• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሕገወጥ ደም ሻጮች የከሰሩበት

June 25, 2014 02:55 am by Editor Leave a Comment

ከአንድ ዓመት በፊት አንድ ህመምተኛ ለሚደረግለት ህክምና ደም የሚያስፈልገው ከሆነ፣ ቤተሰብ አሊያም ወዳጅ ዘመድ ምትክ ደም ሰጥቶለትና የሚያስፈልገው የደም አይነት ከደም ባንክ ወጥቶለት ይታከም ነበር፡፡

ይህ አሠራር ግን በርካቶች የሚያስፈልጋቸውን ደም በቀላሉ እንዳያገኙ የሚያደርግ ሆኖ ቆይቷል፡፡

ቤተሰብ አሊያም የታካሚው የቅርብ ወዳጆችም ‹‹ደም ለግሱና ደማችሁ ተተክቶ ለታካሚው ሌላ ደም ይሰጠው›› የሚለውን ሐሳብ ሲሰሙ ሃሳቡን ይሸሻሉ፣ ከልገሳው ያፈገፍጋሉ እንዲሁም ይፈራሉ፡፡ በዚህም ምክንያት ደማቸው ተወስዶ እምብዛም ጥቅም ላይ መዋል የማይችል ግለሰቦች በደላሎች አማካይነት  በሽያጭ ደም ይለግሳሉ፡፡ ደም ባንክ የእነዚህን ሰዎች ደም በምትክ ወስዶ ከባንኩ ለታካሚዎች ደም ቢሰጥም፣ በሕገወጥ መንገድ ተሸጦ ገቢ የተደረገው ደም ከሞላ ጎደል ይወገድ እንደነበር ባንኩ ይገልጻል፡፡

ይሁንና የዛሬ ዓመት ገደማ ብሔራዊ ደም ባንክ በጀመረው አዲስ አሠራር መሠረት፣ በመንግሥት የሕክምና ተቋም የሚታከሙ ግለሰቦች  የሚያስፈልጋቸው ደም አለምትክ እንዲሰጣቸው አድርጓል፡፡ ይህ መሆኑ ደግሞ በሕገወጥ መንገድ አላግባብ ደማቸውን የሚሸጡ ግለሰቦችን አስቀርቷል፡፡

‹‹የቤተሰብ ደም ተተክቶ ደም ይሰጥ በነበረበት ጊዜ ደላሎች ደም እየሸጡ ከአንድ ሺሕ እስከ ሁለት ሺሕ ብር ድረስ ይቀበሉ ነበር፡፡ ይህንን መረጃ እኛም ልክ እንደ ኅብረተሰቡ በወሬ ደረጃ ነበር የምንሰማው፡፡ ግለሰቦቹን ለመያዝ ከፖሊስ ጋር ተጣምረን ብንሠራም ሕገወጦቹን ማግኘት አልቻልንም ነበር፤›› ያሉት የብሔራዊ ደም ባንክ አገልግሎት ዳይሬክተር ዶ/ር ዳንኤል ገብረ ሚካኤል፣ በአሥራ አንድ ወር የሥራ አፈጻጸም ጊዜ ውስጥ የበጎ ፈቃደኞች ደም ልገሳ ከመቼውም በላይ ጨምሮ ሕገወጦቹ ከጨዋታ ውጪ እንደሆኑ ተናግረዋል፡፡

ምትክ ደም መስጠት ከመቅረቱ በፊት ከበጎ ፈቃደኞች በዓመት የሚሰበሰበው ደም 30 በመቶ አይሞላም ነበር፡፡ ዶክተር ዳንኤል እንደሚሉት ይህ ዛሬ ተቀይሯል፡፡ ምትክ ደምን የማስቀረት ሥራ ሙሉ በሙሉ በመሳካቱ ባለፉት 11 ወራት በነበረው አፈጻጸም በአገር አቀፍ ደረጃ ከበጎ ፈቃደኞች የተሰበሰበው የደም ብዛትም 68 በመቶ ደርሷል፡፡ ቀሪውንም 32 በመቶ ደም ከበጎ ፈቃደኞቹ ለመሰብሰብም ቀላል እንደሆነ ተናግረዋል፡፡

ደም መለገስን በተመለከተ የማኅበረሰቡ አመለካከት እየተቀየረ እንደሆነ የመሰከሩት ዳይሬክተሩ፣ ከ120 ሺሕ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርቶችን በመስጠት ለውጥ ማምጣት እንደተቻለ ተናግረዋል፡፡ እነዚህ ግለሰቦች ከመንግሥት ተቋማት፣ ከግል ተቋማት፣ ከጤና ተቋማት፣ ከሃይማኖት ተቋማት፣ ከዩኒቨርሲቲዎችና ከኮሌጆች የተውጣጡ ናቸው፡፡

አገሪቷ በ350 እና በ450 ሚሊ ሊትር የሚለኩ 850 ሺሕ ከረጢት ደም በዓመት ያስፈልጋታል፡፡ ይሁንና እስከ ዛሬ ድረስ ማሳካት የተቻለው ከ85 እስከ 86 ሺሕ ከረጢት ብቻ ነው፡፡ ለዚህም እንደ ምክንያት የሚጠቀሰው የበጐ ፈቃደኞች አለመበራከት ነው፡፡ በአገር አቀፍ ደረጃ 850 ሺሕ የደም ከረጢት ቢያስፈልግም ደምን በቋሚነት የሚለግሱ በጎ ፈቃደኞች ግን ሦስት ሺሕ ብቻ ናቸው፡፡ አንድ ሰው አንዴ ደም ከለገሰ በኋላ ድጋሚ መለገስ የሚችለው ከሦስት ወራት በኋላ ሲሆን አዲስ አበባ ብቻ በሥርዓቱ የሚስተናገዱ 50 ሺሕ በጐ ፈቃደኞች ያስፈልጓታል፡፡

ሌላው ምክንያት ደግሞ የ44 ዓመት ዕድሜ ያለው የደም ባንክ በስሩ ያሉት አጠቃላይ የደም ባንኮች ቁጥር 25 ብቻ መሆኑ ነው፡፡ ከእነዚህም ውስጥ ስምንት የሚሆኑት ሥራ የጀመሩት ገና ዘንድሮ መሆኑን ዶ/ር ዳንኤል ተናግረዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የኅብረተሰቡ ደም የመለገስ ልምድ እየተሻሻለ ቢመጣም በከፍተኛ ደረጃ አለማደጉ ተግዳሮት እንደሆነ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡

ባንኩ ከሚሰበስበው ደም ውስጥ ዘጠኝ በመቶ የሚሆነውን ያስወግዳል፡፡ ለዚህም ምክንያቱ ደግሞ የሄፒታይተስ ቢ፣ የሄፒታይተስ ሲ፣ የኤችአይቪና በቂጢኝ ኢንፌክሽኖች አማካይነት እንደሆነ ዶ/ር ዳንኤል ተናግረዋል፡፡

ከጥቂት ሳምንታት በፊት በተከበረው ‹‹የዓለም የደም ለጋሾች ቀን›› ላይ በአዲስ አበባ 1300፣ በባህርዳር 200፣ በመቀሌ 300፣ በድሬዳዋ 300 እንዲሁም በሌሎች ከተሞች ላይ ደም ከለጋሾች ተሰብስቧል፡፡ (ሪፖርተር)

Filed Under: Social Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule