• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የጄራርድ ዲፓርዱ የሩሲያዊ ዜግነት ጥያቄና ሀገር ማለት

January 6, 2013 09:43 am by Editor Leave a Comment

በዓለም የተበተንነው ኢትዮጵያዊያን ቁጥር በጣም ብዙ ነው። አሁንም ከኢትዮጵያ ወደ ውጭ ዓለም ለመውጣት ጥረት የሚያደርጉ ወገኖቻችን ቁጥር ቀላል አይደለም። በውጭ የምንኖረው፤ በየምንኖርበት ሀገር፤ የሀገሩን ዜግነት በተለያዬ ምክንያት የወሰድንና ያልወሰድን አለን። ይኼ ሁሉ እንዳለ ሆኖ ግን፤ እኔም ሆንኩ እኔ የማውቃቸው ኢትዮጵያዊያን፤ ሀገራችን በልባችን ቋጥረን ነው የምንጓዘው። እኔ ቁጥሬ፤ በንጉሠ ነገሥቱ ጊዜ ተወልደው አድገው፣ የንጉሠ ነገሥቱን አገዛዝ ኋላ ቀር ነው ብለው ተቃውመው፣ በደርግ ጊዜ ግብግብ ገጥመው፣ አሁንም የወያኔን የፖለቲካ ፍልስፍናና የአስተዳደር መመሪያ በመቃወም ከሀገር ውጪ ካሉት ወገን ነው። በአስተዳደጋችን ሆነ በእምነታችን፤ ሀገራችን ከማንም ሀገር አሳንሰን ተመልክተን አናውቅም።

የገዢዎቻችን ተግባር እንጂ፤ የሀገራችን ጉዳይ ላንዳፍታም እንኳ ጥያቄ ውስጥ አላስገባንም ነበር። በርግጥ በወያኔ አራጋቢነትና እንገንጠል ባይ ታጋዮች፤ ኢትዮጵያዊነት ባሁኑ ሰዓት ጥያቄ ውስጥ መግባቱን አልክድም። እስከ ጥቂት ዓመታት ድረስ፤ ቢያንስ እኔ ባለሁበት አካባቢ ያለን ኢትዮጵያዊያን፤ ከሞላ ጎደል ሁላችንም፤ ሻንጣችንን አዘጋጅተን ሀገር ለመግባት የተዘጋጀን ነበር የምንመስለው። ከመካከላችን አንዱ ቤት ንብረት ካዳበረ፤ ይኼ ሰው ተደላደለ በሚል ዓይን የሚመለከተው ቁጥሩ ቀላል አልነበረም። ይህ ደግሞ፤ በታጋይ ድርጅቶች ዙሪያ ያሉትንም ሆነ በድርጅት ያልታቀፉትን ያካትት ነበር።

ያጠናነው የትምህርት መስክ አስገድዶን፤ ከመንግሥት ጋር የተያያዘ የሥር መስክን የሚያክ በመሆኑ፤ የአሜሪካን የዜግነት መሐላ ለፈፀምነው፤ የነበረብን ፍጥጫ ቀላል አልነበረም። ይህ እንግዲህ፤ በአሜሪካ ብቻ የሚታይ አይደለም የሚል ግምት አለኝ። በአውስትራሊያም ሆነ በአውሮፓ፤ በአረብ ሀገሮችም ሆነ በአፍሪቃ፤ ተመሳሳይ ክንውኖች ይተገበራሉ የሚል ግምት አለኝ። የዚህ ሁሉ ድርደራ መልዕክቱ፤ እኔም ሆንኩ የማውቃቸው ኢትዮጵያዊያን፤ ሀገራችንን ከግል ኑሯችን ውጪ በልባችን ይዘን የምንጓዝ መሆናችንን ለማመልከት ነው። የእኔ የግል የኑሮ ሁኔታም ሆነ ያለኝ አመለካከት፤ ሀገሬን ከኔ እንዳወጣት መንገድ አይከፈትለትም። ስለከፋኝ ወይንም ስለደላኝ፣ ስለተራብኩ ወይንም ስለጠገብኩ፤ የፖለቲካ እምነቴ ግራ ስለገባ ወይንም ቀኝ ስለዘመተ፣ በአስተዳዳሪዎች በደል ስለተፈፀመብኝ ወይንም ስለተሾምኩ፤ የተሰደድኩበት ሀገር ስለደላኝ ወይንም ስለከፋኝ፤ የሀገሬ ሀገሬ መሆን አይለወጥም። እኔ ብቻ አይደለሁም። እኔ የማውቃቸው በሙሉ ማለቴ ነው።

በርግጥ ለኔ ይኼን ገፅ አሳይተውኝ እነሱ ሌላ እምነት ይዘው ቢገኙ ተጠያቂ አልሆንም። ታዲያ አደንቀው የነበር ፈረንሳዊ የኪነ ጥበብ ሰው፤ ጄራርድ ዲፓርዱ፤ ፈረንሣዊነቱን ትቶ ሩሲያዊ ሊሆን ሲወስንና ሲተገብረው፤ ደነገጥኩ። እንዲህ ነው።  ጄራርድ ዲፓርዱ የታወቀ ፈረሣዊ የኪነት ሰው ነው። በእንግሊዝኛና በፈረንሣይኛ ከሠራቸው ፊልሞቹ መካከል ጥቂቶቹን በማየት አወቅሁት፤ አደነቅሁትም። ታዲያ ደግሞ ጥሩ ብዬ፤ በዚያ ቦታ ካስቀመጥኳቸው የኪነት ሰዎች ጋር ሰቅዬ አስቀመጥኩት። ለዚህ ይመስለኛል መደንገጤ። የራሴው ግንዛቤ እንጂ ከሱ ጥፋት የለም። ወደ ራሴ ተመልሼ እኔና ሀገሬን ተመለከትኩ። ደገመችና ብሪጂት ባርዶ ተከተለችው። እሷም ሌላዋ ፈረንሳዊት ነች፡ የሱ ምክንያት፤ “ገንዘቤን እወዳለሁ፤ ግብራችሁ በዛብኝ!”  ነው። የሷ ደግሞ፤ “ሁለት ዝሆኖች ስለታመሙ ፤ ልትገድሏቸው ወስናችኋል። ለኔ ስጡኝና እኔ እጦራቸዋለሁ። አለበለዚያ ግን ሩሲያዊ እሆናለሁ።” ብላ ነው።

መቸም በስለላ ተግባር ተመድበው ወይንም ለሌላ መንግሥት ሲሰልሉ ሊደረስባቸው ሲል ሀገር ጥለው የሚጠፉና ዜግነትን የሚወስዱ መኖራቸው አዲስ አይደለም። በፖለቲካ አመለካከታቸው የተፈረደባቸውና ሀገራቸው የተወረረባቸውም ምርጭ ሲጠፋ ሌላ ዜግነት መውሰዳቸው ያለ ነው። ለኔ ይኼ ካልተደረገልኝ ወይንም በሀገሪቱ እኔ የምለው ካልተፈፀመ ሀገሬን ለቅቄ የሌላ ሀገር ሰው እሆናለሁ ብሎ መዛትና ይኼንኑ መፈፀም ግን ለኔ እንግዳ ሆኖብኛል። መቼም እድሜ ልኬን ተማሪ ነኝና፤ ይኼም አዲስ ትምህርት ሆኖልኝ እስክረዳው ድረስ ይቆረቁረኛል። ይኼም አለ ለካ የሚያሰኘው እንዲህ ዓይነቱ ነው።

ለኔ ይኼ ካልሆነ ወይንም እኔ ተበደልኩ የሚለው፤ ሀገርን የአሁን ክንውን ያደርገዋል። አሁን ደግሞ ከታሪክና ከባህል ያልተያያዘና ጊዜውን ጠባቂ ነው። ታዲያ የሀገርን ምንነት በአሁንና በአሁን የግል ግንዛቤያችን ካስቀመጥነው፤ ያለታሪክና ያለባህል፤ ሀገር የትም ይጣላል። የጄራርድ ዲፓርዱ እና የብሪጂት ባርዶ ውሳኔ ይኼው ነው። ግብሩን አበዛችሁት ወይንም እኔ የምላችህን ካልፈፀማችሁ ማለት ሌላ ትርጉም የለውም። በግለሰብ ደረጃ፤ ጄራርድን ወይንም ብሪጅትን ትክክል አይደሉም ማለቴ አይደለም። ለዚህ ያበቃቸው፤ አስተዳደጋቸው፣ ሀገራዊ እሴታቸው፣ የፖለቲካ አመለካከታቸውና ከገንዘብ ጋር ያላቸው ፍቅር ወይንም ባጠቃላይ የንብረታቸው ብዛት አስተዋፅዖዎች አሏቸው።

የኔ አስተዳደግ፣ የፖለቲካ አመለካከቴና ሀገራዊ እሴቴ ተቃራኒውን ያሳዩኛል። ለዚህም ነው መደንገጤ። ያስገረመኝ ደግሞ፤ ከሩሲያ እየወጡ በዓለም ዙሪያ የተለያዩ ሀገሮችን ጥገኝነት የሚጠይቁ ሰዋች ቁጥር ከፍተኛ መሆኑ ነው። ፈረንሳይ ጥገኝነት ከሚጠይቁባት ሀገሮች አንዷ ናት። ይህ ደግሞ የእስራዔል ዝርያ ያላቸውን ብቻ አይደለም የሚያካትተው። ጄራርድ፡ “ሀገራችሁን ሩስያን አደንቃለሁ። ሕዝባችሁ፣ ታሪካችሁ፣ ጸሐፊዎቻችሁ . . . ባህላችሁና የአስተሳሰብ ሂደታችሁ . . . ሩስያ የታላቅ ዴሞክራሲ ሀገር ናት።”  አለ። በሀገራችን “የሚጥምህንማ አንተ ታውቃለህ!”  ያለውን ገበያተኛ አስታወሰኝ። ነገሩ እንዲህ ነው። አንድ የደለበ በግ ይዞ ገበያ የወጣ ሺያጭ፤ አንድ ገዢ መጥቶ፡ “ዋጋው ስንት ነው ይኼ በግ?” ይለዋል። በዚያን ጊዜ እንዲህ ነበር ማለቱ እኔን ከነ አባ ክልል ቢያስገባኝም፤ (ያኔ አንድ የአሜሪካ ዶላር ሁለት የኢትዮጵያ ብር ነበር ምንዛሬው) “ሃምሳ ብር ነው።” ይለዋል ሺያጭ። “እንዴ ይኼማ የጠገበ አህያ ያስገዛኝ የለም።” ይላል ገዢ የገንዘቡ መብዛት አስገርሞት። “ጌታው፤ የሚጥምህንማ አንተ ታውቃለህ!” በማለት የልቡን ቁስል በሰውዬው ጅንን ራሱን የማክበር ሰቀላው ላይ አዶለበት። የጄራርድን ዴሞክራሲያ ፍለጋ ወደ ሩስያ መንጎድ፤ በዚህ ዓይን ነው ያየሁት።

ከሞላ ጎደል ሁሉም ኢትዮጵያዊያን አላቸው ብዬ ከምገምተው ነገር አንዱ፤ ሀገራችንን ወዳድ መሆናችንን ነው። ገዥዎቻችንን ከሀገራችን ለይተን ነው የምናየው። ገዥዎቻችን እንዲህ አደረጉን እንጂ፤ ሀገራችን እንዲህ አደረገጭን ብለን ሀገራችንን አንወነጅላትም። ይኼን ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማሁት፤ ኢሳያስ ኢትዮጵያን እንዲጠሉ፤ “ኢትዮጵያ መጣችባችሁ!” እያለ፣ አውሮፕላን በሰማይ ስትመጣ፤ ኤርትራዊያንን ሲያስፈራራቸው ነው። እኛ ከዚህ የተለይን ነን። አመለካከታችንም እንዲሁ። “እናንተ የፈለጋችሁትን የምታደርጉባት የግል ንብረታችሁ አይደለችም።”  በማለት። ለዚህም ነው ገዥዎቻችንን የምንታገለው። ሀገራችን የሁላችንም ናት።

ጥር ፳ ፮ ቀን ፳ ፻ ፭ ዓመተ ምህረት

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule