• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ሁለት ፕሮፌሰሮች፡– ፍቅሬ ቶሎሳና ጌታቸው ኃይሌ

February 12, 2017 06:36 pm by Editor Leave a Comment

በአንድ ሰኮንድ ውስጥ ስንት ነገሮች ስንት ሁኔታዎች ይታያሉ?፣ ስንት ድርጊቶች፣ ስንት ሥራዎች ይፈጸማሉ? ስንት ሰዎች ይሞታሉ? ስንት ሰዎች ይወለዳሉ? … አንድ ሰኮንድ ባዘለው ጊዜ ውስጥ ብዙ ጥያቄዎች አሉ፤ በአንድ ደቂቃ ውስጥ ባለው ጊዜ ውስጥ ቢያንስ የስድሳ ሰኮንዶችን ያህል ጥያቄዎች ይፈለፈላሉ፤ በአንድ ሰዓት ውስጥ 60*60= 3600 እነዚህ ደግሞ በ24 ሰዓት ሲባዙ 86 400 ይሆናሉ፤ የሚሆኑትንና የሚደረጉትን ነገሮች ሁሉ መዝግቦ፣ የሚነገሩትን ነገሮች ሁሉ አጣርቶ ይዞ ለሚቀጥለው ትውልድ የሚያስተላልፍ አለ ወይ? የትናንትናውን ሃያ አራት ሰዓት በዝርዝር ማስታወስ የሚችል አለ ወይ? ጊዜውና መሣሪያው ያላችሁ የሳምንቱን፣ የወሩን፣ የዓመቱን ሰኮንዶችና ያቀፉትንና ያዘሉትን ጉዳዮች አጣርታችሁ ለማወቅና ‹‹ተረቱንና ታሪኩን›› ለመለየት ሞክሩ፡፡

እንደኔ የጂኦሎጂ ሀሁ የሚያውቅ ደግሞ ሌላም ጥያቄ ሊያቀርብ ይችላል፤ በጂኦሎጂ ታሪክ የሚቆጠረው በሚልዮን ዓመታት ነው፤ የዛሬ መቶ ሚልዮን ዓመት ምድር እንደዚህ ነበረች፤ ከዚያ በኋላ በዚህ፣ በዚህ ተለዋወጠች እያለ ይነግረናል፤ ተረት ነው የምንለው ወይስ ታሪክ? እንዲያውም አንድ እውነት ልንገራችሁ፤

አሜሪካ አኔ በተማርሁበት ዩኒቨርሲቲ አንድ በበረዶ ድንጋይ በዓለም የታወቀ ፕሮፌሰር ነበረን፤ አንድ ቀን ለመስክ ጥናት ወስዶን አንድ አነስ ያለ ሐይቅ ያለበትን ረባዳ መሬት ቁለቁል እያሳየን የድንጋይ በረዶው ከየት ተነሥቶ ወዴት ሲንሸራተት እንደነበረና ምን እንዳገደውና ሐይቁ እንዴት እንደተፈጠረ ነግሮን ሲጨርስ አጠገባችን ቆሞ ሲያዳምጥ የነበረ የአካባቢው ሰው ድምጹን ከፍ አድርጎ ‘ይህንን ሐይቅ የሠራነው እኛ ነንእኮ!’ አለ፤ የኛ ዓለም ያደነቀው ፕሮፌሰር ሁለቱንም እጆቹን ወደሰማይ ዘርግቶ፣ ‘ያውላችሁ የኔ ሀሳብ ብትንትኑ ወጣ!’ አለን! ታሪክን ተረት ማለት ተረት አያደርገውም፤ ተረትን ታሪክ ማለትም ታሪክ አያደርገውም፡፡

ከጥቂት ዓመታት በፊት የኢትዮጵያ ታሪክ ሊቃውንት ሁሉ ኢትዮጵያውያን ከአረብያ ፈልሰው የመጡ ናቸው እያልን ፈረንጆች የነገሩንን እናስተምር ነበር፤ ሁለመናችን ከአረቦች የመጣ መሆኑን አስተምረናል፤ አሁን አንድ ሌላ ፈረንጅ መጣና ‘የለም፣ ሰዎች ከኢትዮጵያ ወደአረብያ ፈለሱ እንጂ ከአረብያ ወደኢትዮጵያ አልፈለሱም፤ ኢትዮጵያ ሰጪ እንጂ ተቀባይ አልነበረችም፤’ ይለናል፤ የቱ ነው ተረት? የቱ ነው ታሪክ? አንዱ የኢትዮጵያ ታሪክ ሊቅ በቅርቡ በጻፈው የፊታውራሪ ሀብተ ጊዮርጊስ ታሪክ ውስጥ ‘አጼ ምኒልክ ወደደቡብ ሲስፋፉ’ ብሎ ይጀምራል፤ አጼ ሱስንዮስ ከሁለት መቶ ዓመታት በፊት ደቡብ እንደነበረ፣ አንድ ንጉሠ ነገሥትም ዘይላ አካባቢ እንደሞተ፣ የደቡብ እቴጌዎች እንደነበሩ ይነገራል፤ ታዲያ ተረቱ የቱ ነው? ታሪኩ የቱ ነው? ፈረንጅን ተከትሎ ማነብነብ የዘመኑ ባህል ሆነ፤ ጎፈሬን እኛ ስንጠላው ፈረንጅ አገር ገባና ስሙን ለውጦ አፍሮ ተብሎ መጣልን!

የፍቅሬ ቶሎሳን መጽሐፍ ከጊዜው የስደተኞች ፖሊቲካ ጋር አያይዘው የፖሊቲካ አስታራቂነት ተልእኮ የሚሰጡት ሰዎች የመጽሐፉ መሠረት የገባቸው አይመስለኝም፤ እኔንም ካላመለጠኝ መጽሐፉ ሁለቱን የዓለም መሠረታዊ ባላ — ቦታንና ጊዜን — አቀራርቦና አዋኅዶ የያዘ በመሆኑ ከጊዜያዊነት ውጭ መስሎ ይታየኛል፤ መጽሐፉ ለብዙዎቻችን ከባድ የሆነውም በዚህ ምክንያት ይመስለኛል፡፡

ስንት የፈረንጅ ተረቶችን ሳንጨነቅ ታሪክ ብለን አስተምረናል? ስንት የራሳችንን ታሪክ ተረት ብለን ጥለናል? ፍቅሬ ቶሎሳ ያቀረበው አዲስ ነገር ነው፤ አበሻ ደግሞ አዲስ ነገርን አይወድም፤ የፍቅሬን መጽሐፍ እኔ መሀከሉ ደርሼ መቆሜን ነግሬዋለሁ፤ ሰኮንዶቹን፣ ደቂቃዎቹንና ሰዓቶቹን፣ ቀኖቹንና ወሮቹን፣ ዓመቶቹን መንጥሮ ያላየ ሰው እንዴት ብሎ በምን መለኪያ ተረቱንና ታሪኩን በእርግጠኛነት መለየት ይችላል? ለመሆኑ የፍቅሬ ቶሎሳን መጽሐፍ ተረት ነው ለማለት የምንችለው ርእሱን በየት በኩል አልፈን ነው? እኔ መጽሐፉን አንብቤ አልጨረስሁትም፤ በሕይወቴ ጀምሬ መጨረስ ያቃተኝ መጽሐፍ የፍቅሬ ቶሎሳ ሁለተኛው ነው፤ ሌላው ከጀመርሁት ሃምሳ ዓመት የሚሆነው መጽሐፍ የፈረንሳዩ ፈላስፋ የዣ ፖል ሳርትር አንድ መጽሐፍ ነው፤ ሁለቱንም መጽሐፎች አንብቤ ሀሳብ ለመስጠት አለመቻሌ የኔ ጉድለት እንጂ የደራሲዎቹ አይደለም፡፡

በበኩሌ እንደፍቅሬ ያሉ ከያለበት ቃርመው፣ የራሳቸውን አእምሮ አስረግዘውና በምጥ አስጨንቀው አዲስ ነገርን የሚያቀርቡልንን ያበርታችሁ እላለሁ! ግን እንድንደርስባችሁ አለምልሙን!

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
የካቲት/2009

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule