• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከሩስያ በአሜሪካ የፖለቲካ ሂደት ጣልቃ ገብነት ምን እናነባለን?

March 31, 2017 12:29 am by Editor 2 Comments

አሜሪካ ለሩስያ የፖለቲካ ተቀናቃኝ ናት።

የአሜሪካ ርዕዮተ ዓለም ከሩስያ ርዕዮተ ዓለም የተለየ ነው።

በአሜሪካ፤ ከሀገሪቱ የግለሰብ የሃሳብ የነፃነት የተነሳ፤ ከሀገራቸው ይልቅ ራሳቸውን የሚያስቀድሙ ሰዎችም በመንግሥት መዋቅርም ይሁን በንድግ ተግባሩ ውስጥ በኃላፊነት የሚገኙ አሉ። ይህ የግል አመለካከታቸው፣ የራሳቸው ከመሆኑም በላይ፤ በማንም ግለሰብ፤ የበላይ አለቃቸውም ሆነ ለነሱ ተጠያቂ በሆኑ ግለሰቦች ዘንድ፤ አያስገምታቸውም። በአንጻሩ፤ እንደሩስይ ባሉ የአምባገነኖችን የበላይነት በሚያመቻቹና በሚያሞግሱ ሀገራት፤ (ይህ አብዛኛውን በማደግ ላይ ያሉ ሀገራትን ያጠቃልላል። የኢትዮጵያውን የትግሬዎች ወገንተኛ ወራሪ ቡድንንም ይጨምራል።) ነዋሪዎቹ፤ ግለስብ ግለሰብነቱን አጥቶ፤ በገዥዎቹ ፍላጎት የሚተረጎም ማንነትን እንዲቀበሉ ስለሚገደዱ፤ የገዥዎቻቸው አገልጋዮች ናቸው ማለት ይቻላል። ከዚህ የተነሳ፤ ለገንዘብ ሊያድሩ የሚችሉ ግለሰቦች በየትኛውም ሀገር ያሉ ቢሆኑም፤ እንደሩስያ ያሉት ሀገሮች በኃላፊነት የሚያስቀምጧቸውን አበጥረው ተገዥ የሚሆኑትን የሚያወጡ ሲሆን፤ እንደ አሜሪካ ያሉት፤ ክፍትነታቸው ለብዙኀኑ ባደባባይ ያን የግል አመለካከታቸውን ለማወጅ አመቺ ነው።

እንግዲህ በመካከላቸው ባለው ልዩነትና ውድድር የተነሳ፤ አሜሪካና ሩስያ፤ በየትኛውም መስክ ቢሆን፤ ፉክክራቸው ቅድሚያ ይይዛል። ለዚህም፤ ሩስያ፤ በመንግሥት ደረጃ አሜሪካን ለማዳከምና የራሳቸውን ጥቅም ለማስቀደም፤ ሌት ተቀን ይሠራሉ። አሜሪካ ይሄን አታደርግም ማለት አይደለም። ነገር ግን፤ አሜሪካ የበላይነት አለኝ የሚል እብሪት ስላላት፤ “እኔ የምለው ሁልጊዜም ተቀባይነት አለው!” በሚል ጋቢ ተጎናፅፋ፤ “ዓለምን የምመራው እኔ ነኝ፤ ሩስያ ደካማ ናት!” በሚል፤ በሩስያ ላይ ዕቀባ መጣልና የመሳሰሉትን በቦታው አስቀምጣለች። በተወሰን ደረጃም አብረው የሚሰለፉላት ምአንግሥታት አሉዋት። በዚህ የፖለቲካ ጨዋታ መካከል ነው የሩስያን ጣልቃ ገብነት የምናየው።

ሩስያ፤ በአሜሪካ መንግሥት የሚደረገውን ውሳኔ ማወቅ ብቻ አይደለም፤ ከቻለች፤ በውሳኔ አሰጣጡ ላይ እጇን ማስገባት ትፈልጋለች። ማን የጠላቱን እንቅስቃሴ ማወቅ የማይፈልግ አለ? በየሀገሩስ ያሉት ኤምባሲዎች ዋናው ሥራቸው ምን ሆኖ ነው! ሩስያ ግን የሞትና የሽረት ጉዳይ አድርጋ ነው የያዘችው። አያስገርምም። ዓለም መተሳሰርና መተባበር ለእያንዳንዱ ሀገር የሥልጣኔ ግስጋሴና የቴክኖሎጂው እድገት ወሳኝ በሆነበት ወቅት፤ ከህዝቡ ነፃነት ይልቅ የራሳቸውን በሥልጣን መሰንበት የሚያስቀድሙ ሀገሮች፤ ተገደውም ሆነ ወደው ለብቻ መቀመጣቸው፤ አስጊ ነው። ሰሜን ኮሪያ፣ ኤርትራ፣ ሶሪያ፣ ይአትግሬዎቹ ገዥ ቡድን የነገሠባት ኢትዮጵያ፣ የዚህ ባለቤቶች ናቸው። እናም ያንን ሚዛን መድፊያ የግድ ማቀድ፤ ለሩስያ ግድ ሆኖባታል። ታዲያ የሩስያን መሯሯጥ የሚረዳ አካል ደግሞ፤ በአሜሪካ ውስጥ ይገኛል። ይሄም፤ በአሜሪካ ያሉ የራሳቸውን ጥቅም ከሀገራቸው ጥቅም አስበልጠው የሚገኙ ግለሰቦች ናቸው። እንደነዚህ ያሉ ግለሰቦች፤ ለገንዘብ ሲሉ፤ በሰላይነት፣ በተቀጣሪነት እናም መሳሪያ በመሆን ተገዝተው ለሩስያ የሚያገለግሉ ናቸው። ለግልሰብ ጥቅማቸው የሚንሰፈሰፉ ሰዎች በግል አይኖሩም። በጎናቸው መሰሎቻቸውን ይኮለኩላሉ። እናም የብርታታቸው ምሰሶዎች፤ ሌሎች እንደነሱ ያሉ የግል ጥቅም አሳዳጆች ናቸው።

ከግለሰብ ጥቅም አንጻር፤ ግለሰብ ዶናልድ ትራምፕ፤ ራሳቸውን ወዳድ፤ ማንንም ረጋግጠው ወደ ላይ ለመውጣት ቅንጣት የማይሰቀጥጣቸው ናቸው። እናም፤ ማንም በሚፈልጉት መንገድ ወደሚፈልጉት ቦታ ለመሄድ እንቅፋት የሚሆንባቸውን፤ ከሰይጣንም ጋር አብረው ለማጥቃት፤ ወደኋላ አይሉም። ይህ የሩስያ ጉጉትና የትራምፓ ራስ ወዳድነት፤ ባንድ ላይ ተጋጥመው መገኘታቸው ነው፤ ለዚህ አሁን ላለንበት የሩስያ ጣልቃ ገብነት መሠረቱ።

የሩስያ አሜሪካን የመቦርቦር ጥረት አዲስ አይደለም። እስከዛሬም ስታደርገው የነበረ ነው። የትራምፕም ጥቅሙን ማሳደድና የሀገሩን ጥቅም ወደ ትቢያ መጣል አዲስ አይደለም። የነበረ ነው። ምንም ታክስ አለመክፈሉ ብቻ ሳይሆን፤ አሁንም የታክስ መዝገቡን አላሳይም እንዳለ በእብሪት መቀመጡ፤ ምስክር ነው። በዚህ ስሌት፤ የቀድሞዋ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ኃላፊ የነበሩትን ሄለሪ ክሊተንን ለማቸነፍና ፕሬዘዳንት ለመሆን፤ ከሩስያ ጋር ለማበር ፈላጊ ሆኖ ቢገኝ፤ ሩስያም አደገኛ ይሆኑብኛል ያላቸውን የአሜሪካን የቀድሞ የውጭ ጉዳይ ኃላፊዎን ሄለሪ ክሊንተንን ለማስወገድና እንደ ፈረስ እጋልበዋለሁ ብለው የተመኙትን ዶናልድ ትራምፕን ለፕሬዘዳንትነት ለማብቃት፤ ሁለቱም ተጠቃሚዎች የሚሆኑበት አጋጣሚ ነበር። እናም ሌት ተቀን ሠሩበት። በሂደቱም ዶናልድ ትራምፕ ተመረጠ።

ውሎ አድሮ ግን፤ የአሜሪካ ልዩ የሆነ መንግሥታዊ አወቃቀር፣ አሰራርና በውስጡ የተሰገሰጉ ሀገር ወዳዶች፤ “ዝም ብለን አናይም!” በማለት፤ ውስጥ ውስጡን ሚስጢር በማውጣት፤ ይሄው እንዲጋለጥ አደረጉት።

ከዚህ የምናነበው፤ በታጋዩ ወገናችን ውስጥ የሚካሄደውን ክስተት ነው። በውጥረት ላይ ያለው የትግሬዎች ገዥ ቡድን፤ በውስጥና በውጪ ያለበትን ሕዝባዊ ተቃውሞ ለመከላከል፤ በሀገር ውስጥ፤ ፍጹም አረመኔያዊ በሆነ መንገድ፤ ትክክለኛ ያልሆኑ ሕጎችን በማውጣት፣ አላግባብ ሰዎችን አጋፎ በማሰር፣ ሕጉን አጣሞ ፍርድ በመሥጠት፤ የለ ርህራሄ ሕዝቡን እያሰቃየ ነው። በውጪ ያለውን ተቃውሞ ደግሞ፤ ከፍተኛ ወጪ በማፍሰስ፤ የትግል አንድነት እንዳይፈጠር፣ ሆድ አደሮችን ሰግሰጎ በማስገባት፤ ትግሉ ባለበት እንዲቆም አድርጎታል። ምንም እንኳን ከመቼውም የከፋ ሥርዓት በሀገራችን ቢሰፍንም፤ ምንም እንኳን ብዙኀኑ በዚህ በትግሬዎች ገዥ ቡድን ተጠቂ ቢሆንም፤ ምንም እንኳን ታጋዩ ብዙ ቢሆንም፤ አንድነት ከመቼውም በላይ ርቆ ሄዷል። የትግል አንድነት ቀርቶ፤ ተቀራርቦ የመነጋገር ዕድሉ እንዳይሆን ሆኗል። የትግሬዎቹ ገዥ ቡድን ሊኮራ ይገባዋል። ምንም እንኳን ሙሉ በሙሉ ይህ የተደረገው በትግሬዎቹ ገዥ ቡድን የገንዘብ ፍሰትና የግለሰቦች ሆዳምነት ብቻ ነው ባይባልም፤ በአንድነት የመታገሉን ሁኔታ ያደቀቀው፤ በአብላጫው፤ የዚሁ ተወጣሪ ቡድን ጭንቀትና የሆዳሞች ስግብግብነት መሆኑን መካድ አይቻልም። በርግጥ እኔ እበልጥ እኔ እበልጥ ፉክክሩና፤ እኔ ብቻ ነኝ ትክክለኛ ባይነቱ ሚና አለው። ሌላም ተጨማሪ፤ ለዚህ ጸሐፊ ያልታየው ሁኔታ ሊኖር ይችላል። ባጠቃላይ ከሩስያ ጣልቃ ገብነት የሚታየው ይህ ነው።

አንዱዓለም ተፈራ – የእስከመቼ አዘጋጅ

eske.meche@yahoo.com

አርብ፣ መጋቢት ፳፪ ቀን፣ ፳፲፱ ዓመተ ምህረት (03/31/2017)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Mes says

    March 31, 2017 02:21 pm at 2:21 pm

    አቶ አንዳለም ተፈራ በ CNN ፕሮፓጋንዳ አይምሮአቸው ዞሯል መሰለኝ ፣ ፑቲን ራሺያን ከዲክታይተሮች የነጭ አሽከሮች ጋር እንድ ማደወረጋቸው ፍፅም ስህተት ነው ፣ ምእራባውያን የቀድሞው ሶቪየት ተሸንፎ ፈረሰ ብለው እራሳቸውን እንዳሸናፊ ቆጠሩ: እውነታው ግን ሶቪየት ህብረት bankrupt ሆነ ታዲያ ምእራቡ የቀድሞውን የአለም ሰላም ስምምነቶች ከቀድሞ ሶቪየት ጋር የነበራቸውን መሻር ብቻ አይደለም በናቶ ጦር ሩሲያን መክበብ ጀመሩ ፣የማይፈልጉትን መንግሥታት አይ ሲስን በመጠቀም መንግስትን ግልበጣ ጀመሩ ፣ አለምን ከፍተኛ ወደ ኒኒኩለር ጦር አስጊነት ቀየሩት ፣ታዲያ ይህን በመቃወምና የአገርዋን ከበባ ለመቋቋም የምትወስደው ሩሲያ ከወያኔ ጋር ትመሳሰላለች ፣ አቶ አንዱአለም እዛው በአገራችን ፖለቲካ ቢቆዩ ይሻላል እንጂ ኢንተርናሽናል ትንሽ ተዘርባብቆባቸዋል ፣ ሩሲያ ናፖሊዮንን ያሸነፈች ሂትለርን ትምህርት የሰጠች ናት ፣ ሩሲያ ጦርነት መጀመር ሳይሆን ጦርነትን መጨረሽ ግን የተካነች ናተወና ፣ ጀግናን ህዝብና መሪዎችን ከኢትዮጵያ ሹምባሽ መሪዎች ጋር አንድ ማድረግ አለማወቅ ብቻ ሳይሆን አሳፋሪ አባባል ነው ።

    Reply
  2. የዜኑ ሰው says

    March 31, 2017 08:37 pm at 8:37 pm

    ምናልባትም አቶ አንዱአላም ተፈራ በምእራብያኑ ሚዲያ በሚሰሙት ፕሮፖጋንዳ ሳይሸወዱ አይቀሩም መሠለኝ …..እንጂማ ይሄንን እንቶ ፈንቶ የሆነ ፁሁፍ ባላቀረቡ ነበር፡፡
    የቀድሞዋን ሶቭዬት ህብረት ከታላቅነቷ አውርደው እና በታትነዋት አቅመ ቢስ ያደረጓትን እንደነ ሚካኤል ጎርባጆቭ እና ዬልሲን ያሉ የአሜሪካን ተላላኪና ባንዳ መሪዎችን ከወያኔ ጋር ማመሳሰል ሲገባ የተናቀችው ራሺያን ከወደቀችበት አንስቶ: ከአቅመ ቢስነት ወደ ሀያልነት ከፍ አድርጎ ወደ ቀድሞዎ ገናናነቷ የመለሳትን ጀግናና ሀገር ወዳድ መሪ የሆነውን ፑቲንንና መንግስታቸውን ከትግራዩ ወያኔ ጋር ማወዳደር ለተናጋሪው ይቅርና ለሠሚውም ይሰቀጥጣል፡፡ ይመስለኛል አቶ አንዱአለም አሁን ስላለው የራሺያ መንግስትም ሆነ ስለ ፑቲን የሚያውቁት አንዳችም ነገር የለም

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule