• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በአርሲ ጅብ በሰውና የቤት እንስሳት ላይ ጉዳት አደረሰ

February 23, 2015 08:21 am by Editor Leave a Comment

በኦሮሚያ ክልል በአርሲ ዞን በሌሙና- ቢልቢሎ ወረዳ ሌሊት ላይ መኖሪያ ቤት የገባ አንድ ጅብ በሰውና በቤት እንስሳት ላይ ጉዳት ማድረሱን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያ ኢንስፔክተር ጎሳ አማን እንደገለጹት፥ ጅቡ በሰውና እንስሳት ላይ ጥቃት ያደረሰው በሌሙዲማና ሁላሃሳ የገጠር ቀበሌ ነው።

የካቲት 10 ቀን 2007 ከሌሊቱ 10 እስከ 11 ሰዓት በሁለት አርሶ አደሮች የእንስሳት በረትና መኖሪያ ግቢ በመግባት በሁለት አባወራና ስምንት የቤት እንስሳት ላይ ንክሻ መፈጸሙን ገልጸዋል።

አርሶ አደሮቹ የቤት እንስሳቱን ከጅቡ ለማስጣል በገጠሙት ግብ ግብ የተደናገጠው ጅብ ወደ ጭላሎ ተራራ ሊያመልጥ መቻሉን አስታውቀዋል።

ከአርሶ አደሮቹ መካከል አንደኛው ብልታቸው ላይ ሌላው አርሶ አደር ደግሞ በሆዳቸውና ሌላ አካላቸው ላይ በደረሰባቸው ጉዳት አሰላ ሆስፒታል ህክምና በመከታተል ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

ከቤት እንስሳቱ መካከል አራቱ በደረሰባቸው ጉዳት ወዲያውኑ ሲሞቱ፥ ቀሪዎቹ ህክምና ተደርጎላቸው በማገገም ላይ ይገኛሉ ብለዋል።

እንዲሁም በዚሁ የገጠር ሁላሃሳ ቀበሌ ትናንት ከምሽቱ ሁለት ሰአት አካባቢ አንድ ጅብ በአንድ አርሶ አደር መኖሪያ ግቢ በመግባት ተመሳሳይ ጉዳት ማድረሱን ኢንስፔክተር ጎሳ አማን ገልጸዋል።

በእንስሳቱ በረት ጅብ መግባቱን የሰሙት አርሶ አደር መሐመድ አማን ከበረት አባረው ሲያስወጡት መኖሪያ ቤት በመግባት በባለቤታቸው፣ የሁለት ወር ሕጻናን ጭምሮ በሦስት ልጆቻቸውና ሁለት ጎረቤቶቻቸው ላይ ጥቃት መፈጸሙን አስታውቀዋል።

አባወራው ጅቡን በስለትና ዱላ ደብድበው እንደገደሉት አስታውቀው፥ ከፍተኛና መካከለኛ ጉዳት የደረሰባቸው ስድሰቱ ሰዎች አሰላ ሆስፒታል ገብተው ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑን ገልጸዋል።

የአርሲ ዞን እንስሳት ሀብት ልማትና ጤና ጥበቃ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ዶክተር አብዲ ዩሱፍ በሰጡት አስተያየት የዱር እንስሳት መጠለያ የሆነው ደን ከተመናመነ ወዲህ የዱር እንስሳት ወደ ሰዎች መኖሪያ አካባቢ የመምጣቱ ሁኔታ የተለመደ ነው ማለታቸውን ኢዜአ ዘግቧል። [አዲስ አበባ፣ የካቲት 14፣ 2007 (ኤፍ.ቢ.ሲ)]

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule