• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከሩስያ በአሜሪካ የፖለቲካ ሂደት ጣልቃ ገብነት ምን እናነባለን?

March 31, 2017 12:29 am by Editor 2 Comments

አሜሪካ ለሩስያ የፖለቲካ ተቀናቃኝ ናት።

የአሜሪካ ርዕዮተ ዓለም ከሩስያ ርዕዮተ ዓለም የተለየ ነው።

በአሜሪካ፤ ከሀገሪቱ የግለሰብ የሃሳብ የነፃነት የተነሳ፤ ከሀገራቸው ይልቅ ራሳቸውን የሚያስቀድሙ ሰዎችም በመንግሥት መዋቅርም ይሁን በንድግ ተግባሩ ውስጥ በኃላፊነት የሚገኙ አሉ። ይህ የግል አመለካከታቸው፣ የራሳቸው ከመሆኑም በላይ፤ በማንም ግለሰብ፤ የበላይ አለቃቸውም ሆነ ለነሱ ተጠያቂ በሆኑ ግለሰቦች ዘንድ፤ አያስገምታቸውም። በአንጻሩ፤ እንደሩስይ ባሉ የአምባገነኖችን የበላይነት በሚያመቻቹና በሚያሞግሱ ሀገራት፤ (ይህ አብዛኛውን በማደግ ላይ ያሉ ሀገራትን ያጠቃልላል። የኢትዮጵያውን የትግሬዎች ወገንተኛ ወራሪ ቡድንንም ይጨምራል።) ነዋሪዎቹ፤ ግለስብ ግለሰብነቱን አጥቶ፤ በገዥዎቹ ፍላጎት የሚተረጎም ማንነትን እንዲቀበሉ ስለሚገደዱ፤ የገዥዎቻቸው አገልጋዮች ናቸው ማለት ይቻላል። ከዚህ የተነሳ፤ ለገንዘብ ሊያድሩ የሚችሉ ግለሰቦች በየትኛውም ሀገር ያሉ ቢሆኑም፤ እንደሩስያ ያሉት ሀገሮች በኃላፊነት የሚያስቀምጧቸውን አበጥረው ተገዥ የሚሆኑትን የሚያወጡ ሲሆን፤ እንደ አሜሪካ ያሉት፤ ክፍትነታቸው ለብዙኀኑ ባደባባይ ያን የግል አመለካከታቸውን ለማወጅ አመቺ ነው።

እንግዲህ በመካከላቸው ባለው ልዩነትና ውድድር የተነሳ፤ አሜሪካና ሩስያ፤ በየትኛውም መስክ ቢሆን፤ ፉክክራቸው ቅድሚያ ይይዛል። ለዚህም፤ ሩስያ፤ በመንግሥት ደረጃ አሜሪካን ለማዳከምና የራሳቸውን ጥቅም ለማስቀደም፤ ሌት ተቀን ይሠራሉ። አሜሪካ ይሄን አታደርግም ማለት አይደለም። ነገር ግን፤ አሜሪካ የበላይነት አለኝ የሚል እብሪት ስላላት፤ “እኔ የምለው ሁልጊዜም ተቀባይነት አለው!” በሚል ጋቢ ተጎናፅፋ፤ “ዓለምን የምመራው እኔ ነኝ፤ ሩስያ ደካማ ናት!” በሚል፤ በሩስያ ላይ ዕቀባ መጣልና የመሳሰሉትን በቦታው አስቀምጣለች። በተወሰን ደረጃም አብረው የሚሰለፉላት ምአንግሥታት አሉዋት። በዚህ የፖለቲካ ጨዋታ መካከል ነው የሩስያን ጣልቃ ገብነት የምናየው።

ሩስያ፤ በአሜሪካ መንግሥት የሚደረገውን ውሳኔ ማወቅ ብቻ አይደለም፤ ከቻለች፤ በውሳኔ አሰጣጡ ላይ እጇን ማስገባት ትፈልጋለች። ማን የጠላቱን እንቅስቃሴ ማወቅ የማይፈልግ አለ? በየሀገሩስ ያሉት ኤምባሲዎች ዋናው ሥራቸው ምን ሆኖ ነው! ሩስያ ግን የሞትና የሽረት ጉዳይ አድርጋ ነው የያዘችው። አያስገርምም። ዓለም መተሳሰርና መተባበር ለእያንዳንዱ ሀገር የሥልጣኔ ግስጋሴና የቴክኖሎጂው እድገት ወሳኝ በሆነበት ወቅት፤ ከህዝቡ ነፃነት ይልቅ የራሳቸውን በሥልጣን መሰንበት የሚያስቀድሙ ሀገሮች፤ ተገደውም ሆነ ወደው ለብቻ መቀመጣቸው፤ አስጊ ነው። ሰሜን ኮሪያ፣ ኤርትራ፣ ሶሪያ፣ ይአትግሬዎቹ ገዥ ቡድን የነገሠባት ኢትዮጵያ፣ የዚህ ባለቤቶች ናቸው። እናም ያንን ሚዛን መድፊያ የግድ ማቀድ፤ ለሩስያ ግድ ሆኖባታል። ታዲያ የሩስያን መሯሯጥ የሚረዳ አካል ደግሞ፤ በአሜሪካ ውስጥ ይገኛል። ይሄም፤ በአሜሪካ ያሉ የራሳቸውን ጥቅም ከሀገራቸው ጥቅም አስበልጠው የሚገኙ ግለሰቦች ናቸው። እንደነዚህ ያሉ ግለሰቦች፤ ለገንዘብ ሲሉ፤ በሰላይነት፣ በተቀጣሪነት እናም መሳሪያ በመሆን ተገዝተው ለሩስያ የሚያገለግሉ ናቸው። ለግልሰብ ጥቅማቸው የሚንሰፈሰፉ ሰዎች በግል አይኖሩም። በጎናቸው መሰሎቻቸውን ይኮለኩላሉ። እናም የብርታታቸው ምሰሶዎች፤ ሌሎች እንደነሱ ያሉ የግል ጥቅም አሳዳጆች ናቸው።

ከግለሰብ ጥቅም አንጻር፤ ግለሰብ ዶናልድ ትራምፕ፤ ራሳቸውን ወዳድ፤ ማንንም ረጋግጠው ወደ ላይ ለመውጣት ቅንጣት የማይሰቀጥጣቸው ናቸው። እናም፤ ማንም በሚፈልጉት መንገድ ወደሚፈልጉት ቦታ ለመሄድ እንቅፋት የሚሆንባቸውን፤ ከሰይጣንም ጋር አብረው ለማጥቃት፤ ወደኋላ አይሉም። ይህ የሩስያ ጉጉትና የትራምፓ ራስ ወዳድነት፤ ባንድ ላይ ተጋጥመው መገኘታቸው ነው፤ ለዚህ አሁን ላለንበት የሩስያ ጣልቃ ገብነት መሠረቱ።

የሩስያ አሜሪካን የመቦርቦር ጥረት አዲስ አይደለም። እስከዛሬም ስታደርገው የነበረ ነው። የትራምፕም ጥቅሙን ማሳደድና የሀገሩን ጥቅም ወደ ትቢያ መጣል አዲስ አይደለም። የነበረ ነው። ምንም ታክስ አለመክፈሉ ብቻ ሳይሆን፤ አሁንም የታክስ መዝገቡን አላሳይም እንዳለ በእብሪት መቀመጡ፤ ምስክር ነው። በዚህ ስሌት፤ የቀድሞዋ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ኃላፊ የነበሩትን ሄለሪ ክሊተንን ለማቸነፍና ፕሬዘዳንት ለመሆን፤ ከሩስያ ጋር ለማበር ፈላጊ ሆኖ ቢገኝ፤ ሩስያም አደገኛ ይሆኑብኛል ያላቸውን የአሜሪካን የቀድሞ የውጭ ጉዳይ ኃላፊዎን ሄለሪ ክሊንተንን ለማስወገድና እንደ ፈረስ እጋልበዋለሁ ብለው የተመኙትን ዶናልድ ትራምፕን ለፕሬዘዳንትነት ለማብቃት፤ ሁለቱም ተጠቃሚዎች የሚሆኑበት አጋጣሚ ነበር። እናም ሌት ተቀን ሠሩበት። በሂደቱም ዶናልድ ትራምፕ ተመረጠ።

ውሎ አድሮ ግን፤ የአሜሪካ ልዩ የሆነ መንግሥታዊ አወቃቀር፣ አሰራርና በውስጡ የተሰገሰጉ ሀገር ወዳዶች፤ “ዝም ብለን አናይም!” በማለት፤ ውስጥ ውስጡን ሚስጢር በማውጣት፤ ይሄው እንዲጋለጥ አደረጉት።

ከዚህ የምናነበው፤ በታጋዩ ወገናችን ውስጥ የሚካሄደውን ክስተት ነው። በውጥረት ላይ ያለው የትግሬዎች ገዥ ቡድን፤ በውስጥና በውጪ ያለበትን ሕዝባዊ ተቃውሞ ለመከላከል፤ በሀገር ውስጥ፤ ፍጹም አረመኔያዊ በሆነ መንገድ፤ ትክክለኛ ያልሆኑ ሕጎችን በማውጣት፣ አላግባብ ሰዎችን አጋፎ በማሰር፣ ሕጉን አጣሞ ፍርድ በመሥጠት፤ የለ ርህራሄ ሕዝቡን እያሰቃየ ነው። በውጪ ያለውን ተቃውሞ ደግሞ፤ ከፍተኛ ወጪ በማፍሰስ፤ የትግል አንድነት እንዳይፈጠር፣ ሆድ አደሮችን ሰግሰጎ በማስገባት፤ ትግሉ ባለበት እንዲቆም አድርጎታል። ምንም እንኳን ከመቼውም የከፋ ሥርዓት በሀገራችን ቢሰፍንም፤ ምንም እንኳን ብዙኀኑ በዚህ በትግሬዎች ገዥ ቡድን ተጠቂ ቢሆንም፤ ምንም እንኳን ታጋዩ ብዙ ቢሆንም፤ አንድነት ከመቼውም በላይ ርቆ ሄዷል። የትግል አንድነት ቀርቶ፤ ተቀራርቦ የመነጋገር ዕድሉ እንዳይሆን ሆኗል። የትግሬዎቹ ገዥ ቡድን ሊኮራ ይገባዋል። ምንም እንኳን ሙሉ በሙሉ ይህ የተደረገው በትግሬዎቹ ገዥ ቡድን የገንዘብ ፍሰትና የግለሰቦች ሆዳምነት ብቻ ነው ባይባልም፤ በአንድነት የመታገሉን ሁኔታ ያደቀቀው፤ በአብላጫው፤ የዚሁ ተወጣሪ ቡድን ጭንቀትና የሆዳሞች ስግብግብነት መሆኑን መካድ አይቻልም። በርግጥ እኔ እበልጥ እኔ እበልጥ ፉክክሩና፤ እኔ ብቻ ነኝ ትክክለኛ ባይነቱ ሚና አለው። ሌላም ተጨማሪ፤ ለዚህ ጸሐፊ ያልታየው ሁኔታ ሊኖር ይችላል። ባጠቃላይ ከሩስያ ጣልቃ ገብነት የሚታየው ይህ ነው።

አንዱዓለም ተፈራ – የእስከመቼ አዘጋጅ

eske.meche@yahoo.com

አርብ፣ መጋቢት ፳፪ ቀን፣ ፳፲፱ ዓመተ ምህረት (03/31/2017)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Mes says

    March 31, 2017 02:21 pm at 2:21 pm

    አቶ አንዳለም ተፈራ በ CNN ፕሮፓጋንዳ አይምሮአቸው ዞሯል መሰለኝ ፣ ፑቲን ራሺያን ከዲክታይተሮች የነጭ አሽከሮች ጋር እንድ ማደወረጋቸው ፍፅም ስህተት ነው ፣ ምእራባውያን የቀድሞው ሶቪየት ተሸንፎ ፈረሰ ብለው እራሳቸውን እንዳሸናፊ ቆጠሩ: እውነታው ግን ሶቪየት ህብረት bankrupt ሆነ ታዲያ ምእራቡ የቀድሞውን የአለም ሰላም ስምምነቶች ከቀድሞ ሶቪየት ጋር የነበራቸውን መሻር ብቻ አይደለም በናቶ ጦር ሩሲያን መክበብ ጀመሩ ፣የማይፈልጉትን መንግሥታት አይ ሲስን በመጠቀም መንግስትን ግልበጣ ጀመሩ ፣ አለምን ከፍተኛ ወደ ኒኒኩለር ጦር አስጊነት ቀየሩት ፣ታዲያ ይህን በመቃወምና የአገርዋን ከበባ ለመቋቋም የምትወስደው ሩሲያ ከወያኔ ጋር ትመሳሰላለች ፣ አቶ አንዱአለም እዛው በአገራችን ፖለቲካ ቢቆዩ ይሻላል እንጂ ኢንተርናሽናል ትንሽ ተዘርባብቆባቸዋል ፣ ሩሲያ ናፖሊዮንን ያሸነፈች ሂትለርን ትምህርት የሰጠች ናት ፣ ሩሲያ ጦርነት መጀመር ሳይሆን ጦርነትን መጨረሽ ግን የተካነች ናተወና ፣ ጀግናን ህዝብና መሪዎችን ከኢትዮጵያ ሹምባሽ መሪዎች ጋር አንድ ማድረግ አለማወቅ ብቻ ሳይሆን አሳፋሪ አባባል ነው ።

    Reply
  2. የዜኑ ሰው says

    March 31, 2017 08:37 pm at 8:37 pm

    ምናልባትም አቶ አንዱአላም ተፈራ በምእራብያኑ ሚዲያ በሚሰሙት ፕሮፖጋንዳ ሳይሸወዱ አይቀሩም መሠለኝ …..እንጂማ ይሄንን እንቶ ፈንቶ የሆነ ፁሁፍ ባላቀረቡ ነበር፡፡
    የቀድሞዋን ሶቭዬት ህብረት ከታላቅነቷ አውርደው እና በታትነዋት አቅመ ቢስ ያደረጓትን እንደነ ሚካኤል ጎርባጆቭ እና ዬልሲን ያሉ የአሜሪካን ተላላኪና ባንዳ መሪዎችን ከወያኔ ጋር ማመሳሰል ሲገባ የተናቀችው ራሺያን ከወደቀችበት አንስቶ: ከአቅመ ቢስነት ወደ ሀያልነት ከፍ አድርጎ ወደ ቀድሞዎ ገናናነቷ የመለሳትን ጀግናና ሀገር ወዳድ መሪ የሆነውን ፑቲንንና መንግስታቸውን ከትግራዩ ወያኔ ጋር ማወዳደር ለተናጋሪው ይቅርና ለሠሚውም ይሰቀጥጣል፡፡ ይመስለኛል አቶ አንዱአለም አሁን ስላለው የራሺያ መንግስትም ሆነ ስለ ፑቲን የሚያውቁት አንዳችም ነገር የለም

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule