• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዘጸአት ለኢትዮጵያ

February 17, 2015 08:26 am by Editor Leave a Comment

በኢትዮጵያ ምድር፥ ምኒልክን (ዮሴፍን) ‘ማያውቅ፥ አዲስ ንጉሥ መ’ቶ፣
“ለነፃነት” ብሎ፥ የነፃነትን ጧፍ፥ ረጋግጦ አጥፍቶ፣
“ከኔ ወዲያ ላሳር!”፥ አለን አፉን ሞልቶ፣
ያ’ባቶችን ክብር፥ አፈር መሬት ከ’ቶ።

ያገሬ ፈርዖን፥ ልቡ እጅግ ደንድኖ፣
የፈጣሪን ፈቃድ፥ እንዳይሰማ ሆኖ፣
“እንደ’ኔ ያለ ንጉሥ!”፥ እያለ ይጽናናል፣
የበትሩን ምሬት፥ በጠገበ ጉልበት፥ ከተማን ያጸናል።

ስንት አሮን ተላከ? ስንት ሙሴ መጣ?
“የሠራዊት ጌታ፥ ‘ህዝቤን ልቀቅ’ ይላል!”፥ የሚል ቃል ሊያወጣ፣
ስንት ምርጫ ሆነ፥ ስንት ምርጫ ሄደ፣
ደንዳናው ፈርዖን፥ በህዝብና ፍትህ፥ እንደተጓደደ።

ምልክቶች ታዩ፥ ታምራትም መጡ፣
ፈተናው ጸና እንጂ፥ የእብሪተኞችን ልብ፥ ቅንጣት አ’ለወጡ።
የባሰው መጣና፥ የ’እብራውያን’ በኩር፥ እየተሰደደ፣
መልአከ ሞት ጥላ ፥ ‘የፈርኦንን በኩር’፥ ካቻምና ወሰደ፣
ፈርዖን ልቡ ጸንቶ፥ ዘንድሮም ገፋበት፥ ህዝቡን እንዳራደ።

እናማ ህዝቤ ሆይ፣ ጊዜው እጅግ ቀርቧል፥ ነፃነት ሊመጣ፣
ጓዝ ስንቅህን ይዘህ፥ ከተስፋ ዳርቻ፥ ተሰብስበህ ውጣ፣
ማሳደዱ አይቀርም፥ ፈርዖን ከነጭፍራው፥ ይመጣል ሊቀጣ፣
ጥቂት ጭንቅ ይሆናል፥ የድል ቀን ሲመጣ።

ሆኖም ህዝቤ በርታ፥ በደርቅ መሬት ላይ፥ እንሻገራለን፣
ፈርዖን ተከትሎ፥ ወጥመድ ውስጥ ሲገባ፥ ዞረን እናያለን፣
ታዲያ የዛን ጊዜ፥ “እሰየው” አንልም፥ “እግዚኦ!” እንላለን፣
ጌታ በማረን ልክ፥ ለፈርዖን ጭፍራ፥ ምህረት እንሰጣለን።

አደባባይ ወ’ተን፥ “ይቅርታ”ን ዘምረን፣
በደሎቻችንን፥ ፍፁም ተማምረን፣
ከባቢሎን ወንዞች፥ ወዲህ ተሰብስበን፣
በኢትዮጵያ (በጽዮን) ቅጥር ውስጥ፥ እንዳበባ አብበን፣
ለፍቅር እናልፋለን፥ ለተተኪው ትውልድ፥ ፍቅርን አስረክበን።

ጽናልኝ አገሬ፥ ባህር ይከፈላል፥ አዲስ ቀን ይመጣል፣
የእግዚአብሄር ህዝብም፥ በእረፍቱ መስክ ላይ፥ ተዘ’ሎ ይቀመጣል።

03 Feb 2015

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule