
“አንተም በግብፅ ምድር ባሪያ እንደነበርክ አስብ ይህንን ስርአት ጠብቀውም አድርገውም”
ኦሪት ዘዳግም 16 – 12
የንግስት ሳባና የጠቢቡ የንጉስ ሰለሞንን ግንኙነት ተገን አድርጎ የተፈጠረው ሚኒሊክና ሚኒሊክን አጅቦ ከተስፋይቱ ምድር ወደ ታላቋ አገራችን የገባው የኦሪት እምነት አያሌ ሺህ ዘመናትን ማስቆጠሩን የሁለቱም አገር ሕዝቦችና መንግስታት ሊዘነጉት የማይችሉት የእምነት ትስስር ቁርኝቱ እስከ ዛሬ ድረስ አልተበጠሰም።
የክርስትናው እምነት ገኖ በበላይነት እስከተስፋፋበት ጊዜ ድረስ በኢትዮጵያ የኦሪት እምነትን ተከታይ እንደነበረችና በአገራችን ለእምነት ፅኑ መሰረት ወይም ትኩረት የማይሰጡ መንግስታት በተፈራረቁ ቁጥር ሕዝባችን ዛሬም “የእስራኤል አምላክ የተመሰገነ ይሁን” የሚለውን የምስጋና ቃል ከማስተጋባት አልቦዘነም።
የዛሬዋ ነፃይቱ እስራኤል ገና የ64 አመት እድሜ ባለፀጋና በወሽመጥ መሰል ካርታዋ ተከልላ ከአረብ አገራት ጋር ተፋጣ ኢኮኖሚያዊ ፖለቲካዊና ማህበራዊ መሰረቷን አጎልብታ በአለም አሉ ከሚባሉና በሁሉም ረገድ ተፅእኖ ለማሳረፍ በሚችሉ ጠንካራ ህዝቦቿ ህብረት ከብረት በጠነከረ ፅናቷ ጠላቶቿን ድል አድርጋ ዛሬ በወታደራዊ ሆነ በኢኮናሚያዊ ዘርፎች ክንዷን አፈርጥማ በመካከለኛው ምስራቅ ብቸኛዋ የዲሞክራሲ ስርአት ጮራ ፈንጣቂ ለመሆን የበቃች የቆዳ ስፋቷ ትንሽ ጥበቧ ትልቅ የሆነች አገር ናት።
የእስራኤል የነፃነት ኩራት በዋዛ የተገኘ ሳይሆን አገሪቱ እንደ አገር ያቆማት በዜጎቿ ደምና አጥንት የተማገረች እንደሆነች ብዙ ዋቢ መጥቀስ ይቻላል ሆኖም የዚህ ፅሁፍ አላማ ናዚ ያደሰውን ጨካኝ የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ ማስተጋባት ሳይሆን የተስፋይቱ ምድር ከነፃነቷ በኋላም እስከ ዛሬ ልጆቿን ከአለም ዳርቻ ሳትሰበስብ በስደተኛ ወገኖቼ ላይ እየወሰደች ያለችውን መራር እርምጃ መንግስቷና ሕዝቧ የስደተኛውን ችግር በመገንዘብና በኦሪት ዘፍጥረት 15 – 15 ላይ “አንተም በግብፅ ምድር ባሪያ ነበርህ አምላክህ እግዚአብሔር እንዳዳነህ አስብ” የሚለው አምላካዊ ቃል ትእዛዝ መሆኑ ቀርቶ በባለጊዜዎች እንደ ተረት መታየቱ በኢትዮጵያውያን ወገኖቼ ላይ እየደረሰባቸው ያለውን ሰቆቃ ለማሰማትና ኢትዮጵያውያኑ እንደ አገራቸው ለመኖር ተስፋ ያደረጉባት ምድር ሲኦል ልትሆንባቸው እንደማይገባ የበኩሌን ለማለት ስለፈቀድኩ በታሳሪዎች ስም አለማቀፍ ማህበረሰብ ይታደገን ዘንድ ማለት የሚገባኝን ለማለት ወደድኩ።
ዛሬ እኛ የነበረችንን ታላቅ አገር ጥቂት ጎጠኞች በሚያራምዱት የበቀል ፖለቲካ አገራችንን በታትነው እኛንም የመኖር ዋስትና አሳጥተው ለስደት ለእስራት ለሞት የዳረጉን የአገራችንን ታሪክና እምነት እያጎደፉ ካሉ ሞገደኞች ሕይወታቸውን ለማትረፍ ከሞት ጋር ትንቅንቅ ገጥመው የሲናን በረሃ ዘግናኝ ጉዞ ኩላሊታቸውንና ሌላ የሰውነት አካላቸውን የተነጠቁ /የተዘረፉ/ እና በአምላክ ቸርነት ይህ የበረሃ ላይ የውስጥ አካልን ከመዘረፍ ያመለጡ ሕፃናት፣ ወጣቶችና ጎልማሳዎች ነፍሳችን ተረፈች በማለት በተስፋይቱ ምድር በአዲስ ተስፋ ተሞልተው በተገቢው የስደተኛ መብት በመጠቀም የራሳቸውን የአገራቸውንና የሕዝባቸውን የሰቆቃ ኑሮና እንግልት ለአለም ህዝቦች ለማሰማት እየፈለጉ በተቃራኒው ከነ መከራቸው ተስፋና መሸሸጊያ ትሆነናለች ባሉት ቅድስት አገር ኢትዮጵያውያኑ ከድንኳን በተዘጋጁ የጠረፍ እስር ቤቶች ያለ ጠያቂ ያለፉትን ሶስትና አራት አመታት እሮጠው ያልጠገቡ ሕፃናት ሳይቀሩ በበጋ ሐሩር በክረምት ቅዝቃዜ ሲጠበሱ ማየት ኢትዮጵያውያንን ብቻ የሚያሳስብ ሳይሆን ማንም የሰከነ ህሊና ላለው ፍጡር ሁሉ የኢትዮጵያውያኑ መከራ ሊያሳስበው ሊያስጨንቀው መላ ሊያፈላልግለት የሚገባው ጉዳይ ሊሆን እንደሚችል አያከራክርም።
ማንም ሰው አስገዳጅ ሁኔታ ካልተከሰተበት በነፃነት የሚኖርባትን የራሱን የክብር ስፍራ ጥሎ በዘመናዊ ባርነት ለመገዛት የሚቋምጥ ይኖራል ብዬ አላምንም። ማንም ክብሩን ትቢያ ላይ መጣል አይሻም። የማንንም አገር ዘላለማዊ እርስቱ አድርጎ ለመኖር የሚሻ ቀን የጎደለበት ስደተኛ ይኖራል ብዬ አላስብም። መንግስታት ዜጎቻቸውን እንዳይሰደዱ ሀላፊነት የሚሰማው ተግባር ለመከወን ዝግጁ ቢሆኑ ዛሬ የሰው ልጅ ባህር እያሰመጠው እንደ ሸቀጥ በኮንቴይነር እየታሸገ በሚፈጠር የአየር እጥረት እየሞተ ከዚያም ተረፍኩ ሲል የባእዳን ዜጎች ክብረ ነክ የሆነ የወሲብ ፈረሳቸውን ጭነው የሚጋልቡበት መሆንን ማንም እንዲህ አይነቱን ፅልመት ወይም የሞት ታናሽ ወንድም ወደ ሆነ መንከራተት ሊያመራ እንደማይሻ እያንዳንዱ አገር እመራለሁ የሚል የመንግስት አካል ሊያውቅ ይገባዋል።
ዛሬ እስራኤላውያን በአለም ዙሪያ ከሚኖሩበት የማይኖሩበትን አገር መቁጠር ይቀላል፣ እነሱ በመላው አለም የመኖር ዋስትናቸውን አረጋግጠው ሐብት አፍርተው በእውቀት ደርጅተው እየኖሩ የገዛ አገሩ ሳትሆን አገር እንመራለን በሚሉ ለኢትዮጵያና ሕዝቧ መቅሰፍት የሆኑ የራሳቸውን ሕዝብ እያሸበሩ ሽብርተኛነትን እንዋጋለን በሚሉ አስተሳሰብ ድውያን የተፈጠረን ችግር የሌላ አገር መንግስታት እስራኤልን ጨምሮ ለኢትዮጵያውያን ስደተኞች ጆሮ ዳባ ልበስ ማለታቸውን በእጅጉ ያሳዝናል።
የዛሬዋ እስራኤል በ1948 በውድ ልጇ በዳቪድ ቬንጎሪዮን የነፃነት ሸማዋን መልበሷ ከመታወጁ በፊት የእኛ ኢትዮጵያውያን የቀደሙ ወገኖቻችን በእስራኤል ምድር መኖራቸው የዛሬዎቹ የእስራኤል ሹማምንት ለምን ትዝ አልላቸው አለ? ለምንስ እንደ እንግዳ ሊመለከቱን አሰቡ? “ከኋላ የበቀለ ቀንድ ጆሮን ቀደመው” እንደተባለው ለአገሪቱ ቀዳሚ የነበርን የዛሬ ታሳሪ የሆንን ወገኖች በአሳሪዎቻችን ምን ይወሰንብን ይሆን? “ጊዜ ለኩሉ” የተባለው ለእንዲህ አይነት ገጠመኝ ይመስለኛል። “የጊዜ እንጂ የሰው ጀግና የለውም” እንዲሉ ጊዜ ተለውጦ በክብር መኖር የሚገባን የእስራኤል ወዳጆች በምናከብራቸውና በእምነት በምንመስላቸው ወገኖቻችን መታሰራችን አስገራሚም አሳዛኝም ክስተት ነው ብዬ አምናለሁ።
የኢትዮጵያውያንን ዛሬ በእስራኤል ምድር መታሰር በተመለከተ ነፍስ ዘርቶ መቃብር ፈንቅሎ ጠቢቡ ሰለሞን ቢሰማ የዛሬዎቹ እስራኤላውያን ያንን ዘመን ያስቆጠረን የፍቅርና የእምነት ትስስር አፈር እያለበሱት እንዳሉ ይረዱ ይሆን? ሰው በቤቱ እንዴት ይታሰራል? ዛሬ ኢትዮጵያውያን በቅድስት አገር ነፍሳቸውን ለመታደግ የሚያደርጉትን እሩጫ ለነፍሳቸው መድህን መሆን የሚጋባው አካል በአገራቸው ከፈሩትና ከሸሹት ባልተናነሰ መጠን በእስር ለአመታት ሲያሰቃያቸው ማየት ለኔ ኦሪትን መፃረርና የእስራኤል አምላክ ሲል የኖረን የኢትዮጵያን ሕዝብ የፍቅር ልብ ማጉደፍ ይመስለኛል።
የእግዚአብሔር ቃል እንዲህ ይላል ኦሪት ዘዳግም 5 – 6 “ከግብፅ ምድር ከባርነት ቤት ያወጣሁ እግዚአብሔር አምላክህ እኔ ነኝ” ይላል።
እናም የሚያመልኩት አምላክ የባርነት ሰንሰላታቸውን የፈታላቸው እስራኤላውያን አምላክ ያላቸውን እረስተው ዛሬ ማጣፊያ አጥሮት የመኖር ህልውናው አደጋ ላይ የወደቀን ስደተኛን አስሮ ማስጨነቅ የትላንት የግብፅ ምድርን ባርነት መዘንጋትና መንፈሳዊ ተቃርኖን መፍጠር እንደሆነ አያጠያይቅም።
ኦሪትን እከታተላለሁ ቃሉንም አከብራለሁ እንደ እምነቴ በቃሉ እመራለሁ የሚል መንግስትና ሕዝብ መጠጊያ ያጣን ወገን በበረሃ አስሮ ማሰቃየትና ማስጨነቅ የበደል ሁሉ በደል የጭካኔ ሁሉ ጭካኔ ከመሆን አልፎ በኦሪት ዘፍጥረት 24 – 14 ላይ የተጠቀሰውን “ደሃና ችግረኛውን አታስጨንቀው” የሚለውን አምላካዊ ትእዛዝ መሸርሸር እንደሆነ የድርጊቱ ፈፃሚዎች ሊረዱት ይገባል።
በአጠቃላይ ዛሬ ፍትህ፣ ዲምክራሲና ሰላም ከራቋት አገራችን በሚደርስብን የገዥው መደብ በደል ተገፍትረን ሳንወድ በግድ በተለያየ ቦታ የመከራ ቁና እየሰፈርን የምንገኝ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ለመታደግ እጅግ የተቀነባበረና አንድ ወጥ ዘመቻ በስደተኞች ዙሪያ የማድረጉ ተልእኮ በታዋቂ ኢትዮጵያውያን ጥረትና መሉ ፈቃደኛነት እራሱን የቻለ ግብረ ኃይል በመላው አለም ወገንን የመታደግ ዘመቻ ነገ ዛሬ ሳይባል በተለይ ጉዳዩ የሚመለከተው UNHCR የተባለን ተቋምና ሌሎች የግብረ ሰናይ ድርጅቶችን በማስተባበር በተለያየ የአለም ክፍል በኢትዮጵያውያን ስደተኞች ላይ ከአገር ቤት ባልተናነሰ መጠን የሚዘንብብንን የመከራ ዝናብ እንዲያባራልን ሁሉም አገርና ወገን ወዳድ የሆነ ግለሰብም ሆነ አንጋፋ የፖለቲካ ድርጅቶች ፖለቲካው ላይ ብቻ የሚያሰሙንት እሰጥ አገባ እንደተጠበቀ ሆኖ የወገኖቻቸውን ሰቆቃ ለአለም አቀፍ ማህበረሰብ የማሰማት ግዴታ ይጠበቅባቸዋል። በዚፍ ዘርፍ አዲስ መርሐ ግብር መንደፍ ካልቻሉ እንመራዋለን የሚሉት ፖለቲካ ያለ ህዝብ ድጋፍ ውሀ ስለማይቋጥር አዲስ የአሰራር ስልት በአፋጣኛ ሊፈጥሩ ሁኔታዎች ያስገድዳሉ። ይህንንም የወገን የድረሱልኝ ጥሪ ምላሽ ለማስገኘት ሊተባበሩ ይገባል የሚል እምነት አለኝ።
የዚህ ፅሑፍ ማሳረጊያ ለማድረግ የምሻው በመላው አለም የምንገኝ ኢትዮጵያውያን የተነጠቅነውን በአገራችን የመኖር ዋስትና ዳግመኛ እንጎናፀፈው ዘንድ ከምንጊዜውም ይበልጥ ለነፃነታችን መመለስ ባለን አጋጣሚ ሁሉ በመታገዝ ፀረ ወያኔ ትግላችንን ማጎልበትና ከመበታተን ወደ አንድነት የምናመራበትን አማራጭ በማጎልበት ለአገራችን ምድር እንበቃ ዘንድ በአንድነት በያለንበት ለወሳኝ ትግልና ድል እንነሳ።
ቸር ይግጠመን
ሳሙኤል /ከእስራኤል/
Dnt blame israel for ethiopian problem . U must understand that israel is very small country dnt have enough place even for its own citizen and ethiopians are all overe the place and i dnt think king solomon wary about ethiopia .the lady saba went there by her own and slept with him she is not maried with him
what a crap article.everyone think israel is best friend of ethiopia that is bullshit.right now ethiopia have more trade with arab countries than israel.when we ethiopians learn and stand up for our nation advantage.we should be like other nation ,keep our interest first.israel glory is for the jews not ethiopians.our refuges must be treat humanly according to united nation cord.israel is well known not respecting UN cord.you dont detain refugees indefinate,i dont ask to give them resident permit but atleast let them apply refugee status with UN.there is much better countries which can give them settlment.when they migrate to ethiopia long time ago we dont detain them prehapes freedom which never enjoy in their life.they should known better what goes around, come around.
Hi Mr. Samuel ! I totally understand your point. You need some help for the imprisoned migrants, yeah! But don’t mix up things to justify your case. All your arguments are irrelevant to support your message. BTW, ኦሪት ዘፍጥረት 15 – 15 tells nothing like what you said it refers to. Second, you said “…እምነት በምንመስላቸው ወገኖቻችን መታሰራችን አስገራሚም አሳዛኝም ክስተት ነው ብዬ አምናለሁ።” That is ridiculous man! Since when did the Israelites become Christians? I don’t know what kind of Bible you are reading from! But if we both are reading the same Bible, go and read Mt. 27- 25. It says “All the people answered, ‘His blood be on us and on our children! Then he released for them Barab’bas, and having scourged Jesus, delivered him to be crucified.” You see… these people were murderers and still are !! They don’t have a heart for outsiders. See what they are doing to their Palestinian brothers. We are not any closer to them than the Palestinians. The fact that Ethiopian Christians refer to Israel is for the place not for the people.
Criticizing Israelis is correct as they should not forget very quickly their suffering and humiliation in Egypt and under Nazi Germany. In my opinion, they must be defenders of human rights and protectors of all persecuted refugees who seek shelter in Israel. unfortunately, the fact is the opposite and many Ethiopians are suffering in their prisons. The person before me has said that Ethiopia has more trade with the Arabs than Israel and Ethiopia has to strength her relation with Arabs. But doing more trade is not a sign of friendship and good relation. It should not be forgotten that it is Middle East Arabs who are beating, torturing, raping, humiliating and killing Ethiopian maids as if Ethiopians are born for suffering and brutal killing. Last but not least, I would like to appreciate the writer of the article.
አይሁድ ማለት፤የጀርመን ናዚ ማለት ነው። አይሁድ ማለት የክርስትያኖችን እየሱስ ክርስቶስ ጠላት ማለት ነው። ከእስራኤሎች የምትጠብቁ የተረት ተረት አሞጋሾች ዝዮኒዝምን (ናዚኢዝምን) ማሞገስ ማለት ስለሆነ ካሁኑኑ ቅዠታችሁን አቁሙ። በቤተ እስራል ስም “ጥቁር አይሁድ” እያሉ ከእስራሎች ጋር የሚያገናኘን ምንም ደም ሳይኖረን ወያኔ፤ሻዕቢያ፤ደረግ፤ሶአይ ኤ፤ ሞሳድ እና አንዳንድ ባነዳ ህለሰቦች ዘመዶቻችን በዘመናዊ ባርያነት በገንዘብ ሸጠዋቸው ወደ ባርያ ፈንጋይዋ አይሁዳዊቷ እስራል ተሽጠዋል። እዛ ሲደርሱም የባሰ ዘረኝነት ገጥሟቸው ይኸው በዜና እያነበብን ነው። ለዚህ ሁሉ ውረርደት ተጠያቂው ማን ይሆን።
ስለዚህ “አስሬ” እሳራኤል ቅብጥርጥርዮሽ የምትሉት ተረት ተረት ውዳሴአችሁን ካሁኑኑ አቁሙ። እስራል ማለት ማዚ ማለት ነው። ዘመዶቼ በባርነት ተይዘው በገንዘብ ተሽጠዋል። ለዚህ ደግሞ ጥቂት ሰዎች ካልሆኑ ያወገዙት “ባርነቱን” ሕጋዊ ነው ብለውታል። የእስራል ናዚዎች ሌላ ቀርቶ ወያኔን ተገን አድርገው በሰንደቃላማችን ላይ ኰኮባቸውን ለጥፈውበታል። ስንት ጊዜ ልት ኙ ነው እናንተ ኢትዮጵያያን? እስራኤል ሳትኦን ኢትዮጵያ ናት የአምላክ መናኸርያ እና ክርስቶስ የተወለደባት ምድር። የተቀረው ተረት ነው። ናዚዎች/ዘጽዮናዊያን የገለበጡት ውሸት ታሪካችንን አስመልሱ። እስራልን ማሞገስ ይብቃ; እኛ የኢትዮጵያ ልጆች አንጂ የነዚዎቹ ባርያ ፈንጋዮች የእስረኤል ልጆች አይደለንም። አመሰግናለሁ።ይልቁንስ የተሸጡት ዘመዶቻችን የሚያስመልስ ግብረሃይል ባስቸኳይ አቋቁሙልን፤፡ ከመነሻው “አረብ እና አይሁዶች” የኢትዮጵያ መርዞች ሆነው ነው የተፈጠሩት ናቸው። ጌታቸው ረዳ (ኢትዮጵያን ሰማይ ብሎግ አዘጋጅ)
This is a sad story. The only solution that will bring to an end the suffering and humiliation of our brothers and sisters in the hands of Israelis and Arabs is to build a peaceful and prosperous Ethiopia and Eritrea with ample opportunity to fulfill the aspirations of their citizens.