• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሽልማቱን የምቀበለው በአጋሬና የሰላም ጓድ በኾኑት ፕሬዚደንት ኢሣያስ አፈወርቂ ስም ነው” የኖቤል የሰላም ሎሬት ጠ/ሚ/ር ዐቢይ

December 10, 2019 04:27 pm by Editor Leave a Comment

ጠቅላይ ሚንሥትር ዐቢይ አህመድ የዓለም የሰላም ኖቤል ሽልማታቸውን ሲቀበሉ ባደረጉት ንግግር ፕሬዚደንት ኢሣያያስ አፈወርቂ አወደሱ። «ይኽን ሽልማት የምቀበለው በኢትዮጵያውያን እና ኤርትራውያን ስም ነው። በተለይ ደግሞ ለሰላም ሲሉ ከፍተኛውን መስዋእትነት በከፈሉት ስም። በተመሳሳይ ሽልማቱን የምቀበለው በአጋሬና የሰላም ጓድ በኾኑት ፕሬዚደንት ኢሣያያስ አፈወርቂ ስም ነው» ብለዋል። ይኽ ንግግራቸውም ከታዳሚያን ሞቅ ያለጭብጨባ ታጅቧል። የፕሬዚደንት ኢሣያያስ አፈወርቂ «መልካም ፈቃድ፣ እምነት እና ቁርጠኝነት ለኹለት ዐስርተ-ዓመታት በሃገሮቻችን መካከል የዘለቀው መቆራረጥ እንዲያበቃ ወሳኝ ነበር።»  

በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ጦርነቱ ሲከፈት ወጣት እንደነበሩ የተናገሩት ጠቅላይ ሚንሥትር ዐቢይ አህመድ፦ በጦርነት አውድማ  «ወንድም ወንድሙን ሲገድል» መመልከታቸውን ገልጠዋል። የጦርነት መራራ ገጽታን፤ የሰላምን ወሳኝነት አጉልተው ተናግረዋል። በኢትዮጵያ እና ኤርትራ ጦርነት የተነሳ ለኹለት ዐሥርተ-ዓመታት ተለያይተው የነበሩ ቤተሰቦች መገናኘታቸውን፤ «ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሙሉ በሙሉ እንደ አዲስ መጀመሩንም» ጠቅሰዋል። የአየር እና የቴሌኮሙኒኬሽን ግንኙነት በኹለቱ ሃገራት መጀመሩንም በንግግራቸው አሰምተዋል።  

«በአኹኑ ወቅት ትኩረታችን የጋራ መሠረተ-ልማትን ማጎልበት ላይ ነው» ብለዋል። ይኽም የሃገራቱ የምጣኔ ሐብት ትልም መኾኑን አጽንዖት ሰጥተውበታል። ስለመደመር አስተሳሰባቸውም ለታዳሚያኑ ገለጣ አድርገዋል። በአማርኛም፦ «በሰላም እንድታድር ጎረቤትህ ሰላም ይደር» እንላለን ሲሉ ታዳሚያን በጭ ብጫባ አጅበዋቸዋል። አባባሉን በኦሮሚኛ ሲደግሙት ከአዳራሹ ዳግም ጭብጨባ ታጅበው ነበር። ይኽ አባባል አብዛኛው የአፍሪቃ ሃገራት የሚጋሩት መኾኑንም ጠቅሰዋል።ይኽ ምሳሌያዊ አባባል በቃጣናው ሃገራትን ትብብ ትብብርን ለማጠናከር መሪ ነው ብለዋል። 

የአፍሪቃ ቀንድ የሰላም እና የብልጽግና ማዕከል ኾኖ በሌሎች አፍሪቃ ሃገራት በአብነትነት ሲወሰድ ማየት ትልማቸው እንደኾነ ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚንሥትር ዐቢይ፦ “ሁሉንም የፖለቲካ እስረኞች ፈትተናል፤ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት የሚፈጸሙባቸው ማሰቃያዎችን ዘግተናል” ብለዋል። ኢትዮጵያ ውስጥ “የታሰረ ጋዜጠኛ የለም” ሲሉም አክለዋል። “ለእውነተኛ መድብለ ፓርቲ ዲሞክራሲ መሰረቱን አደላድለናል በቅርቡም ነጻ እና ፍትኃዊ ምርጫን እናካሂዳለን” የጽንፈኝነትን እና የከፋፋይነትን መንገድ ማስወገድ እንደሚገባም ተናግረዋል። በማጠቃለያቸውም በአፍሪቃ ቀንድ ሰላም እና ብልጽግናን ለማስፈን የ«መደመር» አስተሳሰባቸውን ዓለም አአፉ ማኅበረሰብ እንዲቀላቀል ጥሪ አስተላልፈዋል። «ሰላም ለሁላችን» ሲሉም በአማርኛ እና ኦሮሚኛ ተናግረው ረዘም ያለ ንግግራቸውን ቋጭተዋል።

(DW)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Left Column, Nobel Peace Prize Laureate Abiy Ahmed Ali

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am
  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule