• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በውኑ መንፈስ ይታሰራልን?

August 10, 2013 11:47 pm by Editor 2 Comments

እንደ ህወሃት አይነት አምባገነን መንግስታት ከተጠናወታቸው በርካታ ችግሮች መካከል ትግል እና ታጋይን ነጣጥሎ ያለማየት ችግር ሲሆን የትግል መሰረቱ ፍትህ እስከሆነ ድረስ፣የትግል መዳረሻው በተፈጥሮ የተገኘን መብት በችሮታ ካልሰጠናችሁ ከሚሉ አምባገነኖች መዳፍ ፈልቅቆ ለማውጣት እስከሆነ ድረስ በእርግጥም ይህ ትግል ከስጋና ከደም በላይ የተሻገረ በብዙሃን ላይ የሚሰርፅ መንፈስ ነው።ስለሆነም እንደመንፈስ የረቀቀው ትግል በታጋዩ ላይ ገዝፎ ይገለጥ ይሆናል እንጂ ታጋዩ ቢሰዋ አልያም በአምባገነኖች የግዞት እስር ቢወረወር ትግሉ አይታሰርም ደግሞም አይሞትም።

ለምሳሌ ፀረ-አፓርታይድ ትግል ማጠንጠኛው ማህበራዊ፣ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ፍትህን መሻት እንዲሁም የዘረኝነትን ክፉ ቀንበር መሰባበር ነበር።

ነገር ግን በወቅቱ የነበሩ የዘረኛው አፓርታይዳዊ አገዛዝ አመራሮች የትግሉን ረቂቅ ወጣቶችንና አዛውንቶችን ለእስርና ለሞት ከመዳረጋቸው ባሻገር የትግሉን መሪ ኔልሰን ማንዴላን በሮበን ደሴት ላይ ለ27 ዓመታት ሊያስሩ ችለዋል።ይሁን እንጂ የትግሉ መንፈስ ፍትህና ነፃነትን የሚፈልጉትን ሁሉ ኮርኩሮ የመቀስቀስ አቅም ስለነበረው ፀረ-አፓርታይድ ፍልሚያው እንደ ሰደድ እሳት ከያቅጣጫው ይንቀለቀል ነበር።ይልቁንም ታጋዮችን በመስበር ትግሉን እናከስማለን የሚሉትን አምባገነኖች የትግሉ ወላፈን እየበላቸው ዛሬ ከመጥፎ ተሞክሯቸው ጋር ታሪክ ሆነው ቀርተዋል።

በሀገራችን ኢትዮጵያም እየተከሰተ ያለው ሁኔታ ከዚህ ብዙም የሚርቅ አይደለም።ታጋዮችን ላነሳሳቸው የህዝብ ጥያቄ መልስ ከመስጠት ይልቅ በግለሰቦች ላይ የሚደረገው ጥቃት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከፋ ቢመጣም የትግሉ እቶን ይበልጥ ከመንደድ ወደኋላ አላለም።ሠርካለም ፋሲል በግፍ በወህኒ እንድትወልድ መደረጉ እነ ርዕዮት አለሙን ከጋዜጠኝነት አላሸሻቸውም፥ይልቁን ስለእውነት እና ፍትህ በመቆም ለብዙ ወጣቶች አርአያ በመሆን የወያኔን የግፍ ፅዋ በወኔ ተጎነጨችው እንጂ።እስክንድር ነጋን በግፍ በህፃን ልጁ ፊት በካቴና በማሰር ወደ ወህኒ ሲጋዝ፣በውርስ ያገኘውን የእናቱን ቤት መንግስት ሲወርሰው በርግጥም በወያኔ ሹማምንት ስሌት ”እስክንድርን ያየ ይቀጣ” በሚል የህዝብ የነፃነት ጥያቄ በፍርሃት ካባ ተሸፍኖ ይቀራል ከሚል የመነጨ ነበር።

በቀለ ገርባን በማሠር፣ባለቤቱን በግፍ ከሥራ በማፈናቀል የተተኪው ትውልድ አካል የሆኑ ህፃናት ልጆቹን ለችግር  በማጋለጥ የኢትዮጵያን ህዝብ የነፃነት ጥያቄ ማፈን አይቻልም።ይልቁን ዛሬ የትግሉ መንፈስ አድማስን ተሻግሮ የነፃነት ጩኸታችንን በአውሮፓ እና በአሜሪካ መንግስታት ተወካዮች ሳይቀር እየተስተጋባ ይገኛል።በቅርቡ በአውሮፓ ህብረት ፓርላማ  የሰብዓዊ መብት ኮሚቴ አባላት በጀርመናዊቷ ባርባራ ሎክቢለር በመመራት ወደ አዲስ አበባ ያቀና ሲሆን በኢትዮጵያ የሚታየው የሰብዓዊ መብት አያያዝ አሳሳቢ መሆኑን የህሊናና የፖለቲካ እስረኞችን ሁኔታ ለማየት ወደ ቃሊቲ እንዲሄዱ ከተደረገ በኋላ በተለመደው የወያኔ ድራማ ከስፍራው ያለ ውጤት እንዲመለሱ ተደርጓል።

በአንድ ነገር ይበልጥ እርግጠኞች ነን፦እልፎች በወያኔ ግዞት በግፍ ሊጣሉ ይችላሉ፣ አዕላፍት ሊሰው ይችላሉ። ነገር ግን የትግላችን መሠረት የሆነው የነፃነት፣የእኩልነት፣የፍትሀዊ የሀብት ክፍፍል፣የማህበራዊ ኢኮኖሚያዊና የፖለቲካዊ ፍትህ ጥያቄያችን ግን ፈፅሞ በግዞት በቃሊቲና መሰል ወኅኒዎች ሊታሠር አይችልም። (ፎቶ: በጸሃፊው የተላከ)

ጸሃፊው በዚህ አድራሻ ይገኛሉ: beyenemesfin77@yahoo.com

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. አለም says

    August 12, 2013 12:22 am at 12:22 am

    የኢትዮፕያን ሪቪው አታሚ ኤልያስ ክፍሌ እንዴት እዚህ ውስጥ ተገኘ?

    Reply
    • abiti says

      August 12, 2013 11:33 am at 11:33 am

      (ፎቶ: በጸሃፊው የተላከ)

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule