• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ወግ ቀማሪው ደራሲ መስፍን ሀብተማርያም አረፉ

July 15, 2014 12:19 am by Editor 2 Comments

ከአቶ ሀብተማሪያም ሞገስና ከወ/ሮ ደስታ አየለ በ1935 ዓ.ም የተወለዱት ደራሲ መስፍን ሀብተማርያም በ 71 ዓመታቸው በአዲስ አበባ ከተማ አረፉ።

ደራሲ መስፍን በልጅነታቸው ባህላዊ የቤተ ክህነት ትምህርት የተማሩ ሲሆን ፣  በሞጆና በአንቦ የአንደኛና የሁለተኛ ደራጃ ትምህርታቸውን አጠናቀዋል። በወቅቱ ቀዳማዊ ኃይለስላሴ ዩኒቨርስቲ ተብሎ በሚጠራው የትምህርት ተቋምም በመግባት በቋንቋዎችና ሥነ-ፅሁፍ ክፍል በማዕረግ በቢኤ ዲግሪ ተመርቀዋል።በመቀጠልም ካናዳ በሚገኘው ቫንኩበር ከተማ በመሄድ ዪኒቨርስቲ ብሪቲሽ ኮሎምብያ ገብተው የፈጠራ ሥነ- ፅሁፍ የማስተር ድግሪ አግኝተዋል።

ደራሲ መስፍን ሀብተማሪያም  አገራቸው ከተመለሱ በኋላ በአማርኛ ቋንቋ በኢልብወለድ አጻጻፍ የትምህርት መስክ በተለያዩ ቦታዎች አስተምረዋል በአዲስ አበባ ዪኒቨርስቲም በቋንቋዎች ጥናት ተቋም የስነጽሁፍ ኮርሶችን በመስጠት ቆይተዋል። ከዚህም በተጨማሪ በኢትዮጵያ ሬድዮና በኩራዝ አሳታሚ ድርጅትም ሰርተዋል።

በህዝብ ዘንድ ከሚታወቁባቸው ድርሰቶቻቸው መካከል የቡና ቤት ስዕሎችና ሌሎች ወጎች፣አዜብና ሌሎች አጫጭር ልብወለዶች፣ዓውደ አመት እና የለሊት ድምጾችና ሌሎች ወጎች ቅድሚያውን ስፍራ የያዙ ሲሆኑ።በሬዲዮና በቴሌቪዢን የሚነበቡ ምርጥ ስራዎች ነበሯቸው።

ደራሲ መስፍን የሚጽፏቸው ጽሁፎች ከትምህርት ሰጪነታቸው እኩል የማዝናናትም ኃይል እንዳላቸው የሚመሰክሩት አንባብያን ብቻ ሳይሆኑ ደራሲያኑም ጭምር ነበሩ።በተለይም ባለቅኔ ደራሲና መምህር  ደበበ ሰይፉ ይበልጥ አድናቂያቸው እንደነበሩ ይነገራል።እዲሁም  የሳቸውን ሥራ በመመርኮዝ የመመረቂያ ጽሁፍ ያቀረቡም ብዙዎች ናቸው።

ደራሲው በራሳቸው ፈቃድ ስራቸውን ለቀው ከሥነ-ጽሁፍ  ሙያ ጋር የተያያዙ ልዩ ልዩ ስራዎች በመስራት የቆዩ ሲሆን ሐምሌ 6 ቀን 2006 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል። ጋዜጠኛ ደራሲና አርታኢ  መስፍን ሐብተማርያም ባለትዳርና የአምስት ልጆች አባት ነበሩ። (ለጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ዜናውን የላኩት ወለላዬ ከስዊድን ናቸው)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Berry says

    July 7, 2022 02:57 am at 2:57 am

    I would like to be notified of new articles

    Reply
    • Editor says

      July 7, 2022 10:06 am at 10:06 am

      When you open an article/news on the bottom right corner you will see a subscription link. Please sign up there.

      Thanks

      Editor

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule