• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሕገወጥ ደም ሻጮች የከሰሩበት

June 25, 2014 02:55 am by Editor Leave a Comment

ከአንድ ዓመት በፊት አንድ ህመምተኛ ለሚደረግለት ህክምና ደም የሚያስፈልገው ከሆነ፣ ቤተሰብ አሊያም ወዳጅ ዘመድ ምትክ ደም ሰጥቶለትና የሚያስፈልገው የደም አይነት ከደም ባንክ ወጥቶለት ይታከም ነበር፡፡

ይህ አሠራር ግን በርካቶች የሚያስፈልጋቸውን ደም በቀላሉ እንዳያገኙ የሚያደርግ ሆኖ ቆይቷል፡፡

ቤተሰብ አሊያም የታካሚው የቅርብ ወዳጆችም ‹‹ደም ለግሱና ደማችሁ ተተክቶ ለታካሚው ሌላ ደም ይሰጠው›› የሚለውን ሐሳብ ሲሰሙ ሃሳቡን ይሸሻሉ፣ ከልገሳው ያፈገፍጋሉ እንዲሁም ይፈራሉ፡፡ በዚህም ምክንያት ደማቸው ተወስዶ እምብዛም ጥቅም ላይ መዋል የማይችል ግለሰቦች በደላሎች አማካይነት  በሽያጭ ደም ይለግሳሉ፡፡ ደም ባንክ የእነዚህን ሰዎች ደም በምትክ ወስዶ ከባንኩ ለታካሚዎች ደም ቢሰጥም፣ በሕገወጥ መንገድ ተሸጦ ገቢ የተደረገው ደም ከሞላ ጎደል ይወገድ እንደነበር ባንኩ ይገልጻል፡፡

ይሁንና የዛሬ ዓመት ገደማ ብሔራዊ ደም ባንክ በጀመረው አዲስ አሠራር መሠረት፣ በመንግሥት የሕክምና ተቋም የሚታከሙ ግለሰቦች  የሚያስፈልጋቸው ደም አለምትክ እንዲሰጣቸው አድርጓል፡፡ ይህ መሆኑ ደግሞ በሕገወጥ መንገድ አላግባብ ደማቸውን የሚሸጡ ግለሰቦችን አስቀርቷል፡፡

‹‹የቤተሰብ ደም ተተክቶ ደም ይሰጥ በነበረበት ጊዜ ደላሎች ደም እየሸጡ ከአንድ ሺሕ እስከ ሁለት ሺሕ ብር ድረስ ይቀበሉ ነበር፡፡ ይህንን መረጃ እኛም ልክ እንደ ኅብረተሰቡ በወሬ ደረጃ ነበር የምንሰማው፡፡ ግለሰቦቹን ለመያዝ ከፖሊስ ጋር ተጣምረን ብንሠራም ሕገወጦቹን ማግኘት አልቻልንም ነበር፤›› ያሉት የብሔራዊ ደም ባንክ አገልግሎት ዳይሬክተር ዶ/ር ዳንኤል ገብረ ሚካኤል፣ በአሥራ አንድ ወር የሥራ አፈጻጸም ጊዜ ውስጥ የበጎ ፈቃደኞች ደም ልገሳ ከመቼውም በላይ ጨምሮ ሕገወጦቹ ከጨዋታ ውጪ እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡

ምትክ ደም መስጠት ከመቅረቱ በፊት ከበጎ ፈቃደኞች በዓመት የሚሰበሰበው ደም 30 በመቶ አይሞላም ነበር፡፡ ዶክተር ዳንኤል እንደሚሉት ይህ ዛሬ ተቀይሯል፡፡ ምትክ ደምን የማስቀረት ሥራ ሙሉ በሙሉ በመሳካቱ ባለፉት 11 ወራት በነበረው አፈጻጸም በአገር አቀፍ ደረጃ ከበጎ ፈቃደኞች የተሰበሰበው የደም ብዛትም 68 በመቶ ደርሷል፡፡ ቀሪውንም 32 በመቶ ደም ከበጎ ፈቃደኞቹ ለመሰብሰብም ቀላል እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

ደም መለገስን በተመለከተ የማኅበረሰቡ አመለካከት እየተቀየረ እንደሆነ የመሰከሩት ዳይሬክተሩ፣ ከ120 ሺሕ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርቶችን በመስጠት ለውጥ ማምጣት እንደተቻለ ተናግረዋል፡፡ እነዚህ ግለሰቦች ከመንግሥት ተቋማት፣ ከግል ተቋማት፣ ከጤና ተቋማት፣ ከሃይማኖት ተቋማት፣ ከዩኒቨርሲቲዎችና ከኮሌጆች የተውጣጡ ናቸው፡፡

አገሪቷ በ350 እና በ450 ሚሊ ሊትር የሚለኩ 850 ሺሕ ከረጢት ደም በዓመት ያስፈልጋታል፡፡ ይሁንና እስከ ዛሬ ድረስ ማሳካት የተቻለው ከ85 እስከ 86 ሺሕ ከረጢት ብቻ ነው፡፡ ለዚህም እንደ ምክንያት የሚጠቀሰው የበጐ ፈቃደኞች አለመበራከት ነው፡፡ በአገር አቀፍ ደረጃ 850 ሺሕ የደም ከረጢት ቢያስፈልግም ደምን በቋሚነት የሚለግሱ በጎ ፈቃደኞች ግን ሦስት ሺሕ ብቻ ናቸው፡፡ አንድ ሰው አንዴ ደም ከለገሰ በኋላ ድጋሚ መለገስ የሚችለው ከሦስት ወራት በኋላ ሲሆን አዲስ አበባ ብቻ በሥርዓቱ የሚስተናገዱ 50 ሺሕ በጐ ፈቃደኞች ያስፈልጓታል፡፡

ሌላው ምክንያት ደግሞ የ44 ዓመት ዕድሜ ያለው የደም ባንክ በስሩ ያሉት አጠቃላይ የደም ባንኮች ቁጥር 25 ብቻ መሆኑ ነው፡፡ ከእነዚህም ውስጥ ስምንት የሚሆኑት ሥራ የጀመሩት ገና ዘንድሮ መሆኑን ዶ/ር ዳንኤል ተናግረዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የኅብረተሰቡ ደም የመለገስ ልምድ እየተሻሻለ ቢመጣም በከፍተኛ ደረጃ አለማደጉ ተግዳሮት እንደሆነ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡

ባንኩ ከሚሰበስበው ደም ውስጥ ዘጠኝ በመቶ የሚሆነውን ያስወግዳል፡፡ ለዚህም ምክንያቱ ደግሞ የሄፒታይተስ ቢ፣ የሄፒታይተስ ሲ፣ የኤችአይቪና በቂጢኝ ኢንፌክሽኖች አማካይነት እንደሆነ ዶ/ር ዳንኤል ተናግረዋል፡፡

ከጥቂት ሳምንታት በፊት በተከበረው ‹‹የዓለም የደም ለጋሾች ቀን›› ላይ በአዲስ አበባ 1300፣ በባህርዳር 200፣ በመቀሌ 300፣ በድሬዳዋ 300 እንዲሁም በሌሎች ከተሞች ላይ ደም ከለጋሾች ተሰብስቧል፡፡ (ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Social Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule