• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በውኑ መንፈስ ይታሰራልን?

August 10, 2013 11:47 pm by Editor 2 Comments

እንደ ህወሃት አይነት አምባገነን መንግስታት ከተጠናወታቸው በርካታ ችግሮች መካከል ትግል እና ታጋይን ነጣጥሎ ያለማየት ችግር ሲሆን የትግል መሰረቱ ፍትህ እስከሆነ ድረስ፣የትግል መዳረሻው በተፈጥሮ የተገኘን መብት በችሮታ ካልሰጠናችሁ ከሚሉ አምባገነኖች መዳፍ ፈልቅቆ ለማውጣት እስከሆነ ድረስ በእርግጥም ይህ ትግል ከስጋና ከደም በላይ የተሻገረ በብዙሃን ላይ የሚሰርፅ መንፈስ ነው።ስለሆነም እንደመንፈስ የረቀቀው ትግል በታጋዩ ላይ ገዝፎ ይገለጥ ይሆናል እንጂ ታጋዩ ቢሰዋ አልያም በአምባገነኖች የግዞት እስር ቢወረወር ትግሉ አይታሰርም ደግሞም አይሞትም።

ለምሳሌ ፀረ-አፓርታይድ ትግል ማጠንጠኛው ማህበራዊ፣ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ፍትህን መሻት እንዲሁም የዘረኝነትን ክፉ ቀንበር መሰባበር ነበር።

ነገር ግን በወቅቱ የነበሩ የዘረኛው አፓርታይዳዊ አገዛዝ አመራሮች የትግሉን ረቂቅ ወጣቶችንና አዛውንቶችን ለእስርና ለሞት ከመዳረጋቸው ባሻገር የትግሉን መሪ ኔልሰን ማንዴላን በሮበን ደሴት ላይ ለ27 ዓመታት ሊያስሩ ችለዋል።ይሁን እንጂ የትግሉ መንፈስ ፍትህና ነፃነትን የሚፈልጉትን ሁሉ ኮርኩሮ የመቀስቀስ አቅም ስለነበረው ፀረ-አፓርታይድ ፍልሚያው እንደ ሰደድ እሳት ከያቅጣጫው ይንቀለቀል ነበር።ይልቁንም ታጋዮችን በመስበር ትግሉን እናከስማለን የሚሉትን አምባገነኖች የትግሉ ወላፈን እየበላቸው ዛሬ ከመጥፎ ተሞክሯቸው ጋር ታሪክ ሆነው ቀርተዋል።

በሀገራችን ኢትዮጵያም እየተከሰተ ያለው ሁኔታ ከዚህ ብዙም የሚርቅ አይደለም።ታጋዮችን ላነሳሳቸው የህዝብ ጥያቄ መልስ ከመስጠት ይልቅ በግለሰቦች ላይ የሚደረገው ጥቃት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከፋ ቢመጣም የትግሉ እቶን ይበልጥ ከመንደድ ወደኋላ አላለም።ሠርካለም ፋሲል በግፍ በወህኒ እንድትወልድ መደረጉ እነ ርዕዮት አለሙን ከጋዜጠኝነት አላሸሻቸውም፥ይልቁን ስለእውነት እና ፍትህ በመቆም ለብዙ ወጣቶች አርአያ በመሆን የወያኔን የግፍ ፅዋ በወኔ ተጎነጨችው እንጂ።እስክንድር ነጋን በግፍ በህፃን ልጁ ፊት በካቴና በማሰር ወደ ወህኒ ሲጋዝ፣በውርስ ያገኘውን የእናቱን ቤት መንግስት ሲወርሰው በርግጥም በወያኔ ሹማምንት ስሌት ”እስክንድርን ያየ ይቀጣ” በሚል የህዝብ የነፃነት ጥያቄ በፍርሃት ካባ ተሸፍኖ ይቀራል ከሚል የመነጨ ነበር።

በቀለ ገርባን በማሠር፣ባለቤቱን በግፍ ከሥራ በማፈናቀል የተተኪው ትውልድ አካል የሆኑ ህፃናት ልጆቹን ለችግር  በማጋለጥ የኢትዮጵያን ህዝብ የነፃነት ጥያቄ ማፈን አይቻልም።ይልቁን ዛሬ የትግሉ መንፈስ አድማስን ተሻግሮ የነፃነት ጩኸታችንን በአውሮፓ እና በአሜሪካ መንግስታት ተወካዮች ሳይቀር እየተስተጋባ ይገኛል።በቅርቡ በአውሮፓ ህብረት ፓርላማ  የሰብዓዊ መብት ኮሚቴ አባላት በጀርመናዊቷ ባርባራ ሎክቢለር በመመራት ወደ አዲስ አበባ ያቀና ሲሆን በኢትዮጵያ የሚታየው የሰብዓዊ መብት አያያዝ አሳሳቢ መሆኑን የህሊናና የፖለቲካ እስረኞችን ሁኔታ ለማየት ወደ ቃሊቲ እንዲሄዱ ከተደረገ በኋላ በተለመደው የወያኔ ድራማ ከስፍራው ያለ ውጤት እንዲመለሱ ተደርጓል።

በአንድ ነገር ይበልጥ እርግጠኞች ነን፦እልፎች በወያኔ ግዞት በግፍ ሊጣሉ ይችላሉ፣ አዕላፍት ሊሰው ይችላሉ። ነገር ግን የትግላችን መሠረት የሆነው የነፃነት፣የእኩልነት፣የፍትሀዊ የሀብት ክፍፍል፣የማህበራዊ ኢኮኖሚያዊና የፖለቲካዊ ፍትህ ጥያቄያችን ግን ፈፅሞ በግዞት በቃሊቲና መሰል ወኅኒዎች ሊታሠር አይችልም። (ፎቶ: በጸሃፊው የተላከ)

ጸሃፊው በዚህ አድራሻ ይገኛሉ: beyenemesfin77@yahoo.com

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. አለም says

    August 12, 2013 12:22 am at 12:22 am

    የኢትዮፕያን ሪቪው አታሚ ኤልያስ ክፍሌ እንዴት እዚህ ውስጥ ተገኘ?

    Reply
    • abiti says

      August 12, 2013 11:33 am at 11:33 am

      (ፎቶ: በጸሃፊው የተላከ)

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule