• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ደስ ይበለን በዚህ ብስራት

April 3, 2014 03:14 am by Editor Leave a Comment

አድዋ! በድልሽ የተገኘ ምስራች

ጊዜው ረዘመ ብሎ ሳይሰለች

ዕድሜው በዕድሜ ላይ እየጨመረ

ጀግኖችን እንደገና እያነሳ እየደመረ

ዛሬም በልጅ ልጅ ልጅ ልጅ ልጅ….ታሪክሽ ታውቀ

የድል ብስራትሽ በዓለም ዓለም ዓለም ዓለም….አንጸባረቀ

የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ሻማ

መሆንሽ ተወራ ሀገር ለሀገር ተሰማ

ይሄው ተከበረ መቶ አስራ ስምንተኛ ዓመት

ሁላችንም ደስ ይበለን በዚህ ብስራት

የአበው ተጋድሎ የጀግንነት ደም

ታሪኩ ተወሳ በከንቱ ፈሶ አልቀረም

የአባ ዳኘው መድፍ አሁንም አገሳ መልሶ

የጣይቱ ስም ተጠራ ተወደሰ አባ ነፍሶ

እንደገና አስተጋባ የአድዋ ድል

ገኖ ታየ ተደነቀ አባ መቻል

ሀብተ ጊዮርጊስ አባ መላ

ስራው በድጋሚ ጎላ።

 አድዋ! በድልሽ የተገኘ ምስራች

ጊዜው ረዘመ ብሎ ሳይሰለች

ዕድሜው በዕድሜ ላይ እየጨመረ

ጀግኖችን እንደገና እያነሳ እየደመረ

ዛሬም በልጅ ልጅ ልጅ ልጅ ልጅ….ታሪክሽ ታውቀ

የድል ብስራትሽ በዓለም ዓለም ዓለም ዓለም….አንጸባረቀ

ራስ አሉላ አባ ነጋ

በከፈለው የደም ዋጋ

ስሙ ዛሬ ሲነሳ

የባልቻ የገበየሁ አብሮ ሲወሳ

እነ አባተ ቧ ያለው

እነ ቃኘው እነ ውቃው

ከተኙበት ቀና ብለው

መቃብሩን ፈነቃቅለው

የአድዋን ድል አበሰሩ

ጀግንነትን አስተማሩ

አድዋ! በድልሽ የተገኘ ምስራች

ጊዜው ረዘመ ብሎ ሳይሰለች

ዕድሜው በዕድሜ ላይ እየጨመረ

ጀግኖችን እንደገና እያነሳ እየደመረ

ዛሬም በልጅ ልጅ ልጅ ልጅ ልጅ….ታሪክሽ ታውቀ

የድል ብስራትሽ በዓለም ዓለም ዓለም ዓለም….አንጸባረቀ

የአበው ተጋድሎ ያፈሰሱት ደም

ተወሳ ተነገረ ከንቱ አልቀረም

የሚኒሊክ መድፍ አሁንም አገሳ መልሶ

የጣይቱ ስም ተጠራ ተወደሰ አባ ነፍሶ

ትውልዱም የአባቶቹን ድል በማደስ

የጀግንነት ስራቸውን እያነሳ በማውደስ

ለመጪውም ጊዜ እንዲሻገር

ኢትዮጵያ በታሪኳ እንድትከበር

የድርሻውን በተግባር አስመሰከረ

ይሄው የድል ቀኑን በአንድነት አከበረ

 አድዋ! በድልሽ የተገኘ ምስራች

ጊዜው ረዘመ ብሎ ሳይሰለች

ዕድሜው በዕድሜ ላይ እየጨመረ

ጀግኖችን እንደገና እያነሳ እየደመረ

ዛሬም በልጅ ልጅ ልጅ ልጅ ልጅ….ታሪክሽ ታውቀ

የድል ብስራትሽ በዓለም ዓለም ዓለም ዓለም….አንጸባረቀ

የጥቁር ህዝቦች የነፃነት ሻማ

መሆንሽ ተወራ ሀገር ለሀገር ተሰማ

ይሄው ተከበረ መቶ አስራ ስምንተኛ ዓመት

ሁላችንም ደስ ይበለን በዚህ ብስራት።

———————————

ማርች 30/2014 (መጋቢት 21/2006) ዓ.ም በስዊድን የዓድዋን 118 ኛ የድል በዓል ስናከብር የቀረበ።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule