• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሃዲያ ሞሃመድ! ያልተዘመረላት ጀግና

July 9, 2015 05:14 am by Editor 4 Comments

ያልተዘመረላት፣ ያልተነገረላት ጀግና ኢትዮጵያዊት ሴት ናት። እንደሌሎች “እኔ ምን አገባኝ? አርፌ ልቀመጥ” ብላ፣ ባርነትንና ዉርደትን አሜን ብላ ተቀብላ፣ ሕሊናዋን ሸጣ፣ የገዢው ፓርቲ አዉደልዳይ ሆዳም ካድሬና አገልጋይ ሆና፣ በዘረኝንትና በጠባብነት በሽታ ተለክፋ መኖር ትችል ነበር። ግን አላደረገችውም።

hadiya moከደቡብ ክልል ከወላይታ ሶዶ ናት። የወያኔ ቡችላው ሃይለማሪያም ደሳለኝ መጣሁበት ካለው። እንደ ሃይለማሪያም ደሳለኝ የሌሎች አሽከር አልሆነችም። እንደ ኃይለማሪያም ደሳለኝ አልተንቦቀቦቀችም። እንደ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ሕሊናዋን አልሸጠችም። የወላይታ ጀግና የሆነውን የንጉስ ጦናን ወኔ ተላብሳ፣ ለእዉነት፣ ለፍትህ፣ ለነጻነት፣ ለዲሞክራሲና ለኢትዮጵያ አንድነት ቆመች። የወላይታ ሕዝብ በባህሉ፣ በቋንቋም በኢትዮጵያዊነቱ የሚኮራ፣ መብቱ ሲደፈር የማይወድ፣ ታታሪ ሕዝብ ነው። ይች ሴት በትክክል የወላይታ ሕዝብን አቋም አንጸባረቀች። ሕገ መንግስቱ በሚፈቅደው የመደራጀት መብት መሰረት፣ መብቷን ለማስከበር፣ የአንድነት ፓርቲን ተቀላቀለች። የወላይታ ዞን የአንድነት አመራር አባል ሆነች።

የአንድነት ፓርቲ፣ የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት በሚል መርህ በወላይታ ዞን ሕዝባዊ ስብሰባ ባደረገበት ወቅት፣ የቅስቀሳ ወረቀቶችን ለሕዝቡ ሳትፈራ ታድል ነበር። ያኔ ገዢዎች አሰሯት። ብዙ ጊዜ በፍርድ ቤት ካንገላቷትና ካሰቃይዋት በኋላ፣ ያለ አንዳች መረጃ፣ በአካባቢ የደህንነት ሃላፊ መመሪያ “አመጽ ቀስቃሽ” ተብላ ተፈረደባት። ወደ ወህኒ ተወረወረች። ያልተዘመረላት የነጻነት ታጋይ ጀግናዋ ሃዲያ ሞሃመድ!!!!

ኢትዮጵያዉያን በየቦታው በአእምሯችን ላለፉት 20 አመታት፣ ወያኔዎች የቀረቀሩትን፣ ስለነርሱ ያለንን የዉሸት ምስል፣ ከአእምሯችን አውጥተን፣ ምንም ጉልበትና አቅም የሌላቸው ደካሞችና የበሰበሱ መሆናቸውን ተገንዝበን፣ እንደ ሃዲያ ሞሃመድ፣ እንደ ርዮት አለሙ፣ እንደ ንግስት ወንዳፍራ፣ እንደ ሜሮን አለማየሁ . . . ብንነሳ የአገራችንን ትንሳኤ እናፋጥነው ነበር። ሰቆቃችን እንዳይራዘም፣ ዉርደታችን እንዳይቀጥል፣ ዛሬ፣ አሁን እንነሳ። ሁላችንም የድርሻችንን ለማበርከት እንዘጋጅ። ነጻነት በጥቂቶች መስዋትነት ብቻ አይገኝም። ለነጻነት ሁሉም የድርሻዉን ይወጣ ዘንድ የግድ ነው!! ትግሉን እንቀላቀል። ከሚሊዮኖች አንዱ እንሁን። (የሚሊዮኖች ድምጽ ፌስቡክ ገጽ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. rasdejen says

    July 10, 2015 09:43 am at 9:43 am

    Sister Hadeya Mohammed, I salute you! It is very true, there are so many Hadeya’s all over Ethiopia who maintained the authentic sovereign and human Ethiopian values. Thousands are murdered in silence.
    We Ethiopians shall liberate not only Ethiopia/Africa but also humanity of the globe which is confronting narcissism and neocolonialism. That can be realized if each of us consistently say no to injustice and salute just courses and people like Hadeya Mohammed.

    Reply
  2. Demelash gobezu says

    July 10, 2015 09:45 am at 9:45 am

    We fighttobringwoyanetothecourtoflaw

    Reply
  3. Daniel G/ says

    July 12, 2015 08:15 am at 8:15 am

    Wagashin lemekfel balchlim ida indalebign ammnalehu ye ethiopia amlak wiletashin yikfelish
    Tarik honesh tnorialeshna
    beta enwedishalen

    Reply
  4. እስከመቼ says

    July 15, 2015 12:59 am at 12:59 am

    ኢትዮጵያዊያን በያለንበት ልንኮራባቸው የሚገቡ ታጋይ እህቶችና ወንድሞች አሉን። ሃድያ ሞሐመድ አንዷ እህታችን ናት። በየቢታው ለወገንተኛው የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት አልገዛም ብለው፤ እንደ ቅድሞ እናቶቻችንና አባቶቻችን በአርበኝነት የሚዋደቁ አሉ። እኛስ እያንዳንዳችን ምን እያደረግን ነው? እነሱኮ ለኛና ለነገዎቹ ኢትዮጵያዊያን እየታገሉ ነው። ከጎናቸው መቆም አለብን። ለኢትዮጵያዊያን! ለኢትዮጵያ! ለራሳችን!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule