• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዘጸአት ለኢትዮጵያ

February 17, 2015 08:26 am by Editor Leave a Comment

በኢትዮጵያ ምድር፥ ምኒልክን (ዮሴፍን) ‘ማያውቅ፥ አዲስ ንጉሥ መ’ቶ፣
“ለነፃነት” ብሎ፥ የነፃነትን ጧፍ፥ ረጋግጦ አጥፍቶ፣
“ከኔ ወዲያ ላሳር!”፥ አለን አፉን ሞልቶ፣
ያ’ባቶችን ክብር፥ አፈር መሬት ከ’ቶ።

ያገሬ ፈርዖን፥ ልቡ እጅግ ደንድኖ፣
የፈጣሪን ፈቃድ፥ እንዳይሰማ ሆኖ፣
“እንደ’ኔ ያለ ንጉሥ!”፥ እያለ ይጽናናል፣
የበትሩን ምሬት፥ በጠገበ ጉልበት፥ ከተማን ያጸናል።

ስንት አሮን ተላከ? ስንት ሙሴ መጣ?
“የሠራዊት ጌታ፥ ‘ህዝቤን ልቀቅ’ ይላል!”፥ የሚል ቃል ሊያወጣ፣
ስንት ምርጫ ሆነ፥ ስንት ምርጫ ሄደ፣
ደንዳናው ፈርዖን፥ በህዝብና ፍትህ፥ እንደተጓደደ።

ምልክቶች ታዩ፥ ታምራትም መጡ፣
ፈተናው ጸና እንጂ፥ የእብሪተኞችን ልብ፥ ቅንጣት አ’ለወጡ።
የባሰው መጣና፥ የ’እብራውያን’ በኩር፥ እየተሰደደ፣
መልአከ ሞት ጥላ ፥ ‘የፈርኦንን በኩር’፥ ካቻምና ወሰደ፣
ፈርዖን ልቡ ጸንቶ፥ ዘንድሮም ገፋበት፥ ህዝቡን እንዳራደ።

እናማ ህዝቤ ሆይ፣ ጊዜው እጅግ ቀርቧል፥ ነፃነት ሊመጣ፣
ጓዝ ስንቅህን ይዘህ፥ ከተስፋ ዳርቻ፥ ተሰብስበህ ውጣ፣
ማሳደዱ አይቀርም፥ ፈርዖን ከነጭፍራው፥ ይመጣል ሊቀጣ፣
ጥቂት ጭንቅ ይሆናል፥ የድል ቀን ሲመጣ።

ሆኖም ህዝቤ በርታ፥ በደርቅ መሬት ላይ፥ እንሻገራለን፣
ፈርዖን ተከትሎ፥ ወጥመድ ውስጥ ሲገባ፥ ዞረን እናያለን፣
ታዲያ የዛን ጊዜ፥ “እሰየው” አንልም፥ “እግዚኦ!” እንላለን፣
ጌታ በማረን ልክ፥ ለፈርዖን ጭፍራ፥ ምህረት እንሰጣለን።

አደባባይ ወ’ተን፥ “ይቅርታ”ን ዘምረን፣
በደሎቻችንን፥ ፍፁም ተማምረን፣
ከባቢሎን ወንዞች፥ ወዲህ ተሰብስበን፣
በኢትዮጵያ (በጽዮን) ቅጥር ውስጥ፥ እንዳበባ አብበን፣
ለፍቅር እናልፋለን፥ ለተተኪው ትውልድ፥ ፍቅርን አስረክበን።

ጽናልኝ አገሬ፥ ባህር ይከፈላል፥ አዲስ ቀን ይመጣል፣
የእግዚአብሄር ህዝብም፥ በእረፍቱ መስክ ላይ፥ ተዘ’ሎ ይቀመጣል።

03 Feb 2015

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule