• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ከዲያስፖራው ጋር የሚደረገው ውይይት ትርጉም እና ፋይዳ ይኖረው ዘንድ በእውነተኛ የለውጥ እርምጃዎች የታጀበ ይሁን!!

June 1, 2018 03:53 am by Editor Leave a Comment

ጠቅላይ ሚኒስተር ዶ/ር አብይ አህመድ በመጭው ነሀሴ ወር 2010 ዓ.ም. ወደ አሜሪካን አገር እንደሚመጡ እና ከዲያስፖራው ማህበረሰብ ጋር የመወያዬት እቅድ እንዳላቸው በስፋት እየተነገረ ይገኛል። በአገር ውስጥም ይሁን በውጭ አገር ያሉ ኢትዮጵያዊያንን ማወያዬት የሚደገፍ ሀሳብ ቢሆንም፣ የሚደረጉት ውይይቶች የአገራችንን ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች መሰረታዊ በሆነ መልኩ ለመፍታት እገዛ የሚያደርጉ መድረኮች ሊሆኑ ይገባል። አገራችን ኢትዮጵያ ስር የሰደዱ፣ ዘመን የጠገቡ እና ዘርፈ ብዙ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ችግሮች ያሉባት አገር ነች። እነዚህ ችግሮች ደረጃ በደረጃ መፍትሄ ያገኙ ዘንድ አገራችን በትክክለኛው የለውጥ ጎዳና ላይ መጓዝ ይኖርባታል። በመሆኑም፣ ከዲያስፖራው ጋር የሚደረግ ውይይት ከዘላቂ መፍትሄ አኳያ የሚቃኝ እንጂ የአጭር ጊዜ ግብ ለማሳካት የሚደረግ የህዝብ ግንኙነት ሥራ ሊሆኑ አይገባም።

ዲያስፖራው ላለፉት ሀያ ሰባት አመታት በአገሩ ጉዳይ ድምፁን ከፍ አድርጎ ሲያሰማ የኖረ ማህበረሰብ ነው። አገሩ የነጻነት ምድር እንድትሆን፣ የህዝቧ አንድነት እንዲጠበቅ፣ እኩልነት እንዲረጋገጥ፣ ፍትህ እንዲሰፍን እና ሰብአዊ መብቶች እንዲከበሩ ዲያስፖራው ያለመታከት የሚቻለውን ሁሉ ሲያደርግ ቆይቷል፤ ወደፊትም እነዚህ እሴቶች በአገራችን እውን ይሆኑ ዘንድ የድርሻውን ሀላፊነት መወጣቱን ይቀጥላል። በጥቅሉ፣ የዲያስፖራው ጥረት በኢትዮጵያ ውስጥ መሰረታዊ የስርአት ለውጥ እንዲመጣ እና አገራችን በተሻለ የኢኮኖሚ እና የፖለቲካ ጎዳና ላይ እንድትጓዝ ማገዝ ነው። ስለሆነም፣ የዶ/ር አብይ አህመድ አስተዳደር ከዲያስፖራው ጋር ለማድረግ ያሰበው ውይይት አገራችንን ወደ ትክክለኛው አቅጣጫ ለመውሰድ የሚደረገው ጥረት አካል መሆን ይኖርበታል።

ዶ/ር አብይ አህመድ የህዝባዊ እምቢተኝነት ግፊት ወደ መሪነት ያመጣቸው እና የለውጥ አቀንቃኝነት ዝንባሌ ያላቸው በመሆኑ በህዝቡ ዘንድ ከፍ ያለ ተስፋ ተጥሎባቸዋል። የጠቅላይ ሚኒስተር ሃላፊነትን ከተረከቡም በኋላ በጎ የሚባሉ በርካታ ሀሳቦችን ሰንዝረዋል። በተለይም፣ ኢትዮጵያዊነትን አስመልክተው ያራመዱት አቋም እና ያደረጉት ንግግር የብዙዎችን ቀልብ ስቧል። ይሁን እና፣ አገራችንን ወደተሻለ የለውጥ ጎዳና ከመውሰድ አኳያ ዶ/ር አብይ ምን ሀሳብ እንዳላቸው እና ምን ተጨባጭ እርምጃ መውሰድ እንደሚፈልጉ ግልፅ አይደለም። ኢትዮጵያን ወደ ዲሞክራሲያዊ ስርአት ለማሸጋገር ፍላጎት እና ቁርጠኝነት እንዳላቸው በግልፅ አይታወቅም። ይህ መሰረታዊ ቁምነገር ግልፅ ባልሆነበት ሁኔታ ከዲያስፖራው ጋር የሚደረገው ውይይት የረባ ትርጉም እና ዘላቂ ፋይዳ ይኖረዋል ብሎ ማሰብ አይቻልም። ከዲያስፖራው ጋር ሊደረግ የታቀደው ውይይት ዘለቄታዊ ጠቀሜታ እንዲኖረው ከተፈለገ፣ አገራችን ወደተሻለ የስርአት ለውጥ ጉዞ መጀመሯን የሚያመለክቱ ተጨባጭ እርምጃዎች በዶ/ር አብይ ሊወሰዱ ይገባል። ዶ/ር አብይ ከታች የተዘረዘሩትን ተጨባጭ እርምጃዎች አጠር ባለ ጊዜ ውስጥ በመውሰድ ለስርአት ለውጥ ያላቸውን ፍላጉት እና ቁርጠኝነት በግልጽ ማሳዬት ይጠበቅባቸዋል።

  1. ሁሉም የፖለቲካ እስረኞች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ ማድረግ፣
  2. ህዝቡን ለማሸበር ከህግ አግባብ ውጭ የጸደቀውን እና አገሪቱን በወታደራዊ አገዛዝ ስር ያደረገውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ዛሬ ነገ ሳይባል እንዲነሳ ማድረግ፣
  3. ዜጎችን ከቀያቸው የማፈናቀል ኢሰብአዊ ወንጀል በአስቸኳይ እንዲቆም ማድረግ፣
  4. የህዝቡን ፖለቲካዊ ተሳትፎ ለመገደብ፣ የመጻፍ እና የመናገር መብትን ለማፈን እና በሰብአዊ መብት ማስከበር ዙሪያ የሚደረጉ ጥረቶችን ለማሽመድመድ የወጡ አፋኝ የፀረ-ሽብር ህግ፣ የሚዲያ አዋጅ እና እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ድንጋጌዎች እንዲሻሩ ማድረግ፣
  5. በፖለቲካ ድርጅቶች፣ በሚዲያ ተቋማት እና ግለሰቦች ላይ የተጣለውን የአሸባሪነት ፍረጃ ማንሳት፣
  6. ሁሉም የፖለቲካ ድርጅቶች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በአገራቸው የለውጥ ሂደት ውስጥ ተሳታፊ የሚሆኑበትን መደላድል መፍጠር።

እነዚህ የለውጥ ፍላጎትን እና ቁርጠኝነትን የሚያንጸባርቁ ተጨባጭ እርምጃዎች እየተወሰዱ ከዲያስፖራው ጋር የሚደረግ ውይይት ጤናማ እና ትርጉም ያለው ይሆናል። ከዚህ በተጨማሪ፣ የሚከተሉትን ሁኔታዎች በማመቻቸት ከዲያስፖራው ጋር የሚደረገው ውይይት የበለጠ ፍሬያማ ማድረግ ይቻላል ብለን እናምናለን።

  1. ከህዝብ ጋር ከሚደረገው ውይይት በተጨማሪ መሰረታቸውን በውጭ ካደረጉ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ የሲቪክ ተቋማት፣ ታዋቂ ግለሰቦች እና አክቲቪስቶች ጋር ውይይት ማድረግ፣
  2. ውይይቶቹ በውጭ ላሉ ሁሉም ሚዲያዎች ክፍት እንዲሆኑ ማድረግ እና ዶ/ር አብይ እራሳቸው ከሚዲያዎቹ ጋር በመገናኘት ከጋዜጠኞች የሚነሱላቸውን ጥያቄዎች እንዲመልሱ ሁኔታውን ማመቻቸት።

ከላይ የተዘረዘሩት እርምጃዎች እየተወሰዱ እና መድረኩ ሁሉንም አሳታፊ እና ለሚዲያዎች ክፍት እንዲሆን ከተደረገ፣ ከዲያስፖራው ጋር የሚደረገው ውይይት የአገራችንን የለውጥ ሂደት ከማገዝ አኳያ ፋይዳ ይኖረዋል ብለን እናምናለን። እነዚህ የቅድሚያ ስራዎች ከተከናወኑ ለአገራችን እና ለህዝባችን የሚጠቅሙ በጎ ጅማሬዎች ሊሆኑ እንደሚችሉ እየገለጽን፣ ሁላችንም በሂደቱ ውስጥ በመሳተፍ የዳበረ ውይይት እንዲደረግ የበኩላችንን አስተዋጽኦ እንደምናደርግ በዚህ አጋጣሚ እናሳውቃለን።

አገራችን ኢትዮጵያ በነጻነት፣ በእኩልነት እና በፍትህ ለዘላለም ትኑር!!

አለምአቀፍ የኢትዮጵያዊያን የጋራ ግብረሀይል1 እና

የኢትዮጵያ ማህበረሰባዊ ድርጅቶች ትብብር2 

ግልባጭ፦ ለኢሳት፣ ለኦኤምኤን፣ ለቮይስ ኦፍ አሜሪካ፣ ለዶቸቬሌ እና ሌሎች የሚዲያ ተቋማት 

መግለጫ፦

  1. አለምአቀፍ የኢትዮጵያዊያን የጋራ ግብረሀይል በተለያዩ ክፍለ-ዓለማት የሚገኙ እና በከተማ ደረጃ የተዋቀሩ ግብረሀይሎችን በአለምአቀፍ ደረጃ የሚያስተባብር የጋራ ስብስብ ነው።
  2. የኢትዮጵያ ማህበረሰባዊ ድርጅቶች ትብብር ከታች የተዘረዘሩትን ድርጅቶች በጋራ የሚያስተባብር አካል ነው።
  • የአፋር ሰብአዊ መብት ድርጅት
  • የኢትዮጵያ ሴቶች መብት ማእከል
  • የሰብአዊ መብት ማህበር በኢትዮጵያ
  • የባለራእይ ወጣቶች ማህበር
  • የድንበር ጉዳዮች ኮሚቴ
  • የኢትዮጵያ የውይይት መድረክ
  • የኢትዮጵያዊያን አሜሪካዊያን ምክርቤት
  • የኢትዮጵያ ውርስ እና ቅርስ ማህበር በሰሜን አሜሪካ
  • የኢትዮጵያዊነት የዜጎች መብት ማስከበሪያ ጉባኤ
  • የመጀመሪያው ሂጅራ ፋውንዴሽን
  • የቀድሞ የኢትዮጵያ መከላከያ እና ፖሊስ አባላት ማህበር
  • ጋሻ ለኢትዮጵያ
  • ዓለምአቀፍ ትብብር ለኢትዮጵያዊያን መብት
  • የኢትዮጵያ ህብረት (የክፍለሀገራት ህብረት)
  • ዓለምአቀፍ የኢትዮጵያ ወጣቶች አንድነት
  • አንድ ኢትዮጵያ ንቅናቄ
  • የተባበሩት የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ንቅናቄ
  • ሕጋዊው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን
  • የአዲሲቱ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ
  • የወላይታ እና ተባባሪዎቹ ማህበር በሰሜን አሜሪካ
  • የተባበሩት የቀድሞ አየር ሃይል አባላት ኢንተርናሽናል ማህበር
  • የኢትዮጵያ ራእይ (ቪዥን ኢትዮጵያ)
  • ያ ትውልድ ተቋም
  • የቀድሞ የኢትዮጵያ አየር ሀይል አባላት በዋሽንግተን ዲሲ
  • የተጠቂዎች ድምጽ ድርጅት

Zemecha18@gmail.com  202-627-0130

info@tibibir.orgwww.tibibir.org  773-341-8511


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule