• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እያፈገፈገ ያለውን ሽፍታ የሚመራው ፃድቃን ጦርነቱ “በቀናት፣ ግፋ ቢል በሳምንታት ይጠናቀቃል” አለ

October 14, 2021 09:17 am by Editor Leave a Comment

የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግንባር / ትህነግ አማጺ ሃይል መሪ የሆነው ጻድቃን ገብረትንሳይ ጦርነቱ እንደማይራዘም አመለከተ። አዲስ ተጀመረ የተባለውን ጦርነት “የቀናት ጉዳይ ነው፣ ግፋ ቢል በሳምንታት ውስጥ ይጠናቀቃል” ሲል የተናገረው ለኒውዮርክ ታይምስ ነው። የትግራይ ሕዝብ የዕድሜ ልክ ጠላት ሲሉ የጠራቸው ኢሳያስ መወገድ እንዳለባቸው ለዓለም ማህበረሰብ አስታውቋል።

የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት እስካሁን ማጥቃት አለመጀመሩን፣ ነገር ግን ዝግጅቱን አጠናቆ መመሪያ እየጠበቀ መሆኑንና ማጥቃት ከጀመረ “ድረሱልኝ” የሚል ጊዜ የሚሰጥ እንዳልሆነ ከዚህ በፊት ሲነገር ነበር። ትህነግ ያወጣውን የድረሱልኝ ጥሪ ተከትሎ መከላከያ ይህንን ቢልም የተለያዩ ሃላፊዎችና ዓለም ዓቀፍ ሚዲያዎች ደጋግመው ጥቃት መጀመሩን እያስታወቁ ነው። የአየር ሃይል አዛዥም በባንዲራ ቀን አየር ኃይል “ጠላትን እየቀጠቀጠ ነው” ብለዋል።

የሽፍታው መሪ ጻድቃን ጦርነቱ የቀናት፣ ግፋ ቢል የሳምንታት ጉዳይ መሆኑንን ሲናገር ከማን ወገንና እንዴት ገምግሞት እንደሆነ ዘገባው ጥልቅ ትንተና አልሰጠም። ነገር ግን ጻድቃን “… Airstrikes took out most of the Tigrayan artillery and forced its troops to retreat into the remote countryside.” ማለቱን ጋዜጣው ዘግቧል። በአየርና በምድር ከባድ መሳሪያ ድብደባ የተነሳ ከባድ መሳሪያና ሽግታው ስብስብ ራቅ ወዳለው የትግራይ ገጠራማ አካባቢ እንዳፈገፈገ ፃድቃን ሳይደብቅ ተናግሯል። (ሩቅ ገጠራማ የተባለው ቆላ ተንቤን ስለመሆኑ በግልጽ አልተገለጸም)።

ኒውዮርክ ታይም የኢትዮጵያ መንግሥት በትህነግ ሃይል የተያዙ ስፍራዎችን ለማስለቀቅ ማጥቃት መጀመሩን “አማጺ” ሲል የሚጠራቸው የትህነግ ሃላፊዎችና የምዕራብ ዲፕሎማቶች እንዳረጋገጡለት ይገልጻል። ከመንግሥት ወገን ምንም መረጃ ማግኘት እንዳልቻለና በመገናኛ እጥረት ሳቢያ በዝርዝር ማቅረብ እንዳልቻለ አመላክቷል።

የመንግስት ቃለ አቀባይ የሆኑት ቢለኔ ስዩም “መንግስት በመላው አገሪቱ ያሉትን ዜጎቹን ከሽብር ተግባራት የመጠበቅና የመከላከል ሃላፊነት አለበት” ሲሉ ለፍራንስ 24 መናገራቸውን በርካታ መገናኛዎች መግለጻቸው ይታወሳል።

የሽፍታው የትግራይ ኃይል አመራር ጻድቃንን በስክል ማናገሩን የጠቀሰው የኒውዮርክ ታይም ዘገባ እንደሚያስረዳው የኢትዮጵያ መከላከያ ሃይል ድሮን፣ ከባድ መሳሪያና ተዋጊ ጀቶችን ተጠቅሞ በትግራይ አማጺ ሃይል ላይ ጥቃት የጀመረው ባለፈው ዓርብ ዕለት ነው ብሏ።

“ሰኞ” አለ የሽፍታው መሪ ጻድቃን “በሺህ የሚቆጠሩ የመከላከያ ሰራዊት ሰኞ የምድር ውጊያ ጀመሩ”፤ አክሎም “ጠላት” በማለት የጠራው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ለወራት ሲዘጋጅ መቆየቱን አመልክቶ “መጪው ጦርነት ለአገሪቱ ወሳኝ ጊዜ ነው” ሲል ተንብይዋል። እነሱም በተመሳሳይ ሲዘጋጁ እንደነበር አስታውቋል።

ስለጦርነቱ ወሳኝነት ያነሳው የወንበዴው መሪ፣ የጦርነቱ ውጤት ወይም መደምደሚያ ወታደራዊ፣ ፖለቲካዊና ዲፕሎማሲያዊ እንደሚሆን አመልክቷል ። ይህንን ሲል ግን ምን ለማለት እንደሆነ ዝርዝሩን ዘጋቢው አልጠየቀም። “ጦርነቱ የሚራዘም አይመስለኝም። የቀናት ጉዳይ ነው። ምናልባትም ሳምንታት” በማለት ፃድቃን ቀን በመቁረጥ ተንብዮዋል። “I don’t think this will be a protracted fight — a matter of days, most probably weeks.”

የትህነግ ቃል አቀባይ ጌታቸው ልክ እንደ ጻድቃን መደብደባቸውን በተደጋጋሚ በመግለጽ ለጦርነት አመቺ የሆነ ገዢ መሬቶችን እንደያዙ ማስታወቁ አይዘነጋም። በሰሜን ወሎ ያሉ የአካባቢውን አስተዳደሮች ያነጋገረው የጀርመን ድምጽ እንዳረጋገጠው የትህነግ ሃይል (በነሱ አባባል የተረፈው) ከተማ እያወደመ፣ ያልቻለም እየሸሸ መሆኑንና ጥቃቱ ተጠናክሮ መቀጠሉን ማስታወቃቸው፣ የትግራይ የጀርመን ድምጽ ባልደረባ በጉዳዩ ላይ አስተያየት እንዳላከለ ይታወሳል።

ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ላይ በየአቅጣጫው የተከፈተውን ዘመቻ በአሉታዊ ጎኑ አሰባስቦ ለዜናው ማዳመቂያነት ኢትዮጵያ ላይ ለተከፈተው የድራማ ማስዋቢያነት ይጠቅመው ዘነድ የሰገሰገው የኒውዮርክ ታይም ዘገባ ኢትዮጵያ ከኢራን፣ ከቱርክና ከቻይና ድሮኖችን በመግዛት በደንብ መታጠቋን ገልጿል። አንድ የምዕራብ ባለሥልጣን እንደነገሩት ጠቅሶ ባለፉት ስድስት ሳምንታት ብዛት ያለው የግዙፍ ካርጎ በረራ ከአረብ ኢምሬትስ ወደ ኢትዮጵያ መጓጓዙን ኒውዮርክ ታይም አመልክቷል። አስከትሎም ጻድቃን አረብ ኢምሬትስን ቀደም ሲልም ሆነ አሁን ዕርዳታ ማድረጓን ማውገዙ አትሟል። የኢሚሬትስ ባለስልጣናት ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ እንዳልሆኑም አስታውቋል።

ጋዜጣው የወቅቱን የትህነግን ሁኔታ ሲያስረዳ “… Airstrikes took out most of the Tigrayan artillery and forced its troops to retreat into the remote countryside.”ብሏል ። የአየር ጥቃቱ አብዛኛውን ከባድ መሳሪያና ሰራዊታቸውን ወደ ሩቅ ገጠራማ ስፍራ እንዲያሸሹና እንዲያፈገፍጉ እንዳደረጋቸው ጻድቃን ለኒውዮርክ ታይም ተናግሯል።

“የትግራይ የዘመናት ጠላት” ሲል የኤርትራን ፕሬዚዳንት ኢሳያስን የጠቀሰው ጻድቃን “ኢሳያስና ሰራዊታቸው ለቀጣናው መርዝ ናቸው” ብሏል። “If the international community is earnestly looking for a peaceful solution, a settlement will not happen without taking care of Isaias.” አያይዘውም “ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ሰላማዊ መፍትሔ ለማግኘት ከልብ የሚፈልግ ከሆነ ፣ ቅድሚያ ኢሳያስን መላ/ ሊያስወግዷቸው ይገባል” የሚል መልዕክት አስተላልፏል።

በስልክ ጻድቃንን ያናገረው የናይሮቢው ዘገቢ ስጋና ደሙን በፍለገው ቦታ እየቀላቀለ ባተመው ጽሁፍ “አሁን ትልቁ ጥያቄ የኤርትራ ሃይሎች ዳግም ኢትዮጵያን ይረዱ ይሆን የሚለው ነው” ሲል ይጠይቅና፣ ሁለት የምዕራብ አገር ባለሥልጣናት እንደነገሩት ጠቆም አድርጎ የኤርትራ ሃይሎች አሁን ላይ (ከ1983 በኋላ ወደትግራይ እንድትቀላቀል የተደረገችው) ሁመራ እንደሚገኙ አንዳንዶችም አማራ ክልል እንደዘለቁ ገልጿል። ዘጋቢው ይህ ቢልም ጻድቃን የኤርትራ ሰራዊትን አስመልክቶ ያለው ነገር የለም። ጌታቸውም “የኤርትራ ሰራዊት ስለመኖሩ እርግጠኞች አይደለንም” ሲል ለፍራንስ 24 አስታወቋል።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News Tagged With: endf, ethiopian terrorists, operation dismantle tplf, tplf terrorist

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule