• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አሳዛኙ የትውልድ ህይወት በሳውዲ አረቢያ «ጂዛን» ከተማ!

January 13, 2014 10:57 pm by Editor 1 Comment

ጂዛን እየተባለ በሚጠራ የሳውዲ አረቢያ ግዛት ውስጥ ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ የሌለውን ጨምሮ ከ50 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን እንደሚኖሩ ይነገራል። የጂዛን ከተማ ሳውዲ አረቢያን ከየመን የሚያዋስን ከተማ እንደመሆኗ በባህር የሚመጡ ብዛት ያላቸው ኢትዮጵያውያን ወደ ሪያድ እና ጅዳ ከተማ ለማቅናት በመሸጋገሪያነት እንደሚጠቀሙባት ይነገራል።

በዚች የድንበር ከተማ አያሌ ኢትዮጵያውያን ጉዳዩ በወል በማይታወቅ ምክንያት ያለ ፍርድ ለ 4 እና 5 አመታት ታስረው የሚሰቃዩባት ከተማ መሆኗን የሚነገሩ ውስጥ አዋቂ ምንጮች ወደ ሃገር ለመመለስ ጥያቄ ያቀርቡ አያሌ ወገኖቻችንም በሪያድ የኢትዮጵያን ኤንባሲ እና ለጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት ያቀረቧቸው ጥያቄዎች እስካሁንም ምላሽ ባለማግኘቱ ህይወታቸው አደጋ ውስጥ መሆኑን ይናገራሉ ። ይህ በዚህ እንዳለ ከሁሉም በላይ እስከፊ አስከፊ በለው የሚገልጹት ምንጮች ከሶስት አመት በፊት በደረሰባት ከባድ የመኪና አደጋ ከወገቧ በታች በድን «ፓራላይዘድ» እንደሆነች የሚነገርላት ኢትዮጵያዊት እህት በዚህ ከተማ ውስጥ በተለምዶ «ኦድ ደርብ » እይተባለ በሚጠራ አካባቢ የሚገኝ አንድ ሆስፒታል ውስጥ ላለፉት ሶስት አመታት የአልጋ ቁራኛ ሆና ሃገር እና ወገን አልባ ሆና ሆስፒታል ውስጥ ለመኖር መገደዷ የአብዛኛውን ወገን ልብ የነካ መሆኑን ምንጮች አክለው ይገልጻሉ ።

በተለይ ስለጉዳዩ በሪያድ የኢትዮጵያ ኤንባሲ እና ለጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት መረጃ እንዳላቸው የሚናገሩ ወገኖች የመንግስት ባለስልጣናቱ ዝምታን መምረጣቸው ለወገን ህይወት ደንታ የሌላቸው ሃላፊነት የጎደላቸው መሆናቸውን ያሳያል ብለዋል። የተጠቀሰችው ኢትዮጵያዊት ወጣት በአካሏ ላይ ለደረሰው አስከፊ የመኪና አደጋ «ኢንሹራስ» ካሳ ሳታገኝ ይቅርታ እንዳደረገች ተድረጎ ሆስፒታል ውስጥ እንዳስፈረሞት የሚገልጹት ምንጮች ወጣቷ አደጋው ከደረሰባት ግዜ ጀምሮ ወደ ሃገር ለመግባት ያደረገችው ጥረት በሳውዲ አረቢያ የኢትዮጵያ የመግንስት ዲፕሎማቶች ድጋፍ እና ትብብር ማጣት ለበለጠ ስቃይ መዳረጓን ገልጸዋል። ወጣቷ በቤት ሰራተኝነት ከ አራት አመት በፊት ወደ ሳውዲ አረቢያ እንደገባች የሚነገርላት ወጣት ከዲጃ መሓመድ ሑሴን ትውልድ እና እድገቷ በአማራ ብ\ክ\መ\የኦሮሚያ ማህበረሰብ ዞን “ደዌ” ከሚባል አካባቢ በመሆኑ ከአረብኛ እና ከኦሮምኛ ቋንቋ ውጭ መናገር እንደማትችል የሚገልጹት ምንጮች ወጣቷ በአሁኑ ግዜ በተፈጠረው አጋጣሚ ህይወቴ ሳታልፍ ከቤተሰቦቼ ጋር እንድገናኝ እርዱኝ እያለች ብትማጸንም እስካሁን ምላሽ እንዳላገኘች ይናገራሉ።

ይህ በዚህ አንድ ወጣት ካሊዶ ኣሕመድ የተባለ ኢትዮጵያዊ በተመሳሳይ አደጋ በጂዛን ጀነራል ሆስፒታል ያልጋ ቁራኛ ከሆነ ድፍን ሁለት ኣመት ከስድስት ወራት እንዳስቋጠረ የሚናገሩ ምንጮች ወጣቱ ፓራላይዝ ከመሆኑም በላይ አይናገርም፣ አይሰማም፣ አያይም። እጅና እግሩ ከብረት አልጋው ጋር ተያይዞ እንድሚገኝ ገልጸዋል ። ወጣቱ ለረጅም ግዜ በመተኛት በሚፈጠር የሰውነት መቆሳሰል የተነሳ ወጣቱ በተጨማሪ በህክምናው አነጋገር \በድ ሶርስ\ በተባለ መጎሳቆሉን ይናገራሉ። ወጣቱን ሳይንሳዊው ህክምና አሳስሮ ወይም በቁሙ ገንዞ እንዳሰቀመጠው የሚናገሩ እነዚሁ የአይን እማኞች የጂዛን ትራፊክ ፅ\ቤት በተደጋጋሚ ለጅዳ እና ሪያድ የኢትዮጵያ ኤንባሲ ቢያሳውቁም እስካሁን ወጣቱን ማንም ያየው እንደሌለ ይናገራሉ ።

በቀርቡ ጅዳ እና በጂዛን ከተማ የሚኖሩ ከስደት ተመላሽ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንን እሮሮ አስመልክቶ በተከታታይ እየዘገበ በሚገኘው በጅዳ የጀርመን ራዲዮ ድምጽ «ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ» ዘገባ የተበሳጩ በጅዳ የኢትዮጵያ መንግስት ዲፕሎማቶች ጋዜጠኛውን ህገወጥ በሆነ መንገድ ወገኑንን በነጻ ለማገልገል በጸሃፊነት ተመርጦ ሲሰራ ከነበረበት ወገን ለወገን ከሚል አንድ ግዜያዊ ኮሚቴ ማገዳቸው የሚታወስ ነው።

Ethiopian Hagere ከጅዳ በዋዲ ብፌስቡክ በኩል ለጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ የላኩት

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Social Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Ephrem Alemayhu says

    April 24, 2014 10:49 pm at 10:49 pm

    ykfet

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule