• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ያልተመጣጠነ ግጥሚያ

October 10, 2012 03:01 am by Editor 2 Comments

ጠቅላይ ሚኒስትር የነበሩት ታመዋልም ሞተዋልም በሚማልበት ሰአት  ሎጋው ሽቦ ተዘፈነ …

የርዕሰ ብሄር መለስ ዜናዊ ሞት ይፋ በሆነበት ሰአት ደግሞ ብር አንባ ሰበርልዎ ተብሎ ሲዘፈን በሰፊው ተሰማ…

ኃይለማርያም ደስ አለኝ ቦታው ተፈቅዶላቸው ሀገር ወከሉ ተብሎ ሲታወጅ አስገራሚው ዘፈን አላቆመም የቤተ  ዘመዱ ይታያል ጉዱ ይባል ተገባ…

*****************************************************************************************************

አጋጣሚ የፈጠረውን ፖለቲካዊ ግርግር በጥበብ ተጠቅሞ በፖለቲካው እንቅስቃሴ ውስጥ የመደራደሪያ አቅም በማበጀት ወይም አቅም በመገንባት አማራጭ ሀይል መሆንን ከማሳየት ፋንታ በቀረርቶና በሽለላ የጨዋታውን ህግ ለመቀየር መመኘት የምኞት ሁሉ መናኛ ቢባል ያስነውር ይሆን?

በትግል አጋሮቻቸው ከአንድ ነፍስ በላይ እንዳላቸው የተስተናገዱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለመጨረሻ ጊዜ የስጋቸውን ነፍስ ተሰናብተው በአጥንታቸው ላይ በቀረው ነፍስ ተንገዳግደው ደቡብ አሜሪካና ሜክሲኮ ብቅ ብለው ነበረ።

ታዲያ ከወዳጃቸው ከቻይናው መሪ ጋር ተጨባብጠው እስከ ወዲያኛው በተሰነባበቱበት ወቅት አጥንታቸው ከስጋቸው መለያየቱን ያላስተዋለ የኮምፒውተር ቆዛሚ አለ ብየ አላምንም።

በዚያን ወቅት በውጭ የሚገኙት የፖለቲካ ጥበብ ያልዞረባቸው ተቃዋሚዎች መንግስት የተገለበጠ መስሏቸው ተዋግቶ ነፃ መሬት እንደያዘ የደፈጣ ተዋጊ ዘራፍ በማለት የተለመደው ምስቅልቅል የፖለቲካ አመራር ከየአቅጣጫው ይጎርፍ ጀመረ።

ሰውየውም ያላቸውን ነፍስ በሙሉ አሟጠው ካመለጡም በኋላ ይህንን ማመን የከበዳቸው ጓዶቻቸው የጠቅላይ ሚኒስትሩን ሬሳ አልሞትክም ብለው ሲክዱ፥ ህዝቡን ደግሞ መሪያችን አልሞቱም በማለት ገገሙ።

ይህም ሆኖ መሪያችው የሚሞት ስጋ ለባሽ መሆናቸውን መቀበል ያቃታቸው እስከሚመስል ድረስ ተደናግጠው በነበረበት ወቅት የመሪያቸውን ሞት በመካድ የመረጋጊያ ግዜ ገዝተው የተቃዋሚዎቻቸውን እንቅስቃሴ በትጋት መከታተል ጀመሩ።

ፖለቲካ የፉክክር ጨዋታ መሆኑን እንጂ የመጫወቱ ተሰጥኦ እምብዛም ያልተካኑት ከሀገር ውጭ የሚገኙ ተቃዋሚዎች ታዲያ የተሸበረው መንግስት ጊዜን ለመግዛት በመረጠው ሜዳ ሲያሰልፋቸው በተርታ ተኰልኩለው የመለስ ዜናዊን ዜና እርፍት ለነበረከት ስምኦን ለማሳመን ያላሉትና ያልሰማነው ትንታኔ የለም እንግዲህ ይህንን ስንል ፉከራውንና ሽለላውን ትተነው ነው።

በመጨርሻም በረከት፤ ሳሞራና፤ ብርሀኔ ገብረክርስቶስ፤ የሞት ትርጉሙ ገብቷቸው የመሪያቸውን ሞት ይፋ አደረጉ።

በዚህን ጊዜ ደግሞ ከሜዳ ውጭ ሆኖ የሚጫወተው ተቃዋሚ ቡድን በጎዶሎ ተጫዋች ከሚጫወተው የገዢው ፓርቲ ላይ ግብ ለማግባት የጫዋታ ስልት ቀይሮ ዋና ሜዳ ውስጥ ለመግባት መሞከሩን ዘንግቶ ድል በድል እያሉ በመዘመር ለመለስ ከሚያለቅሰው ወይም ከሚያስለቅሰው ቲፎዞ ጋር ግብግብ ገጥመው ጨዋታውን በፎርፌ አስረከቡ።

በፖለቲካ ጨዋታ እንደሚታወቀው ዳኛ የሚሆነው ምንግዜም አሸናፊው ነው።

በመሆኑም በተቆጣጠሩት ሜዳና ባላቸው የዳኝነት ስልጣን ተጋጣሚውን ቡድን ከለቀስተኛው ጋር አተካራ ተያይዞ ከሜዳው መራቁን ካረጋገጡ በኋላ የጎደለባቸውን ተጫዋች (ጠቅላይ ሚኒስትሩን) ለመተካት እርስ በርስ ተሳልጠው፥ ተዋቅጠው፥ ተዳጉሰው፥ ተሰልቀው፥ በመጨረሻም ለኃይለማርያም ደሳልኝ የሟቹን የማእረግ ስምና መቀመጫ ሸልመው አሁንም ጨዋታውን በበላይነት መምራት ይዘዋል።

ታዲያ እንዳያችሁት በፎርፌ የተዘረረው የጨዋታው ህግም ይሁን ጥበብ ያልገባው የውጪው ተቃዋሚ ቡድን በሚያስገርም አይነት የምኞት ፈረስ ላይ ቂጥጥ ብሎ በጎደለው ተጫዋች የተተካውን ኃይለማርያም ደሳለኝን በራሱ ቡድን ላይ ጎል እንዲያገባ የቤተዘመዱ ይታያል ጉዱ እያሉ በመዝፈን የምኞት ሁሉ መናኛ የሆነውን ምኞት ተመኙ።

ባልተመጣጠነ ጉልበት፥ ውል በሌለው አመራር፥ ጥበብ ባልዞረበት ስሌት፥ በተለይ ደግሞ፥ በተመሰቀቃቀሉ ድርጅቶች፥ የሚመራው ከሀገር ውጭ የሚደረገው ትግል፤ ጉልበቱን ያፈረጠመን መንግስትና፥ ሁኔታዎችን የመጠቀም የረቀቀ ዘዴ የተለማመደን ግዙፍ ድርጅት፥ እንዲሁም ስልጣን ማለት አስፈላጊ የሆነ የሰይጣን ስራ (power is the necessary evil) መሆኑን ተረደቶ በጭካኔ ለሚወሰድ እርምጃ ቀላል ምክንያት ሰጥቶ ከሚያስፈፅም ቡድን ጋር ሲጋጠም የራስ አቅምንናና የባላንጣን ጉልበት ማወቅ አስፈላጊ ብቻ ሳይሆን ወሳኝም ነው።

መሪውና ተመሪው ተደባልቆ፥ ሽለላና ፉከራ በመሰቃቀሉት፥ በእውቀት ሳይሆን በስሜት በሚንቀሳቀስ በብዙ መሪዎች የሚመራው እንቅስቃሴ የመሸነፍን ልምድ ለሀያ አመት ደግሞ ደጋግሞ ተጎናፅፏል፤ ይህንን ለመቀየር ይህችኑ እውነት ከልብ ማመን የመጀመሪያው እርምጃ ይሆናል።

በተለይ ካገር ውጭ ሆኖ አብሮ ከማይኖረው ህዝብ ላይ የመሪነትን መንፈስ ማዳበር በተግባር ሊተረጎም የማይችል ግብ አልባ ጨዋታ ነው።

የሰማኒያ ሚሊዮን ህዝብ ጉዳይ የኔ ነው ብሎ እራሱን ወክሎ የሚንቀሳቀስ ቡድን መደገፍ እንዳለበት ሁሉ ሀላፊነትን በሚገባ ካልተወጣና መወጣት ካቃተው እንዲስተካከል መጠረብ ይገባዋል።

ስለዚህም በውጭ የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የተመሰቃቀለውን የተቃዋሚ ድምፅ መግራትም ሆነ ማጎለበት ካልቻሉ መገሰፅና መወረፍ አግባብ ነው።

ብዕሬ በተቃዋሚዎች ላይ እንዲህ መሳለቁ ገዢዎቹን ደግፌ ወይንም ፈርቼ አይደለም።

ይህንን ብሶቴን በማስተዋል ያነበበና እንደኔ በውጭ በሚገኘው ተቃዋሚው ተስፋ የቆረጠ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ይገነዘባል ብዬ አምናለሁ።

የመብት ረጋጮቹና የጉልበት አምላኪዎቹ ገዥዎቻችንን ፅናትንና ያላሰለሰን ዘዴ ባደንቅም ለሰማኒያ ሚልዮን ህዝብ ተጠሪ ለመሆን የሚያበቃ የሞራልም ሆነ የሀገር ፍቅር ስሜት የሌላቸው መሆናቸውን መናገር አስፈላጊ ይመስለኛል።

በፖለቲከኞች መሳለቅ መቀለድ ከዛም ሲያልፍ መፀየፍ ግፍና አድሎ ያንገበገብው ብዕር መሄጃ ሲያጣ የሚያነባው እንባ በመሆኑ እንደተለመደው በአንድ አይነት አስተሳሰብ ዙሪያ ብቻ ያልተፃፈን አስተያየት ከተቆጣጠራችሁት መድረክ የምታገሉት ከሆነ ከገዢዎቻችን መንፈስ ያልተለያችሁ ስለሆነ አንድ አርጌያችሁ እንድታገላችሁ እገደዳለሁ ማለት ነው።

በመጨረሻም የፖለቲካ መሪዎችና ፓርቲዎች የመምራት ሀላፊነት ስላለባችሁ በድረገፅ አርበኞች፤ በሬድዮ ፕሮግራም ፊት አውራሪዎች፤ በአጠቃላይ በብዙሃን መገናኛ ባለሙያዎች መመራታችሁን አቁሙና እንደ ፖለቲካ መሪ አላማችሁን ፕሮግራማችሁን ፍልስፍናችሁን አጥምቁንና ምሩን።

የብዙሀን መገናኛ ባለሙያዎች ወይም የድረገፅ፥ ሬድዮንና፥ ፓልቶክ፥ ጋሻ ጃግሬዎች በምታደርጉት ተሳትፎ መብታችሁን እየተለማመዳችሁ መሆኑን ጥያቄ ውስጥ ባላስገባውም ቢይንስ ብያንስ ከሙያ አንፃር በመመልከት ለዲሞክራሲያዊና ሰብዓዊ መብት የሚደርገው ትግል እንዳይጓተት ለፖለቲካ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ እንቅፋት አትሁኑ። ማለትም በሙያችሁ እንደጋዜጠኛ አገልግሉን፤ አለበለዚያም ለአንዱ ፓርቲ አድራችሁ እንደ መሪ ምሩን፤ ተመሰቃቅላችሁ አትመሰቃቅሉን።

እስካሁን ግን ሳታውቁት ጠላታችሁን እያገለገላችሁ ነው።
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይታደጋታል!!

ከዘመድ አገኘሁ

ጸሐፊዉን ለማግኘት ከፈለጉ at: zamedaganiahu@gmail.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. yeselechew says

    October 14, 2012 09:24 pm at 9:24 pm

    Hi Zemed,

    I’m, like you, one of those Ethiopians who’re fed up of the so called diaspora limited opposition parties. እንዳልከው የፖለቲካ ጨዋታው ገና የገባቸው አይመስለኝም:: የአዲሱን ጠ/ሚኒስትር መልካም አመለካከት ብቻ የተማመኑ ነው የሚመስሉት::

    Reply
  2. daniel says

    October 29, 2012 11:12 pm at 11:12 pm

    that is a wonderful idea if understand every body other wise “gunch alfa were” yehe nwe yekurte kene lije lehulume negzabhier matewalen yadelen………….

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule