• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ነን ሶቤ (ዋሸሁ እንዴ?)” ይላል የአምቦው ፈርጥ ሃጫሉ

December 10, 2017 12:14 pm by Editor 4 Comments

“ዋሸሁ እንዴ?” (ነን ሶቤ)  ሲል ይጠይቃል፣ ድምጻዊ  ሃጫሉ ሁንዴሳ። ይህንን ጥያቄ የሚያቀርበው ለታዳሚው ሕዝብ አይደለም። በአስር ሺዎች የታደሙበት የኮንሰርት አዳራሽ  ውስጥ ከታዳሚው ፊት-ለፊት ለተቀመጡት ለእነ አባዱላ ገመዳ፣ ወይንም ደግሞ ለእነ ለማ መገርሳ ይመስላል። ከፍ ሲል ደግሞ ኮንሰርቱን በቀጥታ ስርጭት እየተከታተሉ ላሉት የአድዋ ባለ ግዜዎች የቀረበ ጥያቄ ነው።

ይህ ድምጸ-መረዋ ወጣት በምርጥ ቅላፄው ያንጎራጎረው ፉከራ እና ዜማ እጅግ ያስደምማል። ማስደመሙ እውነትን በመድረክ ላይ መዘርገፉ አይደለም። ከራሱ ደህንነት ይልቅ የወገኑን ስቃይ እና ሰቆቃ በማስቀደሙ ነው። እንዲህ አይነቱ እውነትን አደባባይ ወጥቶ በድፍረት የመናገር “ገት” የነበረው ቴዲ አፍሮ ነበር። ይህንን በማድረጉም በአንባገነኖቹ ጥርስ ውስጥ ገብቶ ብዙ ቢያስከፍለውም፣ ከህዝብ ልብ ውስጥ ሊወጣ አልቻለም።

በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ፣ ትላንት ምሽት የተፈናቀሉ ወገኖችን ለመርዳት የኦሮሞ ሙዚቀኞች ማህበር ባተዘጋጀው “ወገን ለወገን” ኮንሰርት ላይ ድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ መድረኩን ጠቆጣጥሮት ነበር። የሕዝቡን ስሜት እየኮረኮረ፣ ብሶቱን በአደባባይ ዘርግፎታል። ጠንከር ባሉ ቃላት የተቃኘው ስንኝ ከውብ ድምጽና ቀስቃሽ ዜማ ጋር ታጅቦ ሲቀርብ ልዩ ስሜትን ፈጥሮ ነበር። ይህ ዜማ በቀጥታ ስርጭት ሲተላለፍ በአዳራሹ የነበረው ድባብ እጅግ ይደንቃል። ሃጫሉ ይጠይቃል፣ ታዳሚው ስሜቱን በጩኸት ይገልጻል። ኦሮምኛ ባልችልና የሚለውን ነገር ባልረዳ ኖሮ ይጸጽተኝ ነበር። ይህ ወጣት ድምጻዊ መድረኩን ተቆጣጥሮ ይዞ እንዲህ ይል ነበር፤

Geerar geerar naan jettuu

Dhiirri geeraree hin quufne

Hidhaa qaallitti jiraa

Dhiirri geeraree hin quufne

Hidhaa qilinxoo jiraa

Dhiirri geeraree hin quufne

Hidhaa karchallee jiraa

Karchallee Amboo jiraa…

ይህ ስንኝ በካፊል ወደ አማርኛ ሲመለስ፤

“ሸልል ሸልልይሉኛል

ምኑን ልሸልል እኔ

ቂሊንጦ አይደለም ወይ

ቃሊቲ አይደለም ወይ

ከርቸሌ አይደለም ወይ

አምቦ ከርቻሌ አይደለም ወይ…

መኖርያው የወገኔ

የፈረሶቻችንን ዝና፣

የጀግኖቻችንን ዝና

አድዋ ላይ ይነግረና!

መቀሌ ላይ ይነገር!

አብሮ መኖር ይሻላል ብለን…

መከባበር ይሻላል ብለን…

እስከዛሬ ታግሰናል…

ከእንግዲህ ግን ይበቃናል!” ይላል ሃጫሉ።

እስር ቤቱ ሁሉ አፋን አኦሮሞ ይናገራል ሲሉ እነ ስዬ አብርሃ እንኳን የመሰከሩለት ጉዳይ በመሆኑ ይመስላል ሃጫሉ በመሃል እንደ አዝማች፣ “አይደለም እንዴ? ዋሸሁ እንዴ? (ነን ሶቤ?)” የሚለው የአለምዬ ጌታቸውን ስንኝ የሚያክልበት። በቃሊቲ፣  በቂሊንጦ፣ በከርቸሌ፣ … እየማቀቁ ያሉ የሕሊና  እስረኞች ጉዳይ ከራሱ ደህንነት በላይ ስላስጨነቀው ይህችን አጋጣሚ መጠቀም ነበረበት።

ይህ የጥበብ ሰው ከርቸሌን በወሬ ሳይሆን በተግባር ያውቃታል። የአድዋ፣ የመቀሌ የሚላቸው ጥጋበኞች አምቦ ላይ አስረውት ለሁለት አመት አሳቃይተውታል። ለእስር እና ለዱላ ያበቃው ወንጀሉ መብቱን ማቀቁ ነበር። በወሩ መጨረሻ ላይ በጊዮን ሆቴል ያዘጋጀው ኮንሰርትም በወያኔ ካድሬዎች ተሰርዞበታል።

ተከባብረን አብረን እንኑር ያሉ የኦሮሞ መሪዎች፤ እነ ፕ/ር መረራ ጉዲና፣ እነ በቀለ ገርባ በአድዋ ልጆች የግፍ ብትር እየተመቱ ነው። አድዋዎቹ ይህንን መከባበር እንደፍርሃት ከወሰዱት፣ መከባበሩ ካሁን በኋላ ያበቃል የሚል መልዕክት ነው ሃጫሉ ያስተላለፈው።

ይህ የሃጫሉ ስራ፣ አትሌት ለሊሳ ፈይሳ በአሎምፒክ በድረክ ከፈጸመው ጀብዱ አይተናንስም። እርግጥ ነው። አትሌት ለሊሳ አለምአቀፍ ትኩረትን ስቦ ነበር። ሃጫሉ ግን መልዕክቱን ሲያስተላልፍ በአንባገነኖቹ ጉያ ሆኖ፣ ሊመጣበት የሚችለውን ነገር ሁሉ ተጋፍጦ ራሱን ለመስዋእትነት ያዘጋጀ ጀግና ነው።

ይህንን አድርጎ ቢታሰርም፣ ታሪክ ሰርቷልና ምን ግዜም አይቆጨውም። የግዜ ጉዳይ እንጂ አምባገነኑ ስርዓት ይሄዳል የሃጫሉ ስራ ግን ምንግዜም ይዘከራል።

ሙዚቃውን  ለመመልከት እዚህ ላይ ይጫኑ።

ክንፉ አሰፋ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

 

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    December 11, 2017 12:54 am at 12:54 am

    “በአዲስ አበባ ሚሊኒየም አዳራሽ ፣ ትላንት ምሽት የተፈናቀሉ ወገኖችን ለመርዳት የኦሮሞ ሙዚቀኞች ማህበር ባተዘጋጀው “ወገን ለወገን” ኮንሰርት ላይ ድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ መድረኩን ተቆጣጥሮት ነበር።”
    “የኦሮሞኛ ቋንቋ ባልችልና የሚለውን ነገር ባልረዳ ኖሮ ይጸጽተኝ ነበር።” (ክንፉ አሰፋ)
    __ ወገን ለወገን ማለት ምን ማለት ነው!? የኦሮሞ ወገን አማራ፡ ትግሬ፡ ደቡቤ፡ አፋር፡ ሱማሌ መሆኑ ቀረ?
    “የአዲስ አበባ፡ የሐረሩ፡ የአፋሩ፡የኦሮሞው የጉራጌው የትግሬው የአማራው የለውም አባይ አንቺ ወላዋይ እያለ ያቀነቀነው ማን ነበር?..
    መቼ እንኳን ቋንቋውን ለሚችል ለማይችልም ሙዚቃ ቀስቃሽ፡አሳባሪና አስጨፋሪም ነው። እንዲያው ስሙ ያልተሞገሰና በግብዣም ያልተጠራ ወገን እንደተገለለ ተቆጥሮ ማኩረፉና መቀየሙ አይቀርም ለነገሩ ጠሪ አክባሪ ነበር ቃሉ… ነን ሶቤ?

    ፣ ድምጻዊ ሃጫሉ ሁንዴሳ።“ዋሸሁ እንዴ?” (ነን ሶቤ) ሲል ይጠይቃል ይህንን ጥያቄ የሚያቀርበው ለታዳሚው ሕዝብ አይደለም።” ከታዳሚው ፊት-ለፊት ለተቀመጡት ለእነ አባዱላ ገመዳ፣ ወይንም ደግሞ ለእነ ለማ መገርሳ፡ ዶ/ር አብይ ለእነ አዲሱ አረጋ ይመስላል።”(ለሚመለከቱና ለሚገመግሙም) ይህ አግባብነት አለው። የ፻ ዓመት ታሪክ ያላት ኢትዮጵያ ሚሊኒየም አዳራሽ? ” በአዲስ አበባ ላይ የመጨፈሪያና መሰብሰቢያ ቅድሚያ የማግኘት’ልዩ ሕገመንግስታዊ’ ጥቅማጥቅምን መብት ተጠቅሞ ጨፍሮ ወገኑን በቃሊቲ፡ በቅሊንጦ፡ በከርቸሌ አስረው በክልላቸው (እራስን በራስ በሚያስተዳድሩበት) ሰፈር የሌላው ብሔር፡ በሜንጫ ሲታረድ፡ ከነነፍሱ ገደል ሲጨመር፡ በተኛበት ቤቱ ላይ የሰደድ እሳት ተለቆ ሲቃጠል፡ ሴት ከሕጻናት በሜንጫ ሲተለተል፡ነግ በእኔ አለማለታቸው ያመጣው “የምንይልክ ሰፋሪ መጤ” የሚሉ ትምኪት የወለደው ግፍ ጠባብነት እንደሆነ ከነገራቸው ጥሩ ነው። ለመሆኑ ሌላው ብሔር ለኦሮሞ ተፈናቃይ ወገኑ ዕርዳታ እንዴት አልተገኘም? ለታሰሩ ወገኖቹስ ሲዘፈነላቸው ሲሞገሱ እንዴት አብሮ ድምፁን አላሰማም!?

    __በእርግጥ ኦሮሞ የራሱን ቤት በራሱ ላይ ቆልፎ ቁልፉን ጥሎ አፋልጉኝ የወጣው ወይንም ‘ተከልሎና ተከልክሎ’ የበላተኛ ተመካች እንዲሆን የተፈረደበት በእራሱ ቦልጥቀኞች (ዲያስፐርስ) መሆኑን ማመንና መቀበል አለበት።
    * አጫሉ ሁንዴሳ አድዋና መቀሌን ሊያነሳ የታጋይ ጦረኛ(ነፍጠኛ) ኦሮሞዎችን ከእነፈረሳቸው፡ ለሀገር ሉዓላዊነት ታሪክ፡ አልደፈር አልገዛ ባይነት፡ ሀገር እንዳስከበሩ በደምና አጥንታቸው ለአንዲት ኢትዮጵያ እንደተሰው አስታወሰ፡ እንጂ እንደዛሬው ሀገር ጥለው እንደከብት ጋጣ (ክልል) መታጎራቸውን ሊመሰክር አልነበረም!።
    *** ስሕተቱ የመጣው ግን..ጂርቱ…ኢጆሌ ኦሮሞ ቦረና፡ አንቦ፡ወለጋ፡አርሲ፡ባሬንቱ፡ ቱለማ፡ ሜጫ ቦሌ ፡.. ኤሰ ጅርቱ? አብሮ መኖር ይሻላል ብለን… መከባበር ይሻላል ብለን…
    እስከዛሬ ታግሰናል… ከእንግዲህ ግን ይበቃናል!” ይላል ሃጫሉ። ” አጫሉ ይህን የሚለው ማን እማን ላይ? እምን ላይ? ከማን ላይ? ከማን ጋር ቆሞ እንደሚነሳ አልታወቀም!?
    ሌላው ሕዝብ ሁለት ግዜ አልተጠራም በግብዣውም በሽለላውም!ጉድ በል ሰላሌ! ዘንድሮ አለ ነገር! አለ …ጉዲ ሰዲ ቂም በቀል፡ ቁርሾ፡እልህ፡ እግዚኦ መሓረነ…”ያዢ ያጣች ሀገር” አሉ አባቴ ዘይገርም!

    Reply
  2. dergu temelese says

    December 12, 2017 08:20 am at 8:20 am

    በአድ ነው ብአዴን ሁልጊዜም ለአማራ፣
    ህሊናውን ክዶ ለከርሱ የሠራ፣
    አማራ ለሀጫም ብሎ የሚሳደብ፣
    የዓሳ ማጥመጃ የህወሀት መረብ፡፡

    Reply
  3. Mulugeta Andargie says

    December 12, 2017 11:33 pm at 11:33 pm

    ጎልጉሎች!! አጫሉ እኮ ያገሳው የናንተን ሃሳብ ተመርኩዞ አይደለም!! እኔም ተከታትየዋለሁ ኮንሰርቱን!!ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ ሆነብን የናንተ ነገር!!መቼም ጉዳይን ጉዳይ ያነሳውና ዘበቱ ወደ ቁምነገር አልያም ፌዝ ሆኖ ያልፋል! ስለዘበት ስናወራ ማጋነን መዋሸት:ማሳቅ:ማስለቀስ:መዘላበድ:ማቃቃር:ማወዳጀት: ማፋቀር:እና ሌላም ሌላም ይዘከዘካል!!ዘበት ነዋ!!ዘበት ራሷ ቄንጥ አውጪ ናት!! ለባብሳ የወጣች ኮረዳ ይመስል ትሽሞነሞናለች! ቀበጥ ናት እኮ! ወዲያው እኩያዋ ያዝ ሲያደርጋት:ቅብጥናዋን ተወት አድርጋ መለሳለስን ትታተከዋለች:: ዝምድና ተፈራ ሆነ!!እንዲህ ነው ትዳር!!ማን ያገኘዋል?? እመት ቀበጢናም ሳታመነታ ያኳሸማትን ጎረምሳ አቀፍ ነዋ!! ዳሩ ለምን ተኳኩላ ወጣች??ፈዘህ የቀረሀው አንተ!! ልታማት ፈለግህ እንዴ??ኧረ ወዳያ እቴ!! ከረፈፍ ሁላ !!ጎልጉሎች!! መርቀናል!!!አጃኢባ ብለን ነበር!! ምንታደርገዋለህ?? ሳይደግስ አይጣላ ሆነና መቼስ ሸርተት እንበል??እንደ ያፍ ወለምታ እንቁጠረው??እንዲያ ይሻላል!! ብሩክ ጉዞ!!

    Reply
  4. aradw says

    December 14, 2017 09:56 pm at 9:56 pm

    Haccalu: What a literary work. This is not entertainment as other singers do. It is a heavy message to all of us who are concerned for our people and our country that is on a cross road. His message pierce our heart pock our mind to answer the question he left us with. He did not lie. He sees what most of us did not see may be we saw and did not care. As a literary work he put most thing open for us to fill the blank. “እስከዛሬ ታግሰናል…ከእንግዲህ ግን ይበቃናል. This is a reflection of all Ethiopians regardless of nationalities. It is a futile trial to compare Hacchalus song with other as Ato Below put it up as ” …..የለውም አባይ አንቺ ወላዋይ እያለ ያቀነቀነው ማን ነበር?….This was a song of different time to reflect different situation. Haccalu put the peoples grievances in a song. He did not put Oromo grievances or Amhara grievances. He strait forward shows the grievances of all the people. It is a great work as I see it.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ባልደራስ የአገርን ደኅንነት አደጋ ላይ በመጣል ሊጠየቅ ይገባዋል ተባለ July 1, 2022 09:23 am
  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule