• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው

November 27, 2024 11:31 am by Editor Leave a Comment

* ኃላፊዋ በዕለቱ አለመገኘታቸው “ለወደፊቱ እንዳይደገም” ማሳሰቢያ ተሰጣቸው

በዛሬው ዕለት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ወጪ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የ2015 /2016 በጀት አመት የፓስፖርት አገልግሎት አሰጣጥና ውጤታማነትን በተመለከተ የተከናወነ የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት እንዲሁም የ2015 የሂሳብ ኦዲት ሪፖርት ላይ ለመወያየት ስብሰባ ጠርቶ ነበር።

ነገር ግን የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት ስብሰባው ላይ ሳይገኙ መቅረታቸው ቁጣን ፈጥሯል።

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የሺእመቤት ደምሴ (ዶ/ር) ምን አሉ?

“በመሰረቱ ምክር ቤቱ ተመርምረው የቀረቡለትን የዋና ኦዲት ሪፖርቶችን ይፋዊ ውይይት የሚያደርግባቸው የመስሪያ ቤቱ የበላይ ኃላፊ ነው።

“እኔ የመጣችሁትን የተመርማሪ መ/ቤት ኃላፊዎች ኃላፊነታችሁን አከብራለሁ ነገር ግን ዋና ኃላፊ በኦዲት ሪፖርት ምርመራ ላይ መገኘት ግዴታ ነው።

“ዋና ኃላፊዋ በሀገር ውስጥ የሉም። ነገር ግን ደብዳቤያችን ከደረሳቸው በኋላ ነው የወጡት። ይህ ድርጊት ተገቢ አይደለም።

“እኛ ከ10 ቀን በፊት ነው የምናሳውቀው ከ10 ቀን በፊት የምናሳውቅበት የራሱ ምክንያት አለው። መገኘት የማይችሉ ከሆነ reschedule መደረግ ካለበት reschedule መደረግ አለበት አለበለዚህ ግን ችግር የለውም ባላቹ ሰዎች መካሄድ ይችላል ተብሎ ወደ ጎን የሚተው ተግባር አይደለም።

“ይሄ እኮ የመ/ቤቱ ቁልፍ ተግባር ነው።

“ምክር ቤቱ ሃብት ነው የሚሰጠው፣ ይህ ሃብት በአግባቡ፣ በህግ እና በስርዓት መዋሉን ማረጋገጥ መቆጣጠር ይፈልጋል በዛ በሚቆጣጠርበት ሰዓት ኃላፊነት የሰጣቸው አካል አለመገኘት ተገቢ አይደለም።

“በርካታ ስራዎች ሊኖሩ ይችላሉ ግን ከበርካታ ስራዎች የቅድሚያ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር ነው (በኦዲት ምርመራ ሪፖርቱ ላይ መገኘት)።

“ይህ የሚያመላክተው ለኦዲቱ የሰጣችሁትን ትኩረት ነው። ትኩረት መስጠታችሁ አንዱ ማሳያ ተገኝቶ ይሄን ተምሪያለሁ፣ ፈጽሚያለሁ፣ ይሄን አልፈጸኩም ብሎ ፊት ለፊት ያልፈጸመበትን ምክንያት ማስረዳት ከአንድ ኃላፊ የሚጠበቅ ነው። ለወደፊቱ እንዳይደገም አሳስባለሁ” ብለዋል።

ምንም እንኳን ዋና ኃላፊዋ ባይገኙም ስብሰባው ምክትል ዋና ዳይሬክተሮቹ ቢቂላ መዝገቡ እና ጎሳ ደምሴን ጨምሮ ሌሎችም አመራሮች በተገኙበት ተካሂዷል።

ምክትል ዋና ዳይሬክተሮቹ በተፈጠረው ነገር ይቅርታ ጠይቀው “ድጋሚ አይደገምም” ሲሉ ቃል ገብተዋል።

ዋና ኃላፊዋ መገኘት የማይችሉ ከሆነው ቀድመው መናገር ነበረባቸው ተብሏል።

በዚህ አይነት መንገድ (ዋና ኃላፊዋ በሌሉበት) ስብሰባውን ማድረግ የማይገባ ቢሆንም ከዋና ኦዲተር ጀምሮ፣ ከጠ/ሚ ፅ/ቤት ፣ ከተለያዩ ተቋማትም ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጊዜያቸውን መስዕዋት አድርገው “ዋና ተግባራችን ነው” ብለው ስለተገኙ ብቻ ስብሰባው መደረጉ ተገልጿል።

በዛሬው ስብሰባ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በ2015/2016 በጀት ዓመት የክዋኔ እና ሂሳብ ኦዲት ሲመረመር በርካታ ገድለቶች መገኘታቸው ተገልጿል።

ከሪፖርቱ በመነሳት ቋሚ ኮሚቴው በርካታ ጥያቄዎችን አቅርቧል። በጥያቄዎቹ ላይም የአገልግሎቱ ኃላፊዎች ምላሽ ያሉትን ሰጥተዋል።

“ዜጎች ምን ያህል እንደሚንገላቱ የአይን ምስክር ነኝ” – የሺእመቤት ደምሴ (ዶ/ር)

ዛሬ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት የፓስፖርት አገልግሎት አሰጣጥን በተመለከተ በተካሄደው የ2015/2016 የክዋኔ እና ኦዲት ሪፖርት ስብሰባ ላይ በመንግሥት ወጪ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በኩል ስለ ሰራተኞች ስነምግባር፤ ስለ ዜጎች እንግልት ተነስቷል።

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የሺእመቤት ደምሴ (ዶ/ር) መ/ቤቱን “ሁላችንም የምንረግጠው በር ነው ያላችሁ” ሲሉ ገልጸዋል።

“ነገር ግን ሁላችንም ተጠቂ / Victim የሆንበት ጉዳይ ነው እውነቱን ለመናገር” ሲሉ ተናግረዋል። ይህንን ያሉት ስለ ሰራተኞች ስነምግባር እና ስለ ተገልጋይ እንግልት ባነሱት ሃሳብ ነው።

በጉዳዩ ላይ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ኃላፊዎች ለምክር ቤቱ “አጃቢዎቻቸው፣ በቋንቋ፣ ቦታ ባለማወቅ … በተለያዩ ምክንያቶች አጅበዋቸው የሚመጡት እንጂ አገልግሎት ፈላጊዎቻችን አይደለም የሚንገላቱት” ብለዋል።

የምክር ቤት አባልና የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዋ ግን “እኔ ምስክር ነኝ እኔ ተንገላትቻለሁ” ሲሉ ተናግረዋል።

“እኔ ተንገላትቻለሁ፤ እኔ ተገፍቼ ወጥቻለሁ ያውም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መታወቂያ እያሳየሁ፤ ተጎትቼ ወጥቻለሁ ይህንን ከማንም አይን እማኝ አይደለም እኔ ላይ የደረሰ ነው። እኔ ይሄንን የምለው እኔ ተበድያለሁና እኔ ለምን ተበደልኩ ብዬ አይደለም” ብለዋል።

“እኔ ይህን ሃሳብ እያቀረብኩ ያለሁት ከኃላዬ ያለው ዜጋ ምን ያህል እንደሚንገላታ የአይን ምስክር ነኝ ለማለት ነው” ሲሉ አስረድተዋል።

“ይህንን ፈትሹት ፤ ሩቅ አይደለም የሩቅ ጊዜ ትዝታ አይደለም እየናገርኳችሁ ያለሁት ዛሬ ላይ እየተፈጸመ ያለ ነው” ብለዋል።

“አገልግሎት ፈላጊው ወረቀት ይዞ፣ የሞላውን ፕሪንት አድርጎ ይዞ በጣም እየተንገላታ፤ እየተገፋ ያለበት ሰዓት ነው ያ መሆን የለበትም” ሲሉም አሳስበዋል።

አክለው “ለዜጎቻችን መስጠት የምንችለውን አቅማችን የፈቀደውን አገልግሎት በአግባቡና በስርዓት ልንሰጥ ይገባል እንጂ ከዛም አልፎ መንገላታትን ልንጨምርበት አይገባም” ብለዋል።

መ/ቤቱ ያሉትን ቅርንጫፎች አቅም እንዲያጠናክር እና ዜጎችን ከሚያንገላታ አሰራር እንዲታረም በጥብቅ አሳስበዋል። (ቲክቫህ)

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Filed Under: Left Column, News Tagged With: Ethiopia Immigration, FDRE Immigration and Citizenship Service, Selamawit Dawit

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule