• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዘጸአት ለኢትዮጵያ

February 17, 2015 08:26 am by Editor Leave a Comment

በኢትዮጵያ ምድር፥ ምኒልክን (ዮሴፍን) ‘ማያውቅ፥ አዲስ ንጉሥ መ’ቶ፣
“ለነፃነት” ብሎ፥ የነፃነትን ጧፍ፥ ረጋግጦ አጥፍቶ፣
“ከኔ ወዲያ ላሳር!”፥ አለን አፉን ሞልቶ፣
ያ’ባቶችን ክብር፥ አፈር መሬት ከ’ቶ።

ያገሬ ፈርዖን፥ ልቡ እጅግ ደንድኖ፣
የፈጣሪን ፈቃድ፥ እንዳይሰማ ሆኖ፣
“እንደ’ኔ ያለ ንጉሥ!”፥ እያለ ይጽናናል፣
የበትሩን ምሬት፥ በጠገበ ጉልበት፥ ከተማን ያጸናል።

ስንት አሮን ተላከ? ስንት ሙሴ መጣ?
“የሠራዊት ጌታ፥ ‘ህዝቤን ልቀቅ’ ይላል!”፥ የሚል ቃል ሊያወጣ፣
ስንት ምርጫ ሆነ፥ ስንት ምርጫ ሄደ፣
ደንዳናው ፈርዖን፥ በህዝብና ፍትህ፥ እንደተጓደደ።

ምልክቶች ታዩ፥ ታምራትም መጡ፣
ፈተናው ጸና እንጂ፥ የእብሪተኞችን ልብ፥ ቅንጣት አ’ለወጡ።
የባሰው መጣና፥ የ’እብራውያን’ በኩር፥ እየተሰደደ፣
መልአከ ሞት ጥላ ፥ ‘የፈርኦንን በኩር’፥ ካቻምና ወሰደ፣
ፈርዖን ልቡ ጸንቶ፥ ዘንድሮም ገፋበት፥ ህዝቡን እንዳራደ።

እናማ ህዝቤ ሆይ፣ ጊዜው እጅግ ቀርቧል፥ ነፃነት ሊመጣ፣
ጓዝ ስንቅህን ይዘህ፥ ከተስፋ ዳርቻ፥ ተሰብስበህ ውጣ፣
ማሳደዱ አይቀርም፥ ፈርዖን ከነጭፍራው፥ ይመጣል ሊቀጣ፣
ጥቂት ጭንቅ ይሆናል፥ የድል ቀን ሲመጣ።

ሆኖም ህዝቤ በርታ፥ በደርቅ መሬት ላይ፥ እንሻገራለን፣
ፈርዖን ተከትሎ፥ ወጥመድ ውስጥ ሲገባ፥ ዞረን እናያለን፣
ታዲያ የዛን ጊዜ፥ “እሰየው” አንልም፥ “እግዚኦ!” እንላለን፣
ጌታ በማረን ልክ፥ ለፈርዖን ጭፍራ፥ ምህረት እንሰጣለን።

አደባባይ ወ’ተን፥ “ይቅርታ”ን ዘምረን፣
በደሎቻችንን፥ ፍፁም ተማምረን፣
ከባቢሎን ወንዞች፥ ወዲህ ተሰብስበን፣
በኢትዮጵያ (በጽዮን) ቅጥር ውስጥ፥ እንዳበባ አብበን፣
ለፍቅር እናልፋለን፥ ለተተኪው ትውልድ፥ ፍቅርን አስረክበን።

ጽናልኝ አገሬ፥ ባህር ይከፈላል፥ አዲስ ቀን ይመጣል፣
የእግዚአብሄር ህዝብም፥ በእረፍቱ መስክ ላይ፥ ተዘ’ሎ ይቀመጣል።

03 Feb 2015

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule