• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ከአሁን ወዲህ ተገቢውን የህዝብ ድምጽ ሳያገኙ እዚህ ወንበር ላይ መቀመጥ አይቻልም”

May 28, 2018 11:22 am by Editor Leave a Comment

የኦሮሚያ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ለማ መገርሳ የግንቦት 20 ክብረበዓልን አስመልክቶ ካደረጉት ንግግር በወፍ በረር ተመርጦ የተተረጎመ ሀሳብ፤

  • ዴሞክራሲ በወሬ ብቻ አይመጣም፤ የሚሰባበረውን መሰባበር የሚነቀለውን መንቀል ያስፈልጋል።
  • ባህላችንም ዴሞክራሲን እንዲሰፋ የሚያግዝ ሳይሆን በተቃራኒው እንዲቀጭጭ የሚያደረግ ስለሆነ እሱ ላይም መስራት አለብን።
  • እስረኛውን እንደወራጅ ወንዝ እየለቀቅን ያለነው እስርቤት ለመዝጋት እቅድ ስላለን ሳይሆን አዲስ የፖለቲካ አየር ለመፍጠር ስለምንፈልግ ነው።
  • በኦሮሚያ በአንድ አመት ውስጥ 40ሺ እስረኛ በላይ የለቀቅነው ግለሰብን ብቻ ነፃ ለማውጣት ስለምንፈልግ እንዲሁም ለመወደድ ወይም እንዲጨበጨብልን ስለፈለግን ሳይሆን የመጠላለፍ እና የመጠፋፋት ባህላችንን ለመቀየር ነው።
  • ሰዎችን ከእስርቤት ብቻ አይደለም ነጻ ያወጣነው . . . ተሰደው የዜግነት መብታቸውንም ካጡበት የስደት ኑሮ ነው . . . ከባዕድ ሀገር እስር ቤት ጭምርም ነው ።
  • ታሪክ እየቀየርን ነው . . . ሁሉንም የፖለቲካ ፓርቲ ከያሉበት ግቡና አብረን እንሥራ የምንለው የፖለቲካ ገበያ ለመክፈት ሳይሆን በእውነት እና በሀቅ የሀገሪቱን ታሪክ ለመቀየር ስለምንፈልግ ነው። በቦረና በኩል በስደት የወጡትን በቦሌ በኩል እንዲገቡ ያደረግነው ሞተው ሬሳቸው ተጭኖ ከሚመጣልን ይልቅ በህይወት መጥተው ለህዝባቸው እንዲሰሩ እና እንዲያገለግሉ ነው። የሀገሪቱ ዜጋ መሆናቸው እንዲረጋገጥላቸው ነው። እነዚህ አካላት ሀገር ውስጥ ሆነው በህዝባቸው መሀከል ሆነው ሲሰሩ ነው የሚያወሩትን ለውጥ በተግባር ሊያመጡ ሚችሉት።
  • ኦህዴድ “ኦፒዲኦ” ስለሆን ለዘመናት ይጠየፉን እና ይንቁን የነበሩትን እና ከእናንተ በላይ ነን የሚሉትንም ነፃ አውጥተን ለሀገራቸው አብቅተናቸዋል።
  • እኔ ምኞቴን ነግራችኋለሁ . . . እዚህ ወንበር ላይ ለመቆየት አይደለም ዕቅዴ፤ ለዚህ ህዝብ ነፃነት ማምጣት ከቻልን ድላችን ወደኋላ የማይመለስበት ደረጃ መድረሱን ካረጋገጥን ለመልቀቅ ደስተኞች ነን።
  • ከአሁን ወዲህ ተገቢውን የሕዝብ ድምጽ ሳያገኙ እዚህ ወንበር ላይ መቀመጥ አይቻልም።
  • ሶስት ሰዓት አንብቤ 30 ደቂቃ ድንቅ ንግግር ማድረግ ቀላል ነው . . .። መሥራት ነው የሚከብደው። ጥሮ ግሮ ትንሽም ሆን ትልቅ ውጤት ማምጣት ነው ከባዱ። ማውራትም ሺዎች አሳምረው ያወራሉ።
  • እኛ የተሰደደውን ብቻ ነፃ ማውጣት ሳይሆን ሀገሪቱንም ከመበተን አድነናታል፤ . . . እኛ ወደ ስልጣን ስንመጣ ብዙዎቹ አሳንሰው እንዳዩን ሳይሆን ከኦሮሞ ህዝብ የወጣን ቢሆንም ለመላው ኢትዮጵያ የምንተርፍ መሆናችንን አረጋግጠናል። በዳቦ ከሆነ ወደ ሥልጣን በመምጣታችን አንድ ዳቦ እንኳን ለኦሮሞ የጨመርነው የለም፣ ሀገራችን እንድትከበር ግን ማድረግ ችለናል። ክብር ደግሞ ከዳቦ ይበጣል። በቀጣይ ዳቦውን በላባችን ሠርተን እናገኘዋለን።
  • አሁን ተንሰንሰፍስፈው የሚያናግሩን እና በአጀብ አቀባበል የሚያደርጉልን የዓለም ሀገራት ከወራት በፊት በአማላጅ አንኳን ለማናገርም ተጠይፈውን እና እንቢ ብለውን ነበር፤ . . . በአንድነታችን ኦሮሞን ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያንም ነው ያስከበርነው፤ በቀጣይም አፍሪካንም ጭምር ለማስከበር ነው የምንሰራው። አሁንም ህዝባችን ብዙ መከራ አለበት። ዋናው ሰንሰለት ግን ከላያችን ላይ መበጣጠስ ችለናል።
  • ዛሬም በሀሳብ ልዩነትን ተቻችለን አብረን ለህዝባችን መስራት የማንችል እና ልክ እንደ ትናንቱ በመሳሪያ የምንጫረስ ከሆን ምንም ያልተማርን መሀይሞች ነን ማለት ነው።
  • ወንበርን ሀብትን ለማፍሪያነት ፈልገነው የተቀመጥንበት ሲሆን ብቻ ነው ለመልቀቅ የምናንገራግረው . . . ለመቆየትም ስንል ሌላውን የምናጠፋው . . . ፍላጎታችን የሕዝባችንን ኑሮ ለመቀየር ከሆነ ግን ወንበር ላይ ውሎ ለማደር የምንጫረስበት ምክንያት አይኖርም።
  • በፌስቡክ “እከሌን ያስፈታነው እኛ ነን” ብለው የሚፎክሩ አሉ። ይፎክሩ ለህዝብ እስከጠቀመ ድረስ ይሁን ክሬዲቱን ለመውሰድ የሚሰጠው ሰርተፍኬቱ አያልቅም . . . ግን የዛሬ ሶስት ዓመት ለምን አላሰፈቱም? የዛሬ አራት አመትስ . . .? ዛሬም ሁሉ ነገር አልተፈታም፤. . . ብዙ ችግሮቻችን ገና በሂደት ላይ ናቸው። ግን በመደማመጥ መስራት አለብን . . . ነገም ተነስተን በገጀራ ምንጨፋጨፍ ከሆነ እና በዱላ ምንደባደብ ከሆነ ብዙም ሳይቆይ በቅርብ ህዝባችንን መልሰን ወደ ባርነት እንመልሰዋለን ማለት ነው። በንግግር የምንስማማበት የመቻቻልና የአንድነት ዘመን ይሁን።

(ትርጉም፡ በዘሪሁን ገመቹ ዋቤ)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: lemma megerssa, Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule