• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በኢትዮጵያ የኤርትራ ስደተኞች የትጥቅ ትግሉን ለመቀላቀል ወሰኑ

May 23, 2014 02:54 am by Editor 1 Comment

በሺህ የሚቆጠሩ የኤርትራ ስደተኞች የፕሬዚዳንት ኢሳያስን አስተዳደር በትጥቅ ትግል ለማስወገድ ጠመንጃ ካነሱ ተቃዋሚዎች ጋር ለመቀላቀል መወሰናቸውን ሱዳን ትሪቢውን ገለጸ። ውሳኔው የተላለፈው ኤርትራ ለ23ኛ ዓመት ድል በዓልን ተንተርሶ ነው።

ሱዳን ትሪቢውን እንዳለው የኤርትራን ስደተኞች መግለጫ በመጥቀስ እንደዘገበው ኢሳያስ አፈወርቂ ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ አገሪቱን በአንድ ፓርቲ “በረግጠህ ግዛው” አስተዳደር ላለፉት 23 ዓመታት ገዝተዋል። ተያይዞም የአስመራው አገዛዝ በአገሪቱ ዴሞክራሲን፣ የሰብአዊ መብትን፣ ነጻነትን ማጎናጸፍ ባለመቻሉ ስርዓቱ በዚህ መቀጠል እንደሌለበት መስማማታቸውን አመልክቷል።

“ከነጻነት” ማግስት የኤርትራ ተወላጆች እጣ ፈንታቸው ስደት፣ መሰወር፣ ጭቆና፣ እስር፣ ውርደት፣ ማስፈራራት እንደሆነ በመግለጫቸው ያመለከቱት ስደተኞች፣ “የኤርትራ ምድር እንጂ ህዝቦቿ ነጻ አልወጡም” ብለዋል። ጨቋኙ የኤርትራ አገዛዝ አሁንም በዜጎቹ ላይ አረመኔያዊ ተግባሩን ስለገፋበት ጊዜው በህብረት ወታደራዊ ርምጃ የሚወሰድበት እንደሆነ ጠቁመዋል።

ሜይ 22፣ 2014 የወጣው የሱዳን ትሪቢውን ዜና ከላይ በተጠቀሱት ምሬቶች ሳቢያ በኮሌጅ የሚገኙ በመቶዎች የሚቆጠሩ ስደተኞችም ትግሉን ጠመንጃ በማንሳት እንደሚቀላቀሉ ማረጋገጣቸውን አመልክቷል።

“በዲሞክራሲያዊ መርህ የሚመራ መንግስት በኤርትራ በተአምር ይመሰረታል ብለን መጠበቅ አንፈልግም” ማለታቸውን የጠቆመው ሱዳን ትሪቢውን፤ ባለፉት አስር ኣመታት የኤርትራ የጦር ሰራዊት አባላት፣ የባህር ሃይል፣ ጨምሮ በ100 ሺህዎች የሚቆጠሩ የኤርትራ ተወላጆች ወደ ኢትዮጵያ፣ ሱዳን፣ ጅቡቲና የመን መሰደዳቸውን ዘግቧል።

የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ኮሚሽን የአዲስ አበባ ተወካይ የሆኑትን ኪሱት ገብረእግዚአብሔርን ጠቅሶ ዜናው እንደ ገለጸው እስከ ሚያዚያ (ኤፕሪል) መጨረሻ ወደ ኢትዮጵያ የተሰደዱት የኤርትራ ተወላጆች 92,460 መሆናቸውን ዘግቧል፡፡

በአማካይ ቁጥራቸው 2000 የሚጠጋ የኤርትራ ዜጎች በየወሩ የኢትዮጵያን ድንበር እየተሻገሩ እንደሚገቡ፣ እነርሱም ከ18 – 50 ዓመት እድሜ ያላቸው ሁሉ እንዲሳተፉ የሚያስገድደውን ብሔራዊ ውትድርና የሚሸሹ መሆናቸውን ያመለከቱት ሃላፊ፣ ስደተኞቹ ከአስገዳጁ የወታደራዊ አገልግሎት ሌላ የፖለቲካ ጭቆና ሽሽት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚያሰድዳቸው ተናግረዋል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    May 25, 2014 12:08 am at 12:08 am

    >>በምሥራቅ አፍሪካ ቀንዱን አሹሎ ጦርነት የሚያሻ ድንቅ ሀገርና ሕዝብ! ግን እኛ በሰው ሀገር ሉዓላዊነት ጣልቃ አንገባም ብለን አልነበር!? ህወአት አቶ ኢሳያስን ራዕይ ሲያስፈፅም ኤርትራ ተቃዋሚ የአቶ መለስን ራዕይ ሊያስፈፅም ነው!?
    **Ethiopia and Ertiria “one-party state which is considered as one of the most repressive regimes in the world.

    **the regimes in Asmara and in Addis Ababa have failed to bring democracy, human rights and freedom to its people and they don’t want to see the regime prolonging its grip on power.

    ***During the past 23 years become the victim of executions, imprisonment, disappearances, harassment and intimidation.(source awramba times bay Tesfa-Alem Tekle)

    ***In Ethiopia alone, there are 92,460 Eritrean refugees at end of April,2014 Kisut Gebregzabiher a United Nations refugee agency (UNHCR) representative in Addis Ababa told Sudan Tribune.Ethiopia had 150,000refugees only in soudi Arabia.

    ***An average of 2,000 Eritreans cross into Ethiopia every month fleeing political repression or to escape military service which is mandatory to all citizens aged between 18 and 50 and can last a lifetime.(what about Ethiopians in four directions fleed the country every day ?)

    ***International human rights organisations say that Eritrea and Ethioia stands amongst world’s top worst human rights and press freedom records. The regimes are also accused of turning the country into a “giant prison”.(kaliti,klinto)Ethiopia bekage!

    >>>welcome to famaily, group, collective ledereship,the same teacher one book many kaders and blood suckers opportunist (elite) abusing innocent and poor people.(ከኢሳያስ አፈወርቂ ጋር ተቀምጦ መነጋጋር አንድ ቤተ መፃሕፍት ቤት ውስት ውሎ እንደማደር ነው” ያለው የህወአት ሊቅ፣ የኢህአዴግ አዛዥ፣ የብሔር ብሔረሰቦች ፈጣሪ ማን ነበር?

    ***In Ertirea there are up to 10,000 political prisoners languishing in the country’s harsh and secret detention centers, which are sometimes shipping containers.(wow! እሥር ቤቱ ኦሮምኛ ይናገራል ያለው የህወአት ፈላስፋ ማን ነበር!?)
    ***The Eritrean refugees in Ethiopia further called up on those forces of change within the Eritrean(Ethiopian) ruling party, including the army to join them in the struggle to topple the regime so that democratic change is achieved.the two nations will be free. peace love a better life for mutul benefit in 21st centuary.
    **ራሳችን አንቅልፍ ተኝተን ለጎረቤት ኤርትራ፣ ሱዳን፣ ጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ሱማልያ እንቅልፍ ያጣነው፣ለራሳችን የሻማና የጧፍ ጉልበት ለእነሱ የኤሌትሪክ ኀይል ሆነን ሕዝባችንን የምናሸብረው ለመሆኑ አሜሪካና አውሮፓውያን ስንት ቢከፍሉን ነው? ሰበር ዜና “ግንቦት ፳ ሺ፳ የአካባቢው አሸባሪና የቀጣናው አተራማሽ አቶ ኢሳያስ አፈወርቂ የኅያለመለስን ራዕይ አፈፃፀም ተቃውመው ለብሔር ብሄረሰቦች እና በሊዝና በኢንቨስትመንት ሀገሪቷን ለተቀራመቱ(ሕዝቦች) እንዲሁም ከትጥቅ ትግሉ ጀምሮ አሁንም በኢህአዴግ ከፍተኛ አመራር ላይ ላሉ ለኤርትራውያንና ትውልደ ኤርትራውያን ዕድገትና ብልፅግና ሲባል እራሳቸው ለማስቀጠል በቁጭት ተነሰሳስተው ከዛሬ ጀምሮ የምኒሊክን ቤተመንግስት የራሳቸው አድርገው ተቆጣጥረውታል።ታዘበኝ በለው!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm
  • የፋሲል ግንብ እድሳት እንዴት ተካሄደ? የመንጣቱ ምክንያት? January 23, 2025 03:41 pm
  • ታሪካዊዉ የፋሲል ቤተመንግሥት ለምን ነጣ? January 23, 2025 03:04 pm
  • የኢትዮጵያ አየር መንገድ በተወልደ አስተዳደር ዘመን ለተሠራ ስህተት 425ሺ ዶላር ተቀጣ December 14, 2024 01:44 am
  • በትግራይ ከሞትና ከአካላዊ ጉዳት የተረፉት ለስደት ተዳርገዋል November 27, 2024 12:09 pm
  • የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አሠራሩን እንዲያርም ጥብቅ መመሪያ ተሰጠው November 27, 2024 11:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule