• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሕገወጥ ደም ሻጮች የከሰሩበት

June 25, 2014 02:55 am by Editor Leave a Comment

ከአንድ ዓመት በፊት አንድ ህመምተኛ ለሚደረግለት ህክምና ደም የሚያስፈልገው ከሆነ፣ ቤተሰብ አሊያም ወዳጅ ዘመድ ምትክ ደም ሰጥቶለትና የሚያስፈልገው የደም አይነት ከደም ባንክ ወጥቶለት ይታከም ነበር፡፡

ይህ አሠራር ግን በርካቶች የሚያስፈልጋቸውን ደም በቀላሉ እንዳያገኙ የሚያደርግ ሆኖ ቆይቷል፡፡

ቤተሰብ አሊያም የታካሚው የቅርብ ወዳጆችም ‹‹ደም ለግሱና ደማችሁ ተተክቶ ለታካሚው ሌላ ደም ይሰጠው›› የሚለውን ሐሳብ ሲሰሙ ሃሳቡን ይሸሻሉ፣ ከልገሳው ያፈገፍጋሉ እንዲሁም ይፈራሉ፡፡ በዚህም ምክንያት ደማቸው ተወስዶ እምብዛም ጥቅም ላይ መዋል የማይችል ግለሰቦች በደላሎች አማካይነት  በሽያጭ ደም ይለግሳሉ፡፡ ደም ባንክ የእነዚህን ሰዎች ደም በምትክ ወስዶ ከባንኩ ለታካሚዎች ደም ቢሰጥም፣ በሕገወጥ መንገድ ተሸጦ ገቢ የተደረገው ደም ከሞላ ጎደል ይወገድ እንደነበር ባንኩ ይገልጻል፡፡

ይሁንና የዛሬ ዓመት ገደማ ብሔራዊ ደም ባንክ በጀመረው አዲስ አሠራር መሠረት፣ በመንግሥት የሕክምና ተቋም የሚታከሙ ግለሰቦች  የሚያስፈልጋቸው ደም አለምትክ እንዲሰጣቸው አድርጓል፡፡ ይህ መሆኑ ደግሞ በሕገወጥ መንገድ አላግባብ ደማቸውን የሚሸጡ ግለሰቦችን አስቀርቷል፡፡

‹‹የቤተሰብ ደም ተተክቶ ደም ይሰጥ በነበረበት ጊዜ ደላሎች ደም እየሸጡ ከአንድ ሺሕ እስከ ሁለት ሺሕ ብር ድረስ ይቀበሉ ነበር፡፡ ይህንን መረጃ እኛም ልክ እንደ ኅብረተሰቡ በወሬ ደረጃ ነበር የምንሰማው፡፡ ግለሰቦቹን ለመያዝ ከፖሊስ ጋር ተጣምረን ብንሠራም ሕገወጦቹን ማግኘት አልቻልንም ነበር፤›› ያሉት የብሔራዊ ደም ባንክ አገልግሎት ዳይሬክተር ዶ/ር ዳንኤል ገብረ ሚካኤል፣ በአሥራ አንድ ወር የሥራ አፈጻጸም ጊዜ ውስጥ የበጎ ፈቃደኞች ደም ልገሳ ከመቼውም በላይ ጨምሮ ሕገወጦቹ ከጨዋታ ውጪ እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡

ምትክ ደም መስጠት ከመቅረቱ በፊት ከበጎ ፈቃደኞች በዓመት የሚሰበሰበው ደም 30 በመቶ አይሞላም ነበር፡፡ ዶክተር ዳንኤል እንደሚሉት ይህ ዛሬ ተቀይሯል፡፡ ምትክ ደምን የማስቀረት ሥራ ሙሉ በሙሉ በመሳካቱ ባለፉት 11 ወራት በነበረው አፈጻጸም በአገር አቀፍ ደረጃ ከበጎ ፈቃደኞች የተሰበሰበው የደም ብዛትም 68 በመቶ ደርሷል፡፡ ቀሪውንም 32 በመቶ ደም ከበጎ ፈቃደኞቹ ለመሰብሰብም ቀላል እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

ደም መለገስን በተመለከተ የማኅበረሰቡ አመለካከት እየተቀየረ እንደሆነ የመሰከሩት ዳይሬክተሩ፣ ከ120 ሺሕ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርቶችን በመስጠት ለውጥ ማምጣት እንደተቻለ ተናግረዋል፡፡ እነዚህ ግለሰቦች ከመንግሥት ተቋማት፣ ከግል ተቋማት፣ ከጤና ተቋማት፣ ከሃይማኖት ተቋማት፣ ከዩኒቨርሲቲዎችና ከኮሌጆች የተውጣጡ ናቸው፡፡

አገሪቷ በ350 እና በ450 ሚሊ ሊትር የሚለኩ 850 ሺሕ ከረጢት ደም በዓመት ያስፈልጋታል፡፡ ይሁንና እስከ ዛሬ ድረስ ማሳካት የተቻለው ከ85 እስከ 86 ሺሕ ከረጢት ብቻ ነው፡፡ ለዚህም እንደ ምክንያት የሚጠቀሰው የበጐ ፈቃደኞች አለመበራከት ነው፡፡ በአገር አቀፍ ደረጃ 850 ሺሕ የደም ከረጢት ቢያስፈልግም ደምን በቋሚነት የሚለግሱ በጎ ፈቃደኞች ግን ሦስት ሺሕ ብቻ ናቸው፡፡ አንድ ሰው አንዴ ደም ከለገሰ በኋላ ድጋሚ መለገስ የሚችለው ከሦስት ወራት በኋላ ሲሆን አዲስ አበባ ብቻ በሥርዓቱ የሚስተናገዱ 50 ሺሕ በጐ ፈቃደኞች ያስፈልጓታል፡፡

ሌላው ምክንያት ደግሞ የ44 ዓመት ዕድሜ ያለው የደም ባንክ በስሩ ያሉት አጠቃላይ የደም ባንኮች ቁጥር 25 ብቻ መሆኑ ነው፡፡ ከእነዚህም ውስጥ ስምንት የሚሆኑት ሥራ የጀመሩት ገና ዘንድሮ መሆኑን ዶ/ር ዳንኤል ተናግረዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የኅብረተሰቡ ደም የመለገስ ልምድ እየተሻሻለ ቢመጣም በከፍተኛ ደረጃ አለማደጉ ተግዳሮት እንደሆነ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡

ባንኩ ከሚሰበስበው ደም ውስጥ ዘጠኝ በመቶ የሚሆነውን ያስወግዳል፡፡ ለዚህም ምክንያቱ ደግሞ የሄፒታይተስ ቢ፣ የሄፒታይተስ ሲ፣ የኤችአይቪና በቂጢኝ ኢንፌክሽኖች አማካይነት እንደሆነ ዶ/ር ዳንኤል ተናግረዋል፡፡

ከጥቂት ሳምንታት በፊት በተከበረው ‹‹የዓለም የደም ለጋሾች ቀን›› ላይ በአዲስ አበባ 1300፣ በባህርዳር 200፣ በመቀሌ 300፣ በድሬዳዋ 300 እንዲሁም በሌሎች ከተሞች ላይ ደም ከለጋሾች ተሰብስቧል፡፡ (ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Social Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule