• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አሳዛኙ የትውልድ ህይወት በሳውዲ አረቢያ «ጂዛን» ከተማ!

January 13, 2014 10:57 pm by Editor 1 Comment

ጂዛን እየተባለ በሚጠራ የሳውዲ አረቢያ ግዛት ውስጥ ህጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ የሌለውን ጨምሮ ከ50 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን እንደሚኖሩ ይነገራል። የጂዛን ከተማ ሳውዲ አረቢያን ከየመን የሚያዋስን ከተማ እንደመሆኗ በባህር የሚመጡ ብዛት ያላቸው ኢትዮጵያውያን ወደ ሪያድ እና ጅዳ ከተማ ለማቅናት በመሸጋገሪያነት እንደሚጠቀሙባት ይነገራል።

በዚች የድንበር ከተማ አያሌ ኢትዮጵያውያን ጉዳዩ በወል በማይታወቅ ምክንያት ያለ ፍርድ ለ 4 እና 5 አመታት ታስረው የሚሰቃዩባት ከተማ መሆኗን የሚነገሩ ውስጥ አዋቂ ምንጮች ወደ ሃገር ለመመለስ ጥያቄ ያቀርቡ አያሌ ወገኖቻችንም በሪያድ የኢትዮጵያን ኤንባሲ እና ለጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት ያቀረቧቸው ጥያቄዎች እስካሁንም ምላሽ ባለማግኘቱ ህይወታቸው አደጋ ውስጥ መሆኑን ይናገራሉ ። ይህ በዚህ እንዳለ ከሁሉም በላይ እስከፊ አስከፊ በለው የሚገልጹት ምንጮች ከሶስት አመት በፊት በደረሰባት ከባድ የመኪና አደጋ ከወገቧ በታች በድን «ፓራላይዘድ» እንደሆነች የሚነገርላት ኢትዮጵያዊት እህት በዚህ ከተማ ውስጥ በተለምዶ «ኦድ ደርብ » እይተባለ በሚጠራ አካባቢ የሚገኝ አንድ ሆስፒታል ውስጥ ላለፉት ሶስት አመታት የአልጋ ቁራኛ ሆና ሃገር እና ወገን አልባ ሆና ሆስፒታል ውስጥ ለመኖር መገደዷ የአብዛኛውን ወገን ልብ የነካ መሆኑን ምንጮች አክለው ይገልጻሉ ።

በተለይ ስለጉዳዩ በሪያድ የኢትዮጵያ ኤንባሲ እና ለጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት መረጃ እንዳላቸው የሚናገሩ ወገኖች የመንግስት ባለስልጣናቱ ዝምታን መምረጣቸው ለወገን ህይወት ደንታ የሌላቸው ሃላፊነት የጎደላቸው መሆናቸውን ያሳያል ብለዋል። የተጠቀሰችው ኢትዮጵያዊት ወጣት በአካሏ ላይ ለደረሰው አስከፊ የመኪና አደጋ «ኢንሹራስ» ካሳ ሳታገኝ ይቅርታ እንዳደረገች ተድረጎ ሆስፒታል ውስጥ እንዳስፈረሞት የሚገልጹት ምንጮች ወጣቷ አደጋው ከደረሰባት ግዜ ጀምሮ ወደ ሃገር ለመግባት ያደረገችው ጥረት በሳውዲ አረቢያ የኢትዮጵያ የመግንስት ዲፕሎማቶች ድጋፍ እና ትብብር ማጣት ለበለጠ ስቃይ መዳረጓን ገልጸዋል። ወጣቷ በቤት ሰራተኝነት ከ አራት አመት በፊት ወደ ሳውዲ አረቢያ እንደገባች የሚነገርላት ወጣት ከዲጃ መሓመድ ሑሴን ትውልድ እና እድገቷ በአማራ ብ\ክ\መ\የኦሮሚያ ማህበረሰብ ዞን “ደዌ” ከሚባል አካባቢ በመሆኑ ከአረብኛ እና ከኦሮምኛ ቋንቋ ውጭ መናገር እንደማትችል የሚገልጹት ምንጮች ወጣቷ በአሁኑ ግዜ በተፈጠረው አጋጣሚ ህይወቴ ሳታልፍ ከቤተሰቦቼ ጋር እንድገናኝ እርዱኝ እያለች ብትማጸንም እስካሁን ምላሽ እንዳላገኘች ይናገራሉ።

ይህ በዚህ አንድ ወጣት ካሊዶ ኣሕመድ የተባለ ኢትዮጵያዊ በተመሳሳይ አደጋ በጂዛን ጀነራል ሆስፒታል ያልጋ ቁራኛ ከሆነ ድፍን ሁለት ኣመት ከስድስት ወራት እንዳስቋጠረ የሚናገሩ ምንጮች ወጣቱ ፓራላይዝ ከመሆኑም በላይ አይናገርም፣ አይሰማም፣ አያይም። እጅና እግሩ ከብረት አልጋው ጋር ተያይዞ እንድሚገኝ ገልጸዋል ። ወጣቱ ለረጅም ግዜ በመተኛት በሚፈጠር የሰውነት መቆሳሰል የተነሳ ወጣቱ በተጨማሪ በህክምናው አነጋገር \በድ ሶርስ\ በተባለ መጎሳቆሉን ይናገራሉ። ወጣቱን ሳይንሳዊው ህክምና አሳስሮ ወይም በቁሙ ገንዞ እንዳሰቀመጠው የሚናገሩ እነዚሁ የአይን እማኞች የጂዛን ትራፊክ ፅ\ቤት በተደጋጋሚ ለጅዳ እና ሪያድ የኢትዮጵያ ኤንባሲ ቢያሳውቁም እስካሁን ወጣቱን ማንም ያየው እንደሌለ ይናገራሉ ።

በቀርቡ ጅዳ እና በጂዛን ከተማ የሚኖሩ ከስደት ተመላሽ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንን እሮሮ አስመልክቶ በተከታታይ እየዘገበ በሚገኘው በጅዳ የጀርመን ራዲዮ ድምጽ «ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ» ዘገባ የተበሳጩ በጅዳ የኢትዮጵያ መንግስት ዲፕሎማቶች ጋዜጠኛውን ህገወጥ በሆነ መንገድ ወገኑንን በነጻ ለማገልገል በጸሃፊነት ተመርጦ ሲሰራ ከነበረበት ወገን ለወገን ከሚል አንድ ግዜያዊ ኮሚቴ ማገዳቸው የሚታወስ ነው።

Ethiopian Hagere ከጅዳ በዋዲ ብፌስቡክ በኩል ለጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ የላኩት

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Social Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. Ephrem Alemayhu says

    April 24, 2014 10:49 pm at 10:49 pm

    ykfet

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule