• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

መንግሥት መሠረተ ቢስ ውንጀላዎችን ፈጽሞ እንደማይታገስ አስታወቀ

October 28, 2022 10:24 am by Editor Leave a Comment

”የሰብአዊ መብት ባለሙያዎች ኮሚሽን ኢትዮጵያ ላይ ጫና ማሳደር የተቋቋመ ስብስብ ነው” ሲሉ አምባሳደር ታዬ

ኃላፊነት የጎደላቸው አካላት ለአደገኛ የፖለቲካ አጀንዳ ሲባል እየፈጠሯቸው የሚገኙ መሠረተ ቢስ ውንጀላዎችን ኢትዮጵያ ታወግዛለችበምዕራባውያን የተለያዩ አካላት አማካኝነት በኢትዮጵያ ላይ የሚነዙ የሐሰት ስም ማጥፋቶችን የኢትዮጵያ መንግሥት ፈጽሞ አይታገሥም።

እነዚህ አካላት ኢትዮጵያ ውስጥ የከፉ ወንጀሎች ሊፈጸሙ ይችላሉ በሚል የሕወሐትን ጊዜ ያለፈበት ፕሮፓጋንዳ እንደ በቀቀንመድገማቸው አሳፋሪ ነው።

እነዚህ አካላት የሚከሱት ፍንጮችን ወይም ተጨባጭ ክስተቶችን መሠረት አድርገውአይደለም፤ የመፈጸም ዕድል አለ በሚል ያልተጨበጠ ግምት እንጂ።

እጅግ የሚያሳዝነው ደግሞ የተሻለ ስም ያላቸው ተቋማት ሳይቀሩ ይሄንን በኢትዮጵያ ላይ ተቀነባብሮ የሚለቀቅ ፕሮፓጋንዳ ለመቃወም አለመቻላቸው ነው።

ጥቂቶቹም ስለ ኢትዮጵያ የተነገረውን ስምማጥፋት በማመን ሳይሞኙ እንዳልቀሩ ይገመታል። አንዳንዶችም እነዚህን የሐሰት ክሶች ኢትዮጽያን ለማንበርከክ ሊጠቀሙባቸው ይፈልጋሉ።

ይሄን መሰል አስደንጋጭ ክሶችን አቅርቦ የኢትዮጵያ መንግሥትን በማስጨነቅ በሕወሐት ላይ እየወሰደ ያለውን የመከላከል ርምጃ ለማስቀየስ የሚችሉ መስሏቸው ከሆነ ተሳስተዋል።

አንዳንዶችም የሚችሉትን ሁሉ በማድረግ ይህንን ቡድን ለማዳን እየተረባረቡ ነው። አንዳንድ ምዕራባውያን ባለ ሥልጣናት ጭምር ይሄንን የሐሰት ክስ የሚነዙት ኢትዮጵያ ትእዛዛቸውን አልቀበል ስላለቻቸው መሆኑን በይፋ መናገር ጀምረዋል። ይህ ጊዜ አመጣሽ የሐሰት ክስ መሬት ላይ ያለውን እውነታ ጨርሶ አይቀይረውም።

እነዚህ ጉምቱ ተቋማትና ወሳኝ ተዋንያን፣ በቂ ግንዛቤ ሳይኖራቸው በዚህ የሃሰት ዘመቻ እየተሳተፉ ይገኛሉ። ይሄን የመሰሉ የከፉና ሊወገዙ የሚገባቸው ውንጀላዎች ለፖለቲካ ዓላማ መዋላቸው ኃላፊነት የጎደለውና አሳፋሪ ነው በማለት መንግሥት አስታውቋል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ዓለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ባለሙያዎች ኮሚሽን ኢትዮጵያ ላይ ጫና ማሳደር ያስችላል በሚል የፖለቲካ ስሌት የተቋቋመ ስብስብ ነው” ሲሉ በተባበሩት መንግስታት የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ገለጹ።

“አንዳንድ አካላት በፖለቲካዊ ጫና እሳቤ በኢትዮጵያ የዳርፉር አይነት ታሪክ መፍጠር እንደሚፈልጉ በግልጽ በመናገር ላይ ናቸው” ብለዋል አምባሳደር ታዬ በትዊተር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት ገልጸዋል።

የኮሚሽኑ ሪፖርቶች ኢትዮጵያ ላይ ጨምሮ ለሌሎች የአፍሪካ አገራት ከፈጠራ ታሪክነት የዘለለ ትርጉም እንደሌላቸው አመልክተዋል።

ዓለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ባለሙያዎች ኮሚሽን ኢትዮጵያ ላይ የበረታ ጫና ማሳደር ያስችላል በሚል የፖለቲካ ስሌት የተቋቋመ ስብስብ እንደሆነ በግልጽ አሳይቷል ነው ያሉት ቋሚ መልዕክተኛው።

የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብት ምክር ቤት በመስከረም ወር 2015 ዓ.ም ባደረገው 51ኛ መደበኛ ስብሰባ የኮሚሽኑን የቆይታ ጊዜ በአንድ ዓመት ያራዘመ ቢሆንም ኢትዮጵያ የውሳኔ ሀሳቡን እንደማትቀበልና እንደምትቃወም መግለጿ ይታወቃል።

በቅርቡ ኢትዮጵያን አስመልክቶ ያወጣውን የሰብአዊ መብት ሪፖርት መንግስት እንደማይቀበለው ማሳወቁም የሚታወስ ነው።

ሪፖርቱ ከደረጃ በታች የሆነ፣ ሙያዊ ይዘት የጎደለውና ግድ የለሽነት የተሞላበት መሆኑን ገልጸዋል።

የኮሚሽኑ ሪፖርት በሰብአዊ መብት ሽፋን ፖለቲካዊ ፍላጎቶችን የማስፈጸም ተልዕኮ ያለው መሆኑንም መንግስት ለሪፖርቱ በሰጠው ምላሽ መግለጹ የሚታወስ ነው። (ዋልታ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: ethiopian terrorists, Hands off ethiopia, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule