
ከአዘጋጆቹ፤ባለፈው ጊዜ “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፲” በሚል ለቀረበው ምላሽ በድረገጻችን በመላክና በፌስቡክ ላይ በመለጠፍ የተሳተፋችሁትን በሙሉ እናመሰግናለን፡፡ በተለይ በግጥም ምላሻችሁን ለሰጣችሁ በሙሉ ከፍያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ የቅንብሩ አዘጋጅ ወለላዬ በቁጥር አስር ለቀረበው ጥያቄ ምላሻቸውን በሚከተለው መልኩ በግጥም አስፍረዋል፡፡ (እንደተለመደው በየሳምንቱ መልሱን ተከታትለን ባለማቅረባችን ለአንባቢያን ታላቅ ይቅርታ እንጠይቃለን::)
መልስ
እኔ ነኝ፣ እኔ ነኝ፣ – እኔ ነኝ ተዘራ
የማስደስታችሁ – ከክራሬ ጋራ
ብለው የዘፈኑ – በገዛ ስማቸው
ድምጻዊ ተዘራ – ማለት እኚህ ናቸው
ላሁኑ ደግሞ “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፲፩” ወለላዬ የሚከተለውን አቅርበዋል፡፡ ምላሻችሁን በግጥም በመመለስ ለዝግጅቱ ውበት እንድትሰጡ ለማደፋፈር እንወዳለን፡፡ በሚቀጥለው መልሱን በግጥም እናቀርባለን፡፡
ጥያቄ
ዝርዝሩ ሲወጣ – ጀግኖች ሲቆጠሩ
አንደኛው አንበሳ – እኚህ ሰው ነበሩ
እንዲህ የገነነው – ሲጠራ ስማቸው
በምን ምክንያት ነው – ንገሩኝ ማናቸው?
መድፍና ጠመንጃ ጥይት ሲጉዋረሱ
አሳላፊ ነበር የማሩ ገረሱ።
የተባለላቸው ደጃዝማች ገረሱ ዹኪ የሸዋ አርበኛ የነበሩ ናቸው።
ከአዋሽ እስከ ጊቤ ጣሊያንና ባንዳን መቆሚያ መቀመጫ ያሳጣቸው። በቆራ፡ በዳዎ፡ በገፈርሳ፡ በጭቱ፡ በወሊሶ አካባቢ ጣሊያንና ባንዳን የረፈረፋ ጀግና አርበኛ ነው። ብዙ ሺህ የገበሬ ጦር ይዞ ከወራሪ የኢጣሊያ ፋሽት ጋር ሲታገል የቆቀ። ተፈሪ (ሀይለ ስላሴ) በእንግሊዞች ተጭኖ ፊንፍኔ (አዲስ አበባ) ሲገባ እንደ ሌሎች አርበኞች ሄዶ ያልሰገዳለት፡ ነገር ግን ሀይለ ስላሴ በዚህ ጉዳይ ደንግጦ አርባኛው ባለበት አመያ አካባቢ ግንዶ መንደር ላይ በእንግሊዞች ወተደር ታጂቦ ለአርበኛው ሰገዳለት። የመሻንገያ ሹመትም “ፊታውራሪ” አለው። ሽጉጡንም ሸለማው። ከዚያ በሁዋላ አርበኛው ወዳ ጂማና ኢሉ አባቦር የተሰባሰባውን የጠሊያንና ባንዳ ጦር ለመደምሰስ ጊቤን ተሸግሮ ቃላመሃለውን ፈጸመ።ከጊቤ እስክ ጎሬ ያለውን ጠላት ድምስሶ ምርኮኛውን ለዘመዶቹ ነጭ እንግሊዞች አስረክቦ። የጦር መሳሪያውን ለራሱ አደረገ። ከነጻነት በሁዋላ ቃል የተገባለት የጦር አባጋዝነት ሁሉ ተሰርዞ ፊታውራሪነት ወዳ ቀኛዝማችነት ወርዶ አርባኛው በአጼውና በጸሐፊ ትዕዛዜ እንደ ውሃ በቀጠነ ትዕዛዝ የቁም እስር ተፈረዳበት። ከቦታ ቦታ ከግዞትነት በማያንስ መልኩ ሹመት ተብዬው ስራ ተሰጠው።
በሁዋላ ላይ ደግሞ ወደ ፊንፍኔ በመመለስ በሃይለ ስላሴ ነጭ ለባሾች እይታ ስር ሆኖ እስክ እለተ ሞቱ ድረስ በቁም እስርነት ኖረ።
ይህ ጀግና አርበኛ ደጃዝማች ገረሱ ዱኪ ደብሱ (Garasuu Dhukii Dhabsuu Akkee Lubee)የፈረሱ ስም ኣባ ቦራ ይባላል።
ትውልድ ቦታው ካሮ (Kaarroo) የሚባል በወሊሲ አካባቢ ነው። መኖሪያ ቤቱን ሰርቶ የነበረው ጨፎ የሚባል ቦታ ሲሆን ከሞተም በሁዋላ በዚሁ ቦታ እራሱ ባሰራው ጨፎ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ተቀበረ።
ስለ ኢትዮጵያ አርበኞች ሲነሳ፡ ብዙ ጊዜ ንጉሱና ጀሌዎቹ የፈጸሙበት ግፍ ሲገልጹ በሚከተለው መልኩ ነበር
“ኢትዮጵያ ሀገሬ ሞኝ ነሽ ተላላ፡ የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ በላ።” ይባል ነበር።
የሰው ልጅ በሕይወት ያሳለፈው ኑሮ
የውጣ ውረዱ በታሪክ ላይ ሰፍሮ
ለሌሎች ምሣሌ እንዲሆን መማሪያ
በፅሁፍ ይሰፍራል ለትውልድም መኩሪያ
የዚሕ ዓይነቱ ዕድል የዚሕ አይነት ዕጣ
ክብሩን ተሸካሚ ከልኩ ሳይወጣ
ምንም ሳይቀነስ ኣልያም ሳይለጠጥ
የክብር ሥራቸው ከጃችን ሳያመልጥ
ከቶ አከራካሪ ወይም ግራ አጋቢ
ያልሆኑት እኝህ ሰው በውጭም በግቢ
ኮርተው ያኮሩንን ስዎች ስናነሳ
ደጃዝማች ገርሱ የኢትዮጵያ አንበሳ
ሞተው ላገራቸው በዱር በገደሉ
የውጭ ወራሪውን መክቶ በግሉ
በሌለ መሣሪያ ትጥቅ ሳይሙዋላ
በአገር ፍቅር ስሜት በዕምነት በመላ
የገበሬ ጦሩ ተዋጊ በፈረስ
ኣደራጅቶ መርቶ ወራሪን መደምሰስ
ያስተማረን መክፈል ላገር መሥዋዕትነት
ማን እንደ ገረሱ ለኢትዮጵያ በሕይወት »
ገድላቸውን ሰምተን ፍቅር ላገራችው
በታሪክ ተፅፎ እንዳነበብናችው
ተረት በምሳሌ ከሰዎችም ሰምተን
ጀግኖች የነሳሉ ጊዜ ሳይወሰን
አድንቀን ተገርመን ስማቸው ሳይቀረን
የትውልድ ቦታ የዕድሚያቸውን ዘመን
ሁሉንም ጠንቅቀን ካወቅን በሁዋላ
ፎቶዋቸውን ስናይ ሆነ የተሟላ
ታሪክ ትርጉም ሲያገኝ ገፅታ ተላብሶ
ከፊታችን ሲቆም ሕልውና ቀምሶ
ትጥቁም እየታይ ከነጎፈሪያቸው
ማሥባሉ አይቀርም ለካስ እኝህ ናቸው
እኔም አላውቅም
እናንተው ንገሩኝ
ታሪኩን ሥራውን በደንብ አብራሩልኝ
ብዙ ማላውቃቸው ጀግኖች ስላሉ
ከነርሱ መካከል አንዱ ይሆናሉ
ግምባሩን ኮስኩሶ እንደንብ አስፈሪ
ጠመንጃውን ታጥቆ ጠላት አሳፋሪ
ግርማ ሞገሳቸው እጅጉን አስፈሪ
ስማቸው ግን ጠፋኝ እኚህ ፊት አውራሪ
አልገዛም ብሎ ለፋሽስት ወራሪ
ለህዝቡ የቆመ አገሩን አክባሪ
ከሊማሊሞ ገደል እስከ አርማጭሆ ድንበር
በዱር በገደሉ ጠላትን ሲያሸብር
የጣልያኑ ዘማች የሰሜኑ አርበኛ
የውብነህ ልጅ አሞራው በለኛ
ግራ ተጋብቶኛል ማን እንደሆነ እሱ
እኔ አላወኩትም ይነገረኝ መልሱ
የርሻ ሚኒስትሩን
ደጅ አዝማች ታከለን
ተክለ ሃዋሪያን
ይመስላል ፎቶዋቸው
እንደው ግምቴ ነው
ካልሆኑ እርሳቸው
እስቲ ጎበዝ መልስ እኝህ ሰው ማናቸው?
ጀግናዉ በላይ ዘለቀ – የጎጃሙጀግና
ስምህ ይወደሳል ዛሬምእንደገና!
ጅግና የወለደው የጅግና ልጅ
መሸሽ የማያውቀው ይሞታታል እንጂ
በላይ ዘለቀ ነው የኢትዮጵያ ልጅ
ዝርዝሩ ሲወጣ ጀግኖች ሲቆጠሩ
ይሄ ሰውየማ ባሻ ቅጣው እንዳይሆኑ
ያበላይ ዘለቀ የጭንጫው በርበሬ
ጠላት ተሸበረ እየሠማ ወሬ
የዱሩ ደጅ አዝማች የከተማው ደሃ፥
ያበላይ ዘለቀ ታላቁ ዝሆን
ጦር መጣልህ በሉት ይነሣ እንደሆን
ምንጭ ከህዝብ
ኣትቀስቅስልኝ የት ኣገኘሁህና
በነዚህ ሲነሳ ልቤ ይረበሻል ስራየም ይህ ነውና
ለካ ለዚህ ነበር እዳስታውሰው የቀሰቀስከኝ
ጀግንነት ከምሬት ተደበላልቆብኝ
እርር እያልኩኝ እምባየ እየተናነቀኝ
ጀግንነቱ ከነብሴ ተዋህዶ ህያውነት ዘራልኝ
ባንዳዎች በዙ እንጂ ወንድነቱም ቀሰቀሰኝ
ለነጋሪ ብቆይም እግዝሔር ሃጥያቱን ይቅልልልኝ።