• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሜቴኩ ክንፈ እና የኢንሳው ተክለብርሃን በቁጥጥር ሥር ውለዋል

November 13, 2018 01:42 am by Editor 5 Comments

የቀድሞው የሜቴክ ዋና ኃላፊ የነበረው ክንፈ ዳኜው እና የኢንሳ (የህወሃት የኢንፎርሜሽን ስለላ) ኃላፊ የነበረው ተክለብርሃን ወልደአረጋይ በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን የአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት (አብመድ) በፌስቡክ ገጹ ምንጮቹን ጠቅሶ አስታውቋል።

ዋልታ እንደዘገበው ደግሞ “ሱዳን ድንበር አካባቢ የተያዙት ሁለቱ ተጠርጣሪ ግለሰቦች ዛሬ (ማክሰኞ) ከሰአት ወደ አዲስ አበባ እንደሚገቡ የደረሰን መረጃ ያመለክታል”።

አብመድ ግለሰቦቹን በስም ባይጠቅስም በዜናው ላይ ግን “የብረታ ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) እና የኢንሳ የቀድሞ ኃላፊዎች በቁጥጥር ሥር ውለዋል” በማለት ነበር የዘገበው።

ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ትላንት በሰጠው መግለጫ ሜቴክ ያለምንም ጨረታ የ37 ቢሊዮን ብር ግዢ የፈጸመ መሆኑን የተናገረ ሲሆን በሽብር፣ በሰብዓዊ መብቶች ጥሰት እና በሙስና ወንጀሎች የተጠረጠሩ 63 ግለሰቦች እና ኃላፊዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ማስታወቁ ይታወሳል።

ከህወሓት የሚያፈተልኩ መረጃዎች ይፋ በማውጣት በአብዛኛው የሚታወቀው ስዩም ተሾመ ደግሞ በፌስቡክ ገጹ “ጄ/ል ክንፈ ዳኘው እና ጄ/ል ተክለብርሃን ወልደአረጋይ ወደ ሱዳን ለማምለጥ በመሸሽ ላይ እያሉ ማታ ከምሽቱ 5:00 ሰዓት ላይ በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ለማረጋገጥ ተችሏል” በማለት ጽፏል።

ክንፈ እና ተክለብርሃን በትላንትናው ቀን ወልቃይት ገብተው እንደነበር በማኅበራዊ ድረገጾች ተዘግቦ የነበረ ሲሆን ከዚሁ ጋር ተያይዞ ተሳፍረውበታል የተባለውን መኪና ፎቶ ጭምር አብሮ ተለቅቆ ነበር።

ጠ/ሚ/ር ዐቢይ አሕመድ ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ ሁለቱ የህወሓት ቀኝ እጆች ከቀድሞው ኃላፊነታቸው በመነሳት ወዲያውኑ ወደ መቀሌ ከትመው እንደነበር ይታወሳል። እዚያም ሆነው የተለያዩ ቃለምልልሶችንና መረጃዎችን በመልቀቅ የለውጡን አካሄድ ለማጨናገፍ በርትተው ሲሠሩ እንደነበር ይታወቃል። አንዳንዶችም በተለያዩ የኢትዮጵያ ቦታዎች የሚነሱ ግጭቶችን በማስተባበር፣ በገንዘብ በመርዳት፣ መሣሪያ በማቀበል፣ ወዘተ ሁለቱ ሰዎች ቁልፍ ሚና ነበራቸው በማለት ይናገራሉ።

በቀጣይ ሌሎች የህወሓት የቀድሞ ሹማምንት ለፍርድ የሚቀርቡበት ሁኔታ እንደሚኖር ጎልጉል ከተለያዩ ምንጮቹ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

እንደሌሎቹ ከዕውቀት የጸዱ የህወሓት ወንበዴዎች፤ ያለ ዓቅማቸው የጄኔራልነት ማዕረግ የተሸከሙት ሁለቱ ግለሰቦች በበርካታ ወንጀሎች የሚጠየቁ ሲሆን ተክለብርሃን ጄኔራልነቱ አልበቃ ብሎት ከዲግሪ ወፍጮ ቤት እንደ ማንኛውም የህወሓት ወንበዴ የዶክትሬት ዲግሪ መግዛቱ ይታወቃል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

ከዚህ ጋር በተያያዘ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ እስካሁን በቁጥጥር ስር የዋሉ ግለሰቦችን ዝርዝር ይፋ ማድረጉን ፋና ዘግቧል።

በዚህም መሰረት በሰብዓዊ መብት ጥሰት ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት፦

  1. አቶ ጉሃ አጽበሃ ግደይ – የአዲስ አበባ የደህንነት ኃላፊ
  2. አቶ አማኑኤል ኪሮስ መድህን – የሃገር ውስጥ ደህንነት ጥበቃ ዋና መምሪያ ዳይሬክተር
  3. አቶ ደርበው ደመላሽ – የውስጥ ደህንነት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩና የኢኮኖሚ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ
  4. አቶ ተስፋዬ ገብረጻዲቅ – የውስጥ ደህንነት ጥናትና የወንጀል ምርመራ መምሪያ ኃላፊ
  5. አቶ ቢኒያም ማሙሸት – በውስጥ ደህንነት ጥበቃ ዋና መምሪያ የኦፕሬሽን ጉዳይ መምሪያ ኃላፊ (በዋናነት የግንቦት 7 ጉዳይ ክትትል)
  6. አቶ ተሾመ ሀይሌ – የአማራ ክልል የደህንነት ኃላፊ የነበሩና የጥበቃ ዋና መምሪያ ዳይሬክተር
  7. አቶ አዲሱ በዳሳ – በሃገር ውስጥ ደህንነት የኦሮሚያ ክልል ደህንነት ኃላፊ
  8. አቶ ዮሃንስ ወይም ገብረእግዚአብሄር ውበት – የውጭ መረጃ
  9. አቶ ነጋ ካሴ – በጸረ ሽብር መምሪያ የኦነግ ክትትል ኃላፊ
  10. አቶ ተመስገን በርሄ – በጸረ ሽብር መምሪያ የኦነግና ኦብነግ ክፍል ዋና ኃላፊ
  11. አቶ ሸዊት በላይ – በሃገር ውስጥ ደህንነት ኦፕሬሽን መምሪያ የግንቦት 7 ክትትል ምክትል መምሪያ ኃላፊ
  12. አቶ አሸናፊ ተስፋሁን – በሃገር ውስጥ ደህንነት የአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ደህንነት አስተባባሪ
  13. አቶ ደርሶ አያና – በውጭ መረጃ የአማራ ክልል ክትትል
  14. አቶ ሰይፉ በላይ – በውስጥ ደህንነት የደቡብ ክልል ክትትል ኦፊሰር
  15. አቶ ኢዮብ ተወልደ – በውስጥ ደህንነት የደቡብ ክልል ደህንነት ኃላፊ
  16. አቶ አህመድ ገዳ – በውስጥ ደህንነት የኦሮሚያ ክልል ክትትል ምክትል ኃላፊ
  17. ምክትል ኮማንደር አለማየሁ ሀይሉ ባባታ – ቀድሞ የፌደራል ፖሊስ የሽብር ወንጀል ምርመራ ምክትል ዳይሬክተር የነበረና ዋና ዳይሬክተር ሆኖ ያገለገለ
  18. ምክትል ኢንስፔክተር የሱፍ ሀሰን – የሽብር ወንጀል መርማሪ
  19. ዋና ሳጅን እቴነሽ አራፋይኔ – የሽብር ወንጀል መርማሪ
  20. ኢንስፔክተር ፈይሳ ደሜ – የሽብር ወንጀል መርማሪ
  21. ምክትል ኢንስፔክተር ምንላርግልህ ጥላሁን – የሽብር ወንጀል መርማሪ
  22. ዋና ሳጅን ርዕሶም ክህሽን – የሽብር ወንጀል መርማሪ
  23. ኦፊሰር ገብረማሪያም ወልዳይ
  24. ኦፊሰር አስገለ ወልደጊዮርጊስ
  25. ዋና ሱፐር ኢንቴንደንት አሰፋ ኪዳኔ
  26. ዋና ሱፐር ኢንቴንደንት ገብረ እግዚአብሔር ገብረሐዋርያት – የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የጥበቃና ደህንነት ኃላፊ
  27. ዋና ሱፐር ኢንቴንደንት ተክላይ ኃይሉ – የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ሰራተኛ
  28. ዋና ሱፐር ኢንቴንደንት አቡ ግርማ – የሸዋ ሮቢት ማረሚያ ቤት ኃላፊ የነበረና በዝዋይ ማረሚያ ቤት ኃላፊ ሆኖ ሲያገለግል የነበረ
  29. ዋና ሱፐር ኢንቴንደንት አዳነ ሐጎስ – የቃሊቲ ማረሚያ ቤት ሰራተኛ
  30. ዋና ሱፐር ኢንቴንደንት ተስፋሚካኤል አስጋለ – በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ከፍተኛ የደህንነት ባለሙያ
  31. ዋና ሱፐር ኢንቴንደንት ገብራት መኮንን – የዝዋይ ማረሚያ ቤት የጥበቃና ደህንነት ኃላፊ የነበረና የሸዋ ሮቢት ማረሚያ ቤት ጥበቃና ደህንነት ኃላፊ ሆኖ ሲያገለግል የነበረ
  32. ረዳት ኢንስፔክተር አለማየሁ ኃይሉ ወልዴ – በአዲስ አበባ ፖሊስ የወንጀል መርማሪ
  33. ረዳት ኢንስፔክተር መንግስቱ ታደሰ አየለ – በአዲስ አበባ ፖሊስ የወንጀል መርማሪ
  34. አዳነች ወይም ሃዊ ተሰማ ቶላ
  35. ጌታሁን አሰፋ ቶላ
  36. ሙሉ ፍሰሃ

(ባሃሩ ይድነቃቸው)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Uncategorized Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Mulugeta Andargie says

    November 13, 2018 09:53 pm at 9:53 pm

    ሰዎች!! ሁሉም የስራውን ያግኝ!! ኣትማት ይህቺን ጎልጉል!! በግድ! በግድ! ወደየክልላችሁ ትሄዳላችሁ!

    Reply
  2. Ezira says

    November 13, 2018 11:32 pm at 11:32 pm

    ሠላም! ሠላም! ጎልጉሎች እንኳን ደስ አላችሁ
    እልልልልልልልልልልልልልል የሌቦች ቁንጮ ክንፈ ዳኜ ተቀፍደዶ ዘብጥያ ወረደ ፡፡ አብያችን ታሪክ ሠራ ። ደብረ ሰይጣንም ስግደት ላይ ነው አሉ— በደደቢት ቤተ ሰይጣን ቤት። Oh My God! and God Bless ethiopia

    Reply
  3. stand up for your right says

    November 15, 2018 09:53 pm at 9:53 pm

    the chickens came home to roast

    Reply
  4. Amanuel ze Ambo says

    November 17, 2018 07:08 pm at 7:08 pm

    ጎልጉልዬ ተክለብርሃን እንዳልታሰረ ስታውቂ ዜናውን ለምን አላስተካከልሽም? ተሳስተው ያሳሳቱሽ ቢሆንም ይሄን ስህተት አስተካክለሽ ከእንግዲህ ግን ከጠራው ምንጭ ቅጂ!!!

    Reply
  5. Challa says

    November 18, 2018 07:14 pm at 7:14 pm

    ስለ ሽመልስ ክንዴ ሌብነት ብትዘግቡ ከክንፈ ጋር ስለ ስራው ዝርፊያ ዓብይም ያውቀዋል

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule