• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እኚህ ሰው ማናቸው? – ፲፩

September 10, 2014 06:21 am by Editor 15 Comments

ከአዘጋጆቹ፤ባለፈው ጊዜ “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፲” በሚል ለቀረበው ምላሽ በድረገጻችን በመላክና በፌስቡክ ላይ በመለጠፍ የተሳተፋችሁትን በሙሉ እናመሰግናለን፡፡ በተለይ በግጥም ምላሻችሁን ለሰጣችሁ በሙሉ ከፍያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ የቅንብሩ አዘጋጅ ወለላዬ በቁጥር አስር ለቀረበው ጥያቄ ምላሻቸውን በሚከተለው መልኩ በግጥም አስፍረዋል፡፡ (እንደተለመደው በየሳምንቱ መልሱን ተከታትለን ባለማቅረባችን ለአንባቢያን ታላቅ ይቅርታ እንጠይቃለን::)who-is-he-10

መልስ

እኔ ነኝ፣ እኔ ነኝ፣ – እኔ ነኝ ተዘራ

የማስደስታችሁ – ከክራሬ ጋራ

ብለው የዘፈኑ – በገዛ ስማቸው

ድምጻዊ ተዘራ – ማለት እኚህ ናቸው


who is he 11ላሁኑ ደግሞ “እኚህ ሰው ማናቸው? – ፲፩” ወለላዬ የሚከተለውን አቅርበዋል፡፡ ምላሻችሁን በግጥም በመመለስ ለዝግጅቱ ውበት እንድትሰጡ ለማደፋፈር እንወዳለን፡፡ በሚቀጥለው መልሱን በግጥም እናቀርባለን፡፡

ጥያቄ

ዝርዝሩ ሲወጣ – ጀግኖች ሲቆጠሩ

አንደኛው አንበሳ – እኚህ ሰው ነበሩ

እንዲህ የገነነው – ሲጠራ ስማቸው

በምን ምክንያት ነው – ንገሩኝ ማናቸው?

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Who is This Person Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. dereje Mengesha says

    September 10, 2014 04:35 pm at 4:35 pm

    መድፍና ጠመንጃ ጥይት ሲጉዋረሱ
    አሳላፊ ነበር የማሩ ገረሱ።
    የተባለላቸው ደጃዝማች ገረሱ ዹኪ የሸዋ አርበኛ የነበሩ ናቸው።

    Reply
  2. Qaalluu says

    September 12, 2014 09:15 am at 9:15 am

    ከአዋሽ እስከ ጊቤ ጣሊያንና ባንዳን መቆሚያ መቀመጫ ያሳጣቸው። በቆራ፡ በዳዎ፡ በገፈርሳ፡ በጭቱ፡ በወሊሶ አካባቢ ጣሊያንና ባንዳን የረፈረፋ ጀግና አርበኛ ነው። ብዙ ሺህ የገበሬ ጦር ይዞ ከወራሪ የኢጣሊያ ፋሽት ጋር ሲታገል የቆቀ። ተፈሪ (ሀይለ ስላሴ) በእንግሊዞች ተጭኖ ፊንፍኔ (አዲስ አበባ) ሲገባ እንደ ሌሎች አርበኞች ሄዶ ያልሰገዳለት፡ ነገር ግን ሀይለ ስላሴ በዚህ ጉዳይ ደንግጦ አርባኛው ባለበት አመያ አካባቢ ግንዶ መንደር ላይ በእንግሊዞች ወተደር ታጂቦ ለአርበኛው ሰገዳለት። የመሻንገያ ሹመትም “ፊታውራሪ” አለው። ሽጉጡንም ሸለማው። ከዚያ በሁዋላ አርበኛው ወዳ ጂማና ኢሉ አባቦር የተሰባሰባውን የጠሊያንና ባንዳ ጦር ለመደምሰስ ጊቤን ተሸግሮ ቃላመሃለውን ፈጸመ።ከጊቤ እስክ ጎሬ ያለውን ጠላት ድምስሶ ምርኮኛውን ለዘመዶቹ ነጭ እንግሊዞች አስረክቦ። የጦር መሳሪያውን ለራሱ አደረገ። ከነጻነት በሁዋላ ቃል የተገባለት የጦር አባጋዝነት ሁሉ ተሰርዞ ፊታውራሪነት ወዳ ቀኛዝማችነት ወርዶ አርባኛው በአጼውና በጸሐፊ ትዕዛዜ እንደ ውሃ በቀጠነ ትዕዛዝ የቁም እስር ተፈረዳበት። ከቦታ ቦታ ከግዞትነት በማያንስ መልኩ ሹመት ተብዬው ስራ ተሰጠው።
    በሁዋላ ላይ ደግሞ ወደ ፊንፍኔ በመመለስ በሃይለ ስላሴ ነጭ ለባሾች እይታ ስር ሆኖ እስክ እለተ ሞቱ ድረስ በቁም እስርነት ኖረ።
    ይህ ጀግና አርበኛ ደጃዝማች ገረሱ ዱኪ ደብሱ (Garasuu Dhukii Dhabsuu Akkee Lubee)የፈረሱ ስም ኣባ ቦራ ይባላል።
    ትውልድ ቦታው ካሮ (Kaarroo) የሚባል በወሊሲ አካባቢ ነው። መኖሪያ ቤቱን ሰርቶ የነበረው ጨፎ የሚባል ቦታ ሲሆን ከሞተም በሁዋላ በዚሁ ቦታ እራሱ ባሰራው ጨፎ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ተቀበረ።
    ስለ ኢትዮጵያ አርበኞች ሲነሳ፡ ብዙ ጊዜ ንጉሱና ጀሌዎቹ የፈጸሙበት ግፍ ሲገልጹ በሚከተለው መልኩ ነበር
    “ኢትዮጵያ ሀገሬ ሞኝ ነሽ ተላላ፡ የሞተልሽ ቀርቶ የገደለሽ በላ።” ይባል ነበር።

    Reply
  3. Bombu says

    September 14, 2014 10:42 pm at 10:42 pm

    የሰው ልጅ በሕይወት ያሳለፈው ኑሮ
    የውጣ ውረዱ በታሪክ ላይ ሰፍሮ
    ለሌሎች ምሣሌ እንዲሆን መማሪያ
    በፅሁፍ ይሰፍራል ለትውልድም መኩሪያ

    የዚሕ ዓይነቱ ዕድል የዚሕ አይነት ዕጣ
    ክብሩን ተሸካሚ ከልኩ ሳይወጣ
    ምንም ሳይቀነስ ኣልያም ሳይለጠጥ
    የክብር ሥራቸው ከጃችን ሳያመልጥ

    ከቶ አከራካሪ ወይም ግራ አጋቢ
    ያልሆኑት እኝህ ሰው በውጭም በግቢ
    ኮርተው ያኮሩንን ስዎች ስናነሳ
    ደጃዝማች ገርሱ የኢትዮጵያ አንበሳ

    ሞተው ላገራቸው በዱር በገደሉ
    የውጭ ወራሪውን መክቶ በግሉ
    በሌለ መሣሪያ ትጥቅ ሳይሙዋላ
    በአገር ፍቅር ስሜት በዕምነት በመላ
    የገበሬ ጦሩ ተዋጊ በፈረስ
    ኣደራጅቶ መርቶ ወራሪን መደምሰስ
    ያስተማረን መክፈል ላገር መሥዋዕትነት
    ማን እንደ ገረሱ ለኢትዮጵያ በሕይወት »

    Reply
  4. bombu says

    September 14, 2014 11:36 pm at 11:36 pm

    ገድላቸውን ሰምተን ፍቅር ላገራችው
    በታሪክ ተፅፎ እንዳነበብናችው
    ተረት በምሳሌ ከሰዎችም ሰምተን
    ጀግኖች የነሳሉ ጊዜ ሳይወሰን

    አድንቀን ተገርመን ስማቸው ሳይቀረን
    የትውልድ ቦታ የዕድሚያቸውን ዘመን
    ሁሉንም ጠንቅቀን ካወቅን በሁዋላ
    ፎቶዋቸውን ስናይ ሆነ የተሟላ

    ታሪክ ትርጉም ሲያገኝ ገፅታ ተላብሶ
    ከፊታችን ሲቆም ሕልውና ቀምሶ
    ትጥቁም እየታይ ከነጎፈሪያቸው
    ማሥባሉ አይቀርም ለካስ እኝህ ናቸው

    Reply
  5. Ras Ja says

    September 15, 2014 03:09 am at 3:09 am

    እኔም አላውቅም
    እናንተው ንገሩኝ
    ታሪኩን ሥራውን በደንብ አብራሩልኝ

    ብዙ ማላውቃቸው ጀግኖች ስላሉ
    ከነርሱ መካከል አንዱ ይሆናሉ

    Reply
  6. Amsayaw Atnafu says

    September 15, 2014 03:12 am at 3:12 am

    ግምባሩን ኮስኩሶ እንደንብ አስፈሪ
    ጠመንጃውን ታጥቆ ጠላት አሳፋሪ
    ግርማ ሞገሳቸው እጅጉን አስፈሪ
    ስማቸው ግን ጠፋኝ እኚህ ፊት አውራሪ

    Reply
  7. Gadafi Derbew says

    September 15, 2014 03:16 am at 3:16 am

    አልገዛም ብሎ ለፋሽስት ወራሪ
    ለህዝቡ የቆመ አገሩን አክባሪ
    ከሊማሊሞ ገደል እስከ አርማጭሆ ድንበር
    በዱር በገደሉ ጠላትን ሲያሸብር
    የጣልያኑ ዘማች የሰሜኑ አርበኛ
    የውብነህ ልጅ አሞራው በለኛ

    Reply
  8. Seid Ebrahim says

    September 15, 2014 03:17 am at 3:17 am

    ግራ ተጋብቶኛል ማን እንደሆነ እሱ
    እኔ አላወኩትም ይነገረኝ መልሱ

    Reply
  9. Etsub Abebe says

    September 15, 2014 03:21 am at 3:21 am

    የርሻ ሚኒስትሩን
    ደጅ አዝማች ታከለን
    ተክለ ሃዋሪያን
    ይመስላል ፎቶዋቸው
    እንደው ግምቴ ነው
    ካልሆኑ እርሳቸው
    እስቲ ጎበዝ መልስ እኝህ ሰው ማናቸው?

    Reply
  10. Melkamu Mehirete says

    September 15, 2014 03:22 am at 3:22 am

    ጀግናዉ በላይ ዘለቀ – የጎጃሙጀግና
    ስምህ ይወደሳል ዛሬምእንደገና!

    Reply
  11. Getamesay Bekele says

    September 15, 2014 03:24 am at 3:24 am

    ጅግና የወለደው የጅግና ልጅ
    መሸሽ የማያውቀው ይሞታታል እንጂ
    በላይ ዘለቀ ነው የኢትዮጵያ ልጅ

    Reply
  12. Yeab Habesha Abebe says

    September 15, 2014 03:27 am at 3:27 am

    ዝርዝሩ ሲወጣ ጀግኖች ሲቆጠሩ
    ይሄ ሰውየማ ባሻ ቅጣው እንዳይሆኑ

    Reply
  13. Ephrem Nurye says

    September 15, 2014 03:28 am at 3:28 am

    ያበላይ ዘለቀ የጭንጫው በርበሬ
    ጠላት ተሸበረ እየሠማ ወሬ
    የዱሩ ደጅ አዝማች የከተማው ደሃ፥
    ያበላይ ዘለቀ ታላቁ ዝሆን
    ጦር መጣልህ በሉት ይነሣ እንደሆን
    ምንጭ ከህዝብ

    Reply
  14. ገብረየሱስ says

    September 17, 2014 11:36 pm at 11:36 pm

    ኣትቀስቅስልኝ የት ኣገኘሁህና
    በነዚህ ሲነሳ ልቤ ይረበሻል ስራየም ይህ ነውና

    Reply
  15. ገብረየሱስ says

    September 18, 2014 03:30 pm at 3:30 pm

    ለካ ለዚህ ነበር እዳስታውሰው የቀሰቀስከኝ
    ጀግንነት ከምሬት ተደበላልቆብኝ
    እርር እያልኩኝ እምባየ እየተናነቀኝ
    ጀግንነቱ ከነብሴ ተዋህዶ ህያውነት ዘራልኝ
    ባንዳዎች በዙ እንጂ ወንድነቱም ቀሰቀሰኝ
    ለነጋሪ ብቆይም እግዝሔር ሃጥያቱን ይቅልልልኝ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule