• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሃዲያ ሞሃመድ! ያልተዘመረላት ጀግና

July 9, 2015 05:14 am by Editor 4 Comments

ያልተዘመረላት፣ ያልተነገረላት ጀግና ኢትዮጵያዊት ሴት ናት። እንደሌሎች “እኔ ምን አገባኝ? አርፌ ልቀመጥ” ብላ፣ ባርነትንና ዉርደትን አሜን ብላ ተቀብላ፣ ሕሊናዋን ሸጣ፣ የገዢው ፓርቲ አዉደልዳይ ሆዳም ካድሬና አገልጋይ ሆና፣ በዘረኝንትና በጠባብነት በሽታ ተለክፋ መኖር ትችል ነበር። ግን አላደረገችውም።

hadiya moከደቡብ ክልል ከወላይታ ሶዶ ናት። የወያኔ ቡችላው ሃይለማሪያም ደሳለኝ መጣሁበት ካለው። እንደ ሃይለማሪያም ደሳለኝ የሌሎች አሽከር አልሆነችም። እንደ ኃይለማሪያም ደሳለኝ አልተንቦቀቦቀችም። እንደ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ሕሊናዋን አልሸጠችም። የወላይታ ጀግና የሆነውን የንጉስ ጦናን ወኔ ተላብሳ፣ ለእዉነት፣ ለፍትህ፣ ለነጻነት፣ ለዲሞክራሲና ለኢትዮጵያ አንድነት ቆመች። የወላይታ ሕዝብ በባህሉ፣ በቋንቋም በኢትዮጵያዊነቱ የሚኮራ፣ መብቱ ሲደፈር የማይወድ፣ ታታሪ ሕዝብ ነው። ይች ሴት በትክክል የወላይታ ሕዝብን አቋም አንጸባረቀች። ሕገ መንግስቱ በሚፈቅደው የመደራጀት መብት መሰረት፣ መብቷን ለማስከበር፣ የአንድነት ፓርቲን ተቀላቀለች። የወላይታ ዞን የአንድነት አመራር አባል ሆነች።

የአንድነት ፓርቲ፣ የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት በሚል መርህ በወላይታ ዞን ሕዝባዊ ስብሰባ ባደረገበት ወቅት፣ የቅስቀሳ ወረቀቶችን ለሕዝቡ ሳትፈራ ታድል ነበር። ያኔ ገዢዎች አሰሯት። ብዙ ጊዜ በፍርድ ቤት ካንገላቷትና ካሰቃይዋት በኋላ፣ ያለ አንዳች መረጃ፣ በአካባቢ የደህንነት ሃላፊ መመሪያ “አመጽ ቀስቃሽ” ተብላ ተፈረደባት። ወደ ወህኒ ተወረወረች። ያልተዘመረላት የነጻነት ታጋይ ጀግናዋ ሃዲያ ሞሃመድ!!!!

ኢትዮጵያዉያን በየቦታው በአእምሯችን ላለፉት 20 አመታት፣ ወያኔዎች የቀረቀሩትን፣ ስለነርሱ ያለንን የዉሸት ምስል፣ ከአእምሯችን አውጥተን፣ ምንም ጉልበትና አቅም የሌላቸው ደካሞችና የበሰበሱ መሆናቸውን ተገንዝበን፣ እንደ ሃዲያ ሞሃመድ፣ እንደ ርዮት አለሙ፣ እንደ ንግስት ወንዳፍራ፣ እንደ ሜሮን አለማየሁ . . . ብንነሳ የአገራችንን ትንሳኤ እናፋጥነው ነበር። ሰቆቃችን እንዳይራዘም፣ ዉርደታችን እንዳይቀጥል፣ ዛሬ፣ አሁን እንነሳ። ሁላችንም የድርሻችንን ለማበርከት እንዘጋጅ። ነጻነት በጥቂቶች መስዋትነት ብቻ አይገኝም። ለነጻነት ሁሉም የድርሻዉን ይወጣ ዘንድ የግድ ነው!! ትግሉን እንቀላቀል። ከሚሊዮኖች አንዱ እንሁን። (የሚሊዮኖች ድምጽ ፌስቡክ ገጽ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. rasdejen says

    July 10, 2015 09:43 am at 9:43 am

    Sister Hadeya Mohammed, I salute you! It is very true, there are so many Hadeya’s all over Ethiopia who maintained the authentic sovereign and human Ethiopian values. Thousands are murdered in silence.
    We Ethiopians shall liberate not only Ethiopia/Africa but also humanity of the globe which is confronting narcissism and neocolonialism. That can be realized if each of us consistently say no to injustice and salute just courses and people like Hadeya Mohammed.

    Reply
  2. Demelash gobezu says

    July 10, 2015 09:45 am at 9:45 am

    We fighttobringwoyanetothecourtoflaw

    Reply
  3. Daniel G/ says

    July 12, 2015 08:15 am at 8:15 am

    Wagashin lemekfel balchlim ida indalebign ammnalehu ye ethiopia amlak wiletashin yikfelish
    Tarik honesh tnorialeshna
    beta enwedishalen

    Reply
  4. እስከመቼ says

    July 15, 2015 12:59 am at 12:59 am

    ኢትዮጵያዊያን በያለንበት ልንኮራባቸው የሚገቡ ታጋይ እህቶችና ወንድሞች አሉን። ሃድያ ሞሐመድ አንዷ እህታችን ናት። በየቢታው ለወገንተኛው የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት አልገዛም ብለው፤ እንደ ቅድሞ እናቶቻችንና አባቶቻችን በአርበኝነት የሚዋደቁ አሉ። እኛስ እያንዳንዳችን ምን እያደረግን ነው? እነሱኮ ለኛና ለነገዎቹ ኢትዮጵያዊያን እየታገሉ ነው። ከጎናቸው መቆም አለብን። ለኢትዮጵያዊያን! ለኢትዮጵያ! ለራሳችን!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule