
በአማራ ክልል የተነሳውን ብጥብጥ አስመልክቶ በክልሉ የአስቸኳይ ጊዜ ዓዋጅ መታወጁ ይታወቃል። በመሆኑም በርካታ ከተሞች አገልግሎት መስጠት አቁመው ተዘግተው ቆይተዋል። ሆኖም የመከላከያ ኃይል የክልሉን ሰላም ማስጠበቅ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ በርካታ ከተሞች ሰላማቸውን እያገኙ ነው። በተለይ የክልሉ ዋና ከተማና ታሪካዊቷ የጎንደር ከተማ ወደ ቀድሞ ሰላማቸው መመለሳቸውን ኢቢሲ በፎቶ አስደግፎ ዘግቧል። ወጣቶች ወደ መጫወቻ ቦታ እየሄዱ ጊዜያቸውን እያሳለፉ ነው፤ ዜጎች ወደ ቤተክርስቲያን መበሄድ በተለይ የፍልሰታን ጾም ሲካፈሉ ታይተዋል፤ የትራንስፖርት አገልግሎት ተጀምሯል፤ ንግድ ቀጥሏል፤ ዜጎች እየመጣ ባለው ሰላም ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። ፎቶዎቹ እሁድ ዕለት የተወሰዱ ናቸው።
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ





Leave a Reply