• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሕገወጥ ደም ሻጮች የከሰሩበት

June 25, 2014 02:55 am by Editor Leave a Comment

ከአንድ ዓመት በፊት አንድ ህመምተኛ ለሚደረግለት ህክምና ደም የሚያስፈልገው ከሆነ፣ ቤተሰብ አሊያም ወዳጅ ዘመድ ምትክ ደም ሰጥቶለትና የሚያስፈልገው የደም አይነት ከደም ባንክ ወጥቶለት ይታከም ነበር፡፡

ይህ አሠራር ግን በርካቶች የሚያስፈልጋቸውን ደም በቀላሉ እንዳያገኙ የሚያደርግ ሆኖ ቆይቷል፡፡

ቤተሰብ አሊያም የታካሚው የቅርብ ወዳጆችም ‹‹ደም ለግሱና ደማችሁ ተተክቶ ለታካሚው ሌላ ደም ይሰጠው›› የሚለውን ሐሳብ ሲሰሙ ሃሳቡን ይሸሻሉ፣ ከልገሳው ያፈገፍጋሉ እንዲሁም ይፈራሉ፡፡ በዚህም ምክንያት ደማቸው ተወስዶ እምብዛም ጥቅም ላይ መዋል የማይችል ግለሰቦች በደላሎች አማካይነት  በሽያጭ ደም ይለግሳሉ፡፡ ደም ባንክ የእነዚህን ሰዎች ደም በምትክ ወስዶ ከባንኩ ለታካሚዎች ደም ቢሰጥም፣ በሕገወጥ መንገድ ተሸጦ ገቢ የተደረገው ደም ከሞላ ጎደል ይወገድ እንደነበር ባንኩ ይገልጻል፡፡

ይሁንና የዛሬ ዓመት ገደማ ብሔራዊ ደም ባንክ በጀመረው አዲስ አሠራር መሠረት፣ በመንግሥት የሕክምና ተቋም የሚታከሙ ግለሰቦች  የሚያስፈልጋቸው ደም አለምትክ እንዲሰጣቸው አድርጓል፡፡ ይህ መሆኑ ደግሞ በሕገወጥ መንገድ አላግባብ ደማቸውን የሚሸጡ ግለሰቦችን አስቀርቷል፡፡

‹‹የቤተሰብ ደም ተተክቶ ደም ይሰጥ በነበረበት ጊዜ ደላሎች ደም እየሸጡ ከአንድ ሺሕ እስከ ሁለት ሺሕ ብር ድረስ ይቀበሉ ነበር፡፡ ይህንን መረጃ እኛም ልክ እንደ ኅብረተሰቡ በወሬ ደረጃ ነበር የምንሰማው፡፡ ግለሰቦቹን ለመያዝ ከፖሊስ ጋር ተጣምረን ብንሠራም ሕገወጦቹን ማግኘት አልቻልንም ነበር፤›› ያሉት የብሔራዊ ደም ባንክ አገልግሎት ዳይሬክተር ዶ/ር ዳንኤል ገብረ ሚካኤል፣ በአሥራ አንድ ወር የሥራ አፈጻጸም ጊዜ ውስጥ የበጎ ፈቃደኞች ደም ልገሳ ከመቼውም በላይ ጨምሮ ሕገወጦቹ ከጨዋታ ውጪ እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡

ምትክ ደም መስጠት ከመቅረቱ በፊት ከበጎ ፈቃደኞች በዓመት የሚሰበሰበው ደም 30 በመቶ አይሞላም ነበር፡፡ ዶክተር ዳንኤል እንደሚሉት ይህ ዛሬ ተቀይሯል፡፡ ምትክ ደምን የማስቀረት ሥራ ሙሉ በሙሉ በመሳካቱ ባለፉት 11 ወራት በነበረው አፈጻጸም በአገር አቀፍ ደረጃ ከበጎ ፈቃደኞች የተሰበሰበው የደም ብዛትም 68 በመቶ ደርሷል፡፡ ቀሪውንም 32 በመቶ ደም ከበጎ ፈቃደኞቹ ለመሰብሰብም ቀላል እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

ደም መለገስን በተመለከተ የማኅበረሰቡ አመለካከት እየተቀየረ እንደሆነ የመሰከሩት ዳይሬክተሩ፣ ከ120 ሺሕ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርቶችን በመስጠት ለውጥ ማምጣት እንደተቻለ ተናግረዋል፡፡ እነዚህ ግለሰቦች ከመንግሥት ተቋማት፣ ከግል ተቋማት፣ ከጤና ተቋማት፣ ከሃይማኖት ተቋማት፣ ከዩኒቨርሲቲዎችና ከኮሌጆች የተውጣጡ ናቸው፡፡

አገሪቷ በ350 እና በ450 ሚሊ ሊትር የሚለኩ 850 ሺሕ ከረጢት ደም በዓመት ያስፈልጋታል፡፡ ይሁንና እስከ ዛሬ ድረስ ማሳካት የተቻለው ከ85 እስከ 86 ሺሕ ከረጢት ብቻ ነው፡፡ ለዚህም እንደ ምክንያት የሚጠቀሰው የበጐ ፈቃደኞች አለመበራከት ነው፡፡ በአገር አቀፍ ደረጃ 850 ሺሕ የደም ከረጢት ቢያስፈልግም ደምን በቋሚነት የሚለግሱ በጎ ፈቃደኞች ግን ሦስት ሺሕ ብቻ ናቸው፡፡ አንድ ሰው አንዴ ደም ከለገሰ በኋላ ድጋሚ መለገስ የሚችለው ከሦስት ወራት በኋላ ሲሆን አዲስ አበባ ብቻ በሥርዓቱ የሚስተናገዱ 50 ሺሕ በጐ ፈቃደኞች ያስፈልጓታል፡፡

ሌላው ምክንያት ደግሞ የ44 ዓመት ዕድሜ ያለው የደም ባንክ በስሩ ያሉት አጠቃላይ የደም ባንኮች ቁጥር 25 ብቻ መሆኑ ነው፡፡ ከእነዚህም ውስጥ ስምንት የሚሆኑት ሥራ የጀመሩት ገና ዘንድሮ መሆኑን ዶ/ር ዳንኤል ተናግረዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የኅብረተሰቡ ደም የመለገስ ልምድ እየተሻሻለ ቢመጣም በከፍተኛ ደረጃ አለማደጉ ተግዳሮት እንደሆነ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡

ባንኩ ከሚሰበስበው ደም ውስጥ ዘጠኝ በመቶ የሚሆነውን ያስወግዳል፡፡ ለዚህም ምክንያቱ ደግሞ የሄፒታይተስ ቢ፣ የሄፒታይተስ ሲ፣ የኤችአይቪና በቂጢኝ ኢንፌክሽኖች አማካይነት እንደሆነ ዶ/ር ዳንኤል ተናግረዋል፡፡

ከጥቂት ሳምንታት በፊት በተከበረው ‹‹የዓለም የደም ለጋሾች ቀን›› ላይ በአዲስ አበባ 1300፣ በባህርዳር 200፣ በመቀሌ 300፣ በድሬዳዋ 300 እንዲሁም በሌሎች ከተሞች ላይ ደም ከለጋሾች ተሰብስቧል፡፡ (ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Social Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule