ከአዘጋጆቹ፤ባለፈው ጊዜ “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፲” በሚል ለቀረበው ምላሽ በድረገጻችን በመላክና በፌስቡክ ላይ በመለጠፍ የተሳተፋችሁትን በሙሉ እናመሰግናለን፡፡ በተለይ በግጥም ምላሻችሁን ለሰጣችሁ በሙሉ ከፍያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ የቅንብሩ አዘጋጅ ወለላዬ በቁጥር አስር ለቀረበው ጥያቄ ምላሻቸውን በሚከተለው መልኩ በግጥም አስፍረዋል፡፡ (እንደተለመደው በየሳምንቱ መልሱን ተከታትለን ባለማቅረባችን ለአንባቢያን ታላቅ ይቅርታ እንጠይቃለን::)
መልስ
እኔ ነኝ፣ እኔ ነኝ፣ – እኔ ነኝ ተዘራ
የማስደስታችሁ – ከክራሬ ጋራ
ብለው የዘፈኑ – በገዛ ስማቸው
ድምጻዊ ተዘራ – ማለት እኚህ ናቸው
ላሁኑ ደግሞ “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፲፩” ወለላዬ የሚከተለውን አቅርበዋል፡፡ ምላሻችሁን በግጥም በመመለስ ለዝግጅቱ ውበት እንድትሰጡ ለማደፋፈር እንወዳለን፡፡ በሚቀጥለው መልሱን በግጥም እናቀርባለን፡፡
ጥያቄ
ዝርዝሩ ሲወጣ – ጀግኖች ሲቆጠሩ
አንደኛው አንበሳ – እኚህ ሰው ነበሩ
እንዲህ የገነነው – ሲጠራ ስማቸው
በምን ምክንያት ነው – ንገሩኝ ማናቸው?
dereje Mengesha says
መድፍና ጠመንጃ ጥይት ሲጉዋረሱ
አሳላፊ ነበር የማሩ ገረሱ።
የተባለላቸው ደጃዝማች ገረሱ ዹኪ የሸዋ አርበኛ የነበሩ ናቸው።
Qaalluu says
ከአዋሽ እስከ ጊቤ ጣሊያንና ባንዳን መቆሚያ መቀመጫ ያሳጣቸው። በቆራ፡ በዳዎ፡ በገፈርሳ፡ በጭቱ፡ በወሊሶ አካባቢ ጣሊያንና ባንዳን የረፈረፋ ጀግና አርበኛ ነው። ብዙ ሺህ የገበሬ ጦር ይዞ ከወራሪ የኢጣሊያ ፋሽት ጋር ሲታገል የቆቀ። ተፈሪ (ሀይለ ስላሴ) በእንግሊዞች ተጭኖ ፊንፍኔ (አዲስ አበባ) ሲገባ እንደ ሌሎች አርበኞች ሄዶ ያልሰገዳለት፡ ነገር ግን ሀይለ ስላሴ በዚህ ጉዳይ ደንግጦ አርባኛው ባለበት አመያ አካባቢ ግንዶ መንደር ላይ በእንግሊዞች ወተደር ታጂቦ ለአርበኛው ሰገዳለት። የመሻንገያ ሹመትም “ፊታውራሪ” አለው። ሽጉጡንም ሸለማው። ከዚያ በሁዋላ አርበኛው ወዳ ጂማና ኢሉ አባቦር የተሰባሰባውን የጠሊያንና ባንዳ ጦር ለመደምሰስ ጊቤን ተሸግሮ ቃላመሃለውን ፈጸመ።ከጊቤ እስክ ጎሬ ያለውን ጠላት ድምስሶ ምርኮኛውን ለዘመዶቹ ነጭ እንግሊዞች አስረክቦ። የጦር መሳሪያውን ለራሱ አደረገ። ከነጻነት በሁዋላ ቃል የተገባለት የጦር አባጋዝነት ሁሉ ተሰርዞ ፊታውራሪነት ወዳ ቀኛዝማችነት ወርዶ አርባኛው በአጼውና በጸሐፊ ትዕዛዜ እንደ ውሃ በቀጠነ ትዕዛዝ የቁም እስር ተፈረዳበት። ከቦታ ቦታ ከግዞትነት በማያንስ መልኩ ሹመት ተብዬው ስራ ተሰጠው።
በሁዋላ ላይ ደግሞ ወደ ፊንፍኔ በመመለስ በሃይለ ስላሴ ነጭ ለባሾች እይታ ስር ሆኖ እስክ እለተ ሞቱ ድረስ በቁም እስርነት ኖረ።
ይህ ጀግና አርበኛ ደጃዝማች ገረሱ ዱኪ ደብሱ (Garasuu Dhukii Dhabsuu Akkee Lubee)የፈረሱ ስም ኣባ ቦራ ይባላል።
ትውልድ ቦታው ካሮ (Kaarroo) የሚባል በወሊሲ አካባቢ ነው። መኖሪያ ቤቱን ሰርቶ የነበረው ጨፎ የሚባል ቦታ ሲሆን ከሞተም በሁዋላ በዚሁ ቦታ እራሱ ባሰራው ጨፎ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ተቀበረ።
ስለ ኢትዮጵያ አርበኞች ሲነሳ፡ ብዙ ጊዜ ንጉሱና ጀሌዎቹ የፈጸሙበት ግፍ ሲገልጹ በሚከተለው መልኩ ነበር
“ኢትዮጵያ ሀገሬ ሞኝ ነሽ ተላላ፡ የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ በላ።” ይባል ነበር።
Bombu says
የሰው ልጅ በሕይወት ያሳለፈው ኑሮ
የውጣ ውረዱ በታሪክ ላይ ሰፍሮ
ለሌሎች ምሣሌ እንዲሆን መማሪያ
በፅሁፍ ይሰፍራል ለትውልድም መኩሪያ
የዚሕ ዓይነቱ ዕድል የዚሕ አይነት ዕጣ
ክብሩን ተሸካሚ ከልኩ ሳይወጣ
ምንም ሳይቀነስ ኣልያም ሳይለጠጥ
የክብር ሥራቸው ከጃችን ሳያመልጥ
ከቶ አከራካሪ ወይም ግራ አጋቢ
ያልሆኑት እኝህ ሰው በውጭም በግቢ
ኮርተው ያኮሩንን ስዎች ስናነሳ
ደጃዝማች ገርሱ የኢትዮጵያ አንበሳ
ሞተው ላገራቸው በዱር በገደሉ
የውጭ ወራሪውን መክቶ በግሉ
በሌለ መሣሪያ ትጥቅ ሳይሙዋላ
በአገር ፍቅር ስሜት በዕምነት በመላ
የገበሬ ጦሩ ተዋጊ በፈረስ
ኣደራጅቶ መርቶ ወራሪን መደምሰስ
ያስተማረን መክፈል ላገር መሥዋዕትነት
ማን እንደ ገረሱ ለኢትዮጵያ በሕይወት »
bombu says
ገድላቸውን ሰምተን ፍቅር ላገራችው
በታሪክ ተፅፎ እንዳነበብናችው
ተረት በምሳሌ ከሰዎችም ሰምተን
ጀግኖች የነሳሉ ጊዜ ሳይወሰን
አድንቀን ተገርመን ስማቸው ሳይቀረን
የትውልድ ቦታ የዕድሚያቸውን ዘመን
ሁሉንም ጠንቅቀን ካወቅን በሁዋላ
ፎቶዋቸውን ስናይ ሆነ የተሟላ
ታሪክ ትርጉም ሲያገኝ ገፅታ ተላብሶ
ከፊታችን ሲቆም ሕልውና ቀምሶ
ትጥቁም እየታይ ከነጎፈሪያቸው
ማሥባሉ አይቀርም ለካስ እኝህ ናቸው
Ras Ja says
እኔም አላውቅም
እናንተው ንገሩኝ
ታሪኩን ሥራውን በደንብ አብራሩልኝ
ብዙ ማላውቃቸው ጀግኖች ስላሉ
ከነርሱ መካከል አንዱ ይሆናሉ
Amsayaw Atnafu says
ግምባሩን ኮስኩሶ እንደንብ አስፈሪ
ጠመንጃውን ታጥቆ ጠላት አሳፋሪ
ግርማ ሞገሳቸው እጅጉን አስፈሪ
ስማቸው ግን ጠፋኝ እኚህ ፊት አውራሪ
Gadafi Derbew says
አልገዛም ብሎ ለፋሽስት ወራሪ
ለህዝቡ የቆመ አገሩን አክባሪ
ከሊማሊሞ ገደል እስከ አርማጭሆ ድንበር
በዱር በገደሉ ጠላትን ሲያሸብር
የጣልያኑ ዘማች የሰሜኑ አርበኛ
የውብነህ ልጅ አሞራው በለኛ
Seid Ebrahim says
ግራ ተጋብቶኛል ማን እንደሆነ እሱ
እኔ አላወኩትም ይነገረኝ መልሱ
Etsub Abebe says
የርሻ ሚኒስትሩን
ደጅ አዝማች ታከለን
ተክለ ሃዋሪያን
ይመስላል ፎቶዋቸው
እንደው ግምቴ ነው
ካልሆኑ እርሳቸው
እስቲ ጎበዝ መልስ እኝህ ሰው ማናቸው?
Melkamu Mehirete says
ጀግናዉ በላይ ዘለቀ – የጎጃሙጀግና
ስምህ ይወደሳል ዛሬምእንደገና!
Getamesay Bekele says
ጅግና የወለደው የጅግና ልጅ
መሸሽ የማያውቀው ይሞታታል እንጂ
በላይ ዘለቀ ነው የኢትዮጵያ ልጅ
Yeab Habesha Abebe says
ዝርዝሩ ሲወጣ ጀግኖች ሲቆጠሩ
ይሄ ሰውየማ ባሻ ቅጣው እንዳይሆኑ
Ephrem Nurye says
ያበላይ ዘለቀ የጭንጫው በርበሬ
ጠላት ተሸበረ እየሠማ ወሬ
የዱሩ ደጅ አዝማች የከተማው ደሃ፥
ያበላይ ዘለቀ ታላቁ ዝሆን
ጦር መጣልህ በሉት ይነሣ እንደሆን
ምንጭ ከህዝብ
ገብረየሱስ says
ኣትቀስቅስልኝ የት ኣገኘሁህና
በነዚህ ሲነሳ ልቤ ይረበሻል ስራየም ይህ ነውና
ገብረየሱስ says
ለካ ለዚህ ነበር እዳስታውሰው የቀሰቀስከኝ
ጀግንነት ከምሬት ተደበላልቆብኝ
እርር እያልኩኝ እምባየ እየተናነቀኝ
ጀግንነቱ ከነብሴ ተዋህዶ ህያውነት ዘራልኝ
ባንዳዎች በዙ እንጂ ወንድነቱም ቀሰቀሰኝ
ለነጋሪ ብቆይም እግዝሔር ሃጥያቱን ይቅልልልኝ።