተጠቅሜ እንኳን ለብርሃነ ልደቱ አደረሰን እላለሁ፤ እኔም ከሃገር፣ ከቤተሰብ፣ ከዘመድና ከጓደኛ ተለይቼ ባህሉንና ወጉን ጠንቅቄ ከማላውቀው ሕዝብ ጋር በእኛ አቆጣጠር ባለፈው ታሕሳስ 16 ቀን 2009 ዓ/ም የፈረንጆችን የገና በአል አክብሬ አሁን ደግሞ የእኛን ታሕሳስ 29 ቀን 2009 ላይ ከኢትዮጵያውያንና ከኤርትራውያን ወገኖቼ ጋር ለማክበር በዝግጅት ላይ ነኝ፤ እዚህ ላይ የቀን ልዩነት ቢኖርም የመከበሩ ዋና ዓላማና የቀኑ ባለቤት የሆነው ግን አንድ ነው፤ እሱም ከድንግል ማርያም ተወልዶ ሰው በመሆን በሰው ልጆች መካከል በመመላለስ “እግዚአብሔር ከእኛ ጋር” ለማለት ድፍረት እንዲሆነን “አማኑኤል” የተባለው ጌታ ኢየሱስ ነው።

ዛሬ ይችን አጭር መልእክት ጽፌ እንድልክ ያነሳሳኝ ዋና ጉዳይ በተለያየ ሚዲያ ሁላችንም እንዳየነው በዚህ የፈረንጆች ክሪስመስ አከባበር ላይ ሰፊ ትኩረት የተሰጠው ጉዳይ ስጦታን እርስበርስ መቀባበል እንጂ የበአሉ ዋና ባለቤት በሆነው ላይ አለመሆኑ አስገርሞኝ ነው፤ በእኛ አገርም ሁሉም እንደ አቅሙ ድፎ ዳቦው፣ ቆሎው፣ ዶሮው፣ በጉ፣ ቅርጫው፣ ጠላው፣ ጠጁ፥ አረቄው ከገና ጨዋታውና ከዘፈኑ ጋር አይቀርበትም፤ ይህን ሳስብ ታዲያ ምንም እንኳን ይህን በመሰለና መጠኑን በጠበቀ መልኩ በአግባቡ ደስ መሰኘቱ ባይከፋም እንደ ባለ አእምሮ ሰው ቆም በማለት የሚከተሉትን ሦስት የሕይወት ጥያቄዎች በማስተዋልና ትኩረት በመስጠት አብረን እንድናያቸው ወደድኩ፡-

1) ይህ በታላቅ ፌስታ የምናከብረው የልደት በዓል በእውነት ባምሳሉ ለክብሩ ለፈጠረው የአዳም ዘር በሙሉ ፋይዳው ምንድር ነው??? የሚለው ወሳኝ የህይወት ጥያቄ ዋናውና የመጀመሪያው ይሆናል ማለት ነው።

መልሱን የሚነግረን በዘላለም ፍቅሩና ምህረቱ ይህንኑ ሥራ የሠራልን ፈጣሪ አምላክ በህያው ቃሉ እንጂ ሰው በራሱ ሊመልስ ይቅርና የሚናገረውንና የሚጠቅመውን እንኳ የሚያውቅ አይመስለኝም፤ ሁሉን ቻይ የሆነው እግዚአብሔርም (በሉቃስ 2፡10-11) ላይ “እነሆ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና’’ ይለናል።

ይህን ቃል ለትምህርታችን ዘርዘር በማድረግ አብረን በትእግስት እስቲ እንየው፡- ለሕዝቡ ሁሉ ስላለ ሁላችንንም ይመለከተናል፤ ታላቅ ደስታ በመባሉ ደግሞ ጊዜያዊ የሆነው ሰው ሠራሽ ምድራዊ ደስታ ከሰማይ በመላእክት በኩል የመጣውን ደስታ ፈጽሞ አይተካውም ፤ በአጠቃላይ ከሰማናቸውና ከምንሰማቸው በላይ የሆነና የምሥራች ተብሎ የተነገረ፣ በሚያስፈራ በሽታም ሆነ በሌላ አስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ እንኳን ብንሆን ፍርሃታችንን አስወግዶ ደፋር የሚያደርገንና ፍጹም ፈዋሽ የሆነ የማያዳግም መድሐኒት ከሴቶች መካከል የተባረከች ከተባለች ከድንግል ማርያም ክርስቶስ ብቻ ሳይሆን ጌታና አማኑኤል የሆነ ለእኛ እንደተወለደልን ማስተዋልና የመለኮትን የመድሃኒትነት ስጦታ በቃሉ እንደተነገረን ትእዛዝ/Prescription/ ተቀብለን ሰዎች ከሚሰጡን ጊዜያዊ ስጦታ ባለፈ መልኩ መጠቀም መቻል ብልህነትና አስተዋይነት ይመስለኛል፤ ሕይወት ጅማሬ ብቻ ሳይሆን መጨረሻም አለውና።

እስቲ እዚህ ላይ ስጦታን በተመለከተ ይህን ልበልና ላጠቃል፣ አንድ የሚወደን ሰው ፍቅሩን ለመግለጽ በውድ ዋጋ ገዝቶ በሰርጋችን እለት በብዙ ሕዝብ ፊት ሲሰጠን አልቀበል ብንለው ምን ይሰማው ይሆን? ታዲያ በዮሐንስ ወንጌል 3፡16 ላይ እንደተጠቀሰው በሃጢአት ምክንያት ለሞተው የሰው ዘር በሙሉ ውድ አንድ ልጁን በመድኒትነት የሰጠውን የምህረት አምላክን ስጦታ አልቀበል ብንል ማነው የሚጎዳው? ሰጪው ደስ ብሎት ሲሰጥ ተቀባዩ ገብቶት በመቀበል ካልተጠቀመበት ሰጪውን እስከነስጦታው መናቅ አይሆንብንምን?ደግሞስ ለዚህ ሰሞኑን ለምናከብረው በዓል ምክንያት ስለሆነው ሰማያዊ ስጦታ ሰጪው እንድንመራበት በሰጠን መጽሐፍ ቅዱስ ላይ፡ አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ሰውን ሁሉ ስለመውደዱ /ዮሐ 3፡16/ ለገዛ ልጁ ሳይራራ ስለ ሁላችን በደል አሳልፎ የሰጠው /ሮሜ 8፡32/ ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገለጠ….ወዘተ ለሚለው ህያው ቃል እያንዳንዳችን በግል ምን ዓይነት መልስ ይኖረን ይሆን???

2) ሌላው የሕይወት ትክክለኛ ትርጉም በእውነት ምንድር ነው? የሚለው ይሆናል፤ ምናልባት መልሱ፡- መብላት መጠጣት፣ ንብረት ማካበት፣ ማግባትና ልጅ መውለድ፣ እድሜ ጠግቦ ጉዞን መጨረስ ይሆን ይሆናል፤ እነዚህ ሁሉ መልካም ናቸው፤ ነገር ግን ሁሉም ጊዜያዊና ጠፊ በመሆናቸው ብል ሳይበላው ከሞት ባሻገር አብሮ የሚሻገር የዘላለም ርስታችንን በዚች በተበላሸች ምድር እያለን ካላረጋገጥን እጅግ የሚያሳዝን መንፈሳዊ የሕይወት ክስረት ነው የሚሆነውና አሁንም እናስተውል::

3) ጌታ ኢየሱስ በምድር አስተምሮው ላይ ስም ሰጥቶ የሃይማኖት ድርጅት በመመስረት የዚህ ሃይማኖት ተከታይ ካልሆናችሁ መንግሥተ ሰማይ አትገቡብ አላለም፤ ነገር ግን በሩ እኔ ነኝ በእኔ የሚገባ ይድናል/ዮሐ 10፡9/፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም /ዮሐ 14፡6/፤ ልጅም ትወልዳለች እርሱ ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ያድናቸዋል /ማቴ 1።21/፤ ልጁ ያለው ሕይወት አለው የእግዚአብሔር ልጅ የሌለው ሕይወት የለውም /1ኛ ዮሐ 5፡12/፤ በአጠቃላይ ከዘፍጥረት እስከ ራእይ ድረስ ያሉት መጽሐፍት የሚናገሩት የምህረት አምላክ የሆነው ቸሩ እግዚአብሔር በኃጢአት ምክንያት ከኤደን ገነት የወጣውን የአዳም ዘር በልጁ ሞትና ትንሳኤ መልሶ ማስገባቱን ነው፤ ወንድም ወንድሙን አያድንምና /መዝ 49፡7/ ስለዚህ የገዛ ክንዱ መድሃኒት አመጣለት /ኢሳ 59፡16/ ስለሚል ባለንበት ሃይማኖት ውስጥ በመሆን መጽሐፍ ቅዱስን ትኩረት ሰጥተን ለማጥናት ቀኑ ሳይመሽ አሁኑኑ እንድንጀምር በእግዚአብሔር ፍቅር ከልቤ አሳስባለሁ፤

ትናንት ላናገኘው አልፏል፤ ነገም የእኛ መሆኑን አናውቅም፤ ዛሬ ግን እንድንጠቀምበት የተሰጠን የእድሜያችን እንቁ ሃብት ነውና ብልህና አስተዋይ እንሁን።

ቸሩ በቸርነቱ ይርዳን!!!

አሜን።
እውነቱ ይነገር ነኝ (eunethiwot@gmail.com)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. ጎይቶም says

    January 12, 2017 12:43 am at 12:43 am

    እውነት ነው፤ እኛ ሁላችን ልናስብበት የሚገባና ቆም ብለን በማሰብ ድካማችንን በማስወገድ እውነተኛ ማንነታችንን በፍቅርና በሰላም አብረን ለመኖር ብልህ ሰዎች እንሁን!

    Reply
  2. Tadesse says

    January 30, 2017 07:14 pm at 7:14 pm

    Agree and liked it very much.

    Reply
  3. Mulugeta Andargie says

    February 3, 2017 07:46 am at 7:46 am

    Guys!!! Politics has no truth as mathematics has. It is human philosophy. Otherwise, our theory would be metaphysics. It will not be materialistic. Don’t expect from any politician truth.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule