• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እውነቱ ይውጣ!

May 2, 2015 04:39 am by Editor 1 Comment

ሴቶችን በወንዶች ፊት፣ ወንዶችን በሴቶች ፊት ልብስ እያስወለቁ የአካላቸውን ክፍሎች ሁሉ ለማየት የሚያስችል እንቅስቃሴ አንዲሠሩ ማስገደድ በሽተኞችን ያስደስታል፤ የምርመራ ዘዴ ግን አይደለም፤ ውርደት እንዲሰማቸው ከሆነ በወራዶች ሰዎች ፊት የምን መዋረድ አለ? ወራዶች እነሱ ደረጃ ላይ ከእነሱ ጋር ያስተካክላሉ አንጂ አያዋርዱም፤ በሌላ አነጋገር ወራዶች አያዋርዱም፤ ወራዶቹ ደንቆሮዎችም ሆነው ነው እንጂ ልብስ የሚያስወልቁ እነሱ ብቻ አይደሉም፤ ሀኪሞችም ልብስ አስወልቀው፣ አጋድመው በጣታቸውም ሆነ በመሣሪያ የፈለጉትን የአካል ክፍል አንደፈለጉ ያደርጉታል፤ ወራዶቹና ደንቆሮዎቹ ከሚያደርጉት የሀኪሞቹ የሚለየው ሀኪሞቹ ሰዎችን ለማዳን ሲሉ ነው፤ ወራዶቹና ደንቆሮዎቹ ግን የራሳቸውን ሱስ ለማርካት፣ የራሳቸውን ህመም ለማስታገስ ነው፤ ወራዶቹንና ደንቆሮዎቹን ከመለዮአቸው አራቁቻቸዋለሁ!

ከነውር በቃላት ወደነውር በተግባር፣ ያውም በመሥሪያ ቤት!

ዱሮ ዱሮ ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ቲያትር ፊት ለፊት የአንድ ኢጣልያዊ ቡና ቤት ነበር፤ እዚያ ውጭ ተቀምጠን ቡና ስንጠጣ አንዲት ውብ ሴት ወደጸጉር መሥሪያው ቤት ስትመጣ የሁላችንም ዓይኖች እየዘለሉ እስዋ ላይ ዐረፉ፤ ከሦስታችን አንዱ ስለሴትዮዋ የወሲብ ችሎታ በዝርዝር መናገር ሲጀምር ሁለታችን ተያየንና አፈርን፤ ጨዋታው የጣመለት መስሎት ሲቀጥል የሕግ ባለሙያ የሆነ ጓደኛዬ አቋረጠውና ‹‹ስማ! ይህን ጊዜ እናትህ በአንድ ቦታ ስታልፍ አንዱ እንዳንተ ያለ ስለእርስዋ ችሎታ ያወራ ይሆናል!›› አለው፤ ሊጠጣ ወደአፉ ያስጠጋውን ስኒ ቁጭ አደረገና ተነሥቶ ሄደ፡፡

ሥልጣን ተሰጥቷቸው ሴቶችን ልብስ እያስወለቁ ምርመራ ነው የሚሉ በእናቶቻቸውና በእኅቶቻቸው ላይ ሊደርስ እንደሚችል አይገነዘቡም ይሆናል፤ ደንቆሮ የሚያደርጋቸውም ይኸው ነው፤ የአንዱ እናት አንድ ቦታ ላይ ራቁትዋን ቆማ በሽተኞች ተሰብስበው ሲስቁባት፣ በሌላ ቦታ ደግሞ ጓደኛው የእሱን እናት ወይም እኅት ያንኑ እያደረገ ያስቅባት ይሆናል፤ አንተ በእኔ እናትና በእኔ እኅት አስቅባቸው፤ እኔ ደግሞ በአንተ እናትና በአንተ እኅት አስቅባቸዋለሁ፤ ይህንን እየሠራን ኑሮአችንን እናቃናለን፤ እቤታቸው ሲገቡና ከእናቶቻቸውና ከእኅቶቻቸው ጋር ሲቀመጡና ሲበሉ (?!) ሰው ይመስላሉ፤ እነዚያም ግፉ የተፈጸመባቸው እናቶችና እኅቶች ‹ነውራቸውን› ምሥጢር አድርገው ለሰው ስለማይናገሩ ግፈኞችና የግፍ ሰለባዎች አብረው ይበላሉ!

አሁን ለመጀመሪያ ጊዜ አንዳንድ ሴቶች የደረሰባቸውን ተናገሩ፤ አሁን ያፍራሉ የተባሉት እውነቱን ራቁቱን አወጡትና ከእፍረት ነጻ ወጡ! እውነቱ ሲወጣ የሚያፍረው ማን ነው? ደካማዎቹና የግፍ ሰለባ የነበሩት በጭራሽ አያፍሩም፤ የሚያፍሩት ግፈኞቹ ናቸው፤ የሚያፍሩት የሕዝብን አደራ በማቆሸሻቸው፣ በሥልጣን በመባለጋቸው፣ የሕዝብንና የአገርን ክብር በማዋረዳቸው ያፍራሉ፤ ኅሊናቸው በየቀኑ ነፍሳቸውን አርባ ሲገርፋት እየሳሳች እንቅልፍ ትነሳቸዋለች፡፡

ለመሆኑ በአገሩ ሊቃነ ጳጳሳት፣ ጳጳሳት፣ መነኮሳት፣ ቀሳውስት — ሼሆች፣ ሽማግሌዎች በአገሩ የለንም?

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    May 5, 2015 03:52 am at 3:52 am

    >>>> ለመሆኑ በአገሩ ሊቃነ ጳጳሳት፣ ጳጳሳት፣ መነኮሳት፣ ቀሳውስት — ሼሆች፣ ሽማግሌዎች በአገሩ የለንም? ሊ/ጠበብት መስፍን ወልደ ማርያም..”ዳኛማ ቢኖር!” አሉ እኛ የእኔ አባት…ለመሆኑ ይህ ሁሉ ማዕረጋቸውን የዘረዘሯቸው ከሥም አልፎ በተግባር ቢኖሩን ምንኛ ሀገረ ኢትዮጵያ የተባረከችና የታደለ ህዝብ በሆነ!? እንግዲህ አሁን አውርቶ አደር..አድርባይ..እበላ ባይ…ይህ በደላላ አየር በአየር የተገኘ የትምህርት ወረቀት ጭንቅላታቸውን ያደነዘዘው ምላሳቸው የረዘመ፣ ልባቸው የተደፈነ፣ፈርሃ እግዝሐብሄር የሌላቸው ልማታዊ ወሮ በሎች በበዙበት፣ ክልላዊ ተቧባኞች ዙሪያውን በጥቅማጥቅም (ራዕይ)የተተበተበችና የምትቦጨቅ ሀገር ለመሆኑ በየትኛውን ሕግ፣ ሃይማኖት፣ ባሕልና ወግ ኖረው ለዚህና ለመጪው ትውልድ ይጨነቃሉ…”አሹቅ መብላት ያልፈለገ አንገቱን ለካራ ሰጠ” ይላሉ..፷፪ ሆነው ፬ነጥብ ፱ ሚለየን ብር አዋጥው በሰው ሀገር ከሚገደሉ ለምን ከእኛ ጋር ተጫርተው ከገበያ ውጭ አናደርጋቸውም ነበር” ይላሉ..ሌላው ዓለም ኢትዮጵያውያን ክርስቲያን በሊቢያ በረሃ በጥይትና በሜንጫ ተሰው እያለ ሀዘኑን ሲገልጽ …የኢህአዴግ ቡድን “ማንነታቸው ገና ያልታወቀ ሕገወጥ ስደተኞች፤ “ይህ ለሌላውም ወጣት ጥሩ መማሪያ የሚሆን ነው ብለው ውስጣዊ ደስታቸውን ገልፀዋል!? …ለመታየት በእየአዳራሹ የፀሐይ መነፅር ያደረጉ የአዞ እንባ የሚያነቡ(ዘመነኛ ልማታዊ አገልጋዮች)ጭረሽም ሰማዕታትንና ቤተሰቦቻቸውን ማስታወቂያ መስሪያ አደረጓቸው…የሐዘኑን ድንኳን የምርጫ ካርድ አደሉበት… ለመሆኑ የኋላዊት እመቤት አዜብ ጎላ ልጆቼን በኢትዮጵያ ህዝብ ዕርዳታ እያሳዳግሁ በጋራ ራዕዩን ሳይበረዝና ሳይሸረፍ አስቀጥላለሁ ብለው ለሃጭና ንፍጥ ሲዝረከረክ ታዝበው ለክልላዊ ፎቶ ብቻ ብቅ ሲሉ ለሰማዕታት ለቅሶ ጥቁር ለብሰው ደረት አልደለቁም ጥፍት አሉ።የአዲስ አበባ ሕዝብ ውለታው ይህ ነበር? እንግዲህ አንዳንድ ከጥፋት ተርፈው የተገኙም ሃይማኖታቸውን ጠብቀዋል “ብጹሕ ወቅዱስ አቡነ መቃሪዎስ ለ፳፭ኛ በዓለ ሲመታቸው መታሰቢያነቱ በሊቢያ ለተሰውት እንዲሆን አሳሰቡ!”በሊቢያ የተሰውት ኢትዮጵያውያን ክርስትያኖች “ሰማዕታተ ኢትዮጵያ በምድረ ሊቢያ” በመባል እንዲጠሩና ገድላቸውም በየዓመቱ እንዲዘከር ቅዱስ ሲኖዶስ ወሰነ!!!

    “ማሌሊቶች ሃይማኖተ ቢስ ነን አይሉም! ቃሊቲ እስር ቤት ክርስቶስ በመስኮት ገባ ብለው እያለቀሱ ታምራት ለዓይኔ እንዳያሳዩ “መንግስትና ሃይማኖት የተለያየ ነው” “ሃይማኖታዊ መንግስት የለም!”..የሚሉ ጩልሌዎች ችግሩ ያለው የሃይማኖት ወገንተኝነት/ተጽዕኖ በሌላው ላይ እንዳይኖር ተባለ እንጂ..በነፃ ገበያና በነፃ ሃይማኖት በግብረሰዶም ሀገርና ትውልድ በክሎ አጥፍቶ መጥፋት ሌላ ወንጀል ነው። ግፍ በዝቶ የተረፈበት በከንቱዎች፣ በከሃዲዎችና በእርጉሞች የተወረረች አላግባቡ እየረከሰች ያለች ክብርት ሀገር “አሁን ለመጀመሪያ ጊዜ አንዳንድ ሴቶች የደረሰባቸውን ተናገሩ፤ አሁን ያፍራሉ የተባሉት እውነቱን ራቁቱን አወጡትና ከእፍረት ነጻ ወጡ! እውነቱ ሲወጣ የሚያፍረው ማን ነው? ደካማዎቹና የግፍ ሰለባ የነበሩት በጭራሽ አያፍሩም፤ የሚያፍሩት ግፈኞቹ ናቸው፤ የሚያፍሩት የሕዝብን አደራ በማቆሸሻቸው፣ በሥልጣን በመባለጋቸው፣ የሕዝብንና የአገርን ክብር በማዋረዳቸው ያፍራሉ፤ ኅሊናቸው በየቀኑ ነፍሳቸውን አርባ ሲገርፋት እየሳሳች እንቅልፍ ትነሳቸዋለች፡፡በአርግጥ ለአሁኑ ሆዳቸው ክብራቸው፣ እራቁታቸውን ተወልደው መሬት ላይ ባዶ ቂጣቸውን ተንደባለው ማደጋቸውን እረሱ ከጥጋብ በስተጀርባ እርሃብ፣ ከትምህኪት ጎን ቁርሾ፣ ከበደል ላይ በቀል..ከጭለማውም ባሻገር ብርሃን አለ።ሁሉም ለአምጭው ይከፈላል በለው!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule