• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“አልጠግብ ባይ ሲተፋ ያድራል”

September 3, 2016 03:52 am by Editor Leave a Comment

መግቢያ

አይ ወያኔ! መጨረሻቸውን በዓይናችን ልናይ ይሆን? አቦ አታስጎምጁኝ! ዓለማቸዉን ሲቀጩ ማቆሚያ ያጠራት ዓለማቸው ጨርሳ ልትቀጭባቸው ነው መሰል! እየዘረፉ እየገፈፉ፣ ሕዝቡን አደኸዩት፣ አስራቡት፣ አሳረዙት። እነሱ ግን ለዕርድ እንደተዘጋጀ ሰንጋ ሲደልቡ፣ ሲሰቡ ሩብ ምዕት ዓመታት አለፉ! አልጠግብ ብለው ግን መትፋት ጀምረዋል! ሕዝባችንን፣ አንገሽግሸውት አንገቱ ድረሰውታል። የከፋው የከረፋው ሕዝብ ከዳር እስከ ዳር ተነቃንቋል! ኦሮሞው ተነስቷል። አማራው ተነስቷል። ኮንሶው ተንስቷል። ኦጋዴን ተነሷል። … እስከወዲያኛው ከፋፍለነዋል ያሉት ኦሮሞ እና አማራ ተስማምቷል! ዕቅዳቸው ከሽፏል።

የወያኔ የግድያ ቡድን አባላት፣ ያልታጠቁ የዜጎቻችንን ደም በጭካኔ አፍስሰው፣ እኵይ ተግባራቸውን ከጀግንነት ቆጥረው ይፎክሩበታል፣ ያቅራሩበታል። አሁን ሴት ገድሎ ምን ያስፎክራል? ሕጻን ገድሎ ምን ያስሸልላል? እኵይ! እኵይ! እኵይ! የእንግሊዝኛው ቋንቋ የበለጠ ይገልጻቸዋል! COWARDS! ያ አልበቃ ብሎአቸው በግፍ ገድለው በነሱው ብሶ ሕዝቡን ሲኮንኑት ማየት አያንገሸግሽም? ንጹህ ዜጎችን እያሰሩ “ሽብርተኞች ናቸው” እያሉ ሲወነጅሉ ማየት አያበሽቅም? የታሠሩትን እያሰቃዩ፣ ያሾፉበታል። አዎን፣ ሰላም ያሸብራቸዋል። አንድነት ያሸብራቸዋል። አገር ወዳድነት ያሸብራቸዋል። አፋቸውን ሞልተው “ልማታችንን ለማደናቀፍ የተነሱ ጸረ-ልማት ኃይሎች በቁጥጥር ሥር አዋልን” እያሉ ይበሻቀጣሉ። ዕውነት ነው፣ እነሱ ከድኃው አፍ እየነጠቁ፣ እየሰቡ፣ እየዳበሩ ለምተዋል። አብዛኛው ከአፉ እየተነጠቀ ያጎርሳቸዋል። እየተራበ፣ እየከሳ እየሰለለ መንምኖ እንሱን ያለማል። ይኸ  ሁሉ መብት መጋፋት፣ የዘረፋ ተግባር ዕድሜአቸውን የሚያራዘምላችሁ እየመሰላቸው ጭካኔአቸውን በላይ በላዩ ይጨምራሉ። የወያኔ አጨካከን ከሰው የተፈጠሩ አያስመስላቸውም። የመረረው የመጨረሻውን ዕርምጃ የመውሰዱን ሐቅ፣ ያ በኮለስትሮል የደነደነው አዕምሮቻቸው መረዳት ተስኖታል። ወያኔዎችች የበሉት ያገሳቸዋል! በላይ በላዩ! (ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule