• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በኢትዮጵያ የኤርትራ ስደተኞች የትጥቅ ትግሉን ለመቀላቀል ወሰኑ

May 23, 2014 02:54 am by Editor 1 Comment

በሺህ የሚቆጠሩ የኤርትራ ስደተኞች የፕሬዚዳንት ኢሳያስን አስተዳደር በትጥቅ ትግል ለማስወገድ ጠመንጃ ካነሱ ተቃዋሚዎች ጋር ለመቀላቀል መወሰናቸውን ሱዳን ትሪቢውን ገለጸ። ውሳኔው የተላለፈው ኤርትራ ለ23ኛ ዓመት ድል በዓልን ተንተርሶ ነው።

ሱዳን ትሪቢውን እንዳለው የኤርትራን ስደተኞች መግለጫ በመጥቀስ እንደዘገበው ኢሳያስ አፈወርቂ ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ አገሪቱን በአንድ ፓርቲ “በረግጠህ ግዛው” አስተዳደር ላለፉት 23 ዓመታት ገዝተዋል። ተያይዞም የአስመራው አገዛዝ በአገሪቱ ዴሞክራሲን፣ የሰብአዊ መብትን፣ ነጻነትን ማጎናጸፍ ባለመቻሉ ስርዓቱ በዚህ መቀጠል እንደሌለበት መስማማታቸውን አመልክቷል።

“ከነጻነት” ማግስት የኤርትራ ተወላጆች እጣ ፈንታቸው ስደት፣ መሰወር፣ ጭቆና፣ እስር፣ ውርደት፣ ማስፈራራት እንደሆነ በመግለጫቸው ያመለከቱት ስደተኞች፣ “የኤርትራ ምድር እንጂ ህዝቦቿ ነጻ አልወጡም” ብለዋል። ጨቋኙ የኤርትራ አገዛዝ አሁንም በዜጎቹ ላይ አረመኔያዊ ተግባሩን ስለገፋበት ጊዜው በህብረት ወታደራዊ ርምጃ የሚወሰድበት እንደሆነ ጠቁመዋል።

ሜይ 22፣ 2014 የወጣው የሱዳን ትሪቢውን ዜና ከላይ በተጠቀሱት ምሬቶች ሳቢያ በኮሌጅ የሚገኙ በመቶዎች የሚቆጠሩ ስደተኞችም ትግሉን ጠመንጃ በማንሳት እንደሚቀላቀሉ ማረጋገጣቸውን አመልክቷል።

“በዲሞክራሲያዊ መርህ የሚመራ መንግስት በኤርትራ በተአምር ይመሰረታል ብለን መጠበቅ አንፈልግም” ማለታቸውን የጠቆመው ሱዳን ትሪቢውን፤ ባለፉት አስር ኣመታት የኤርትራ የጦር ሰራዊት አባላት፣ የባህር ሃይል፣ ጨምሮ በ100 ሺህዎች የሚቆጠሩ የኤርትራ ተወላጆች ወደ ኢትዮጵያ፣ ሱዳን፣ ጅቡቲና የመን መሰደዳቸውን ዘግቧል።

የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ኮሚሽን የአዲስ አበባ ተወካይ የሆኑትን ኪሱት ገብረእግዚአብሔርን ጠቅሶ ዜናው እንደ ገለጸው እስከ ሚያዚያ (ኤፕሪል) መጨረሻ ወደ ኢትዮጵያ የተሰደዱት የኤርትራ ተወላጆች 92,460 መሆናቸውን ዘግቧል፡፡

በአማካይ ቁጥራቸው 2000 የሚጠጋ የኤርትራ ዜጎች በየወሩ የኢትዮጵያን ድንበር እየተሻገሩ እንደሚገቡ፣ እነርሱም ከ18 – 50 ዓመት እድሜ ያላቸው ሁሉ እንዲሳተፉ የሚያስገድደውን ብሔራዊ ውትድርና የሚሸሹ መሆናቸውን ያመለከቱት ሃላፊ፣ ስደተኞቹ ከአስገዳጁ የወታደራዊ አገልግሎት ሌላ የፖለቲካ ጭቆና ሽሽት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚያሰድዳቸው ተናግረዋል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    May 25, 2014 12:08 am at 12:08 am

    >>በምሥራቅ አፍሪካ ቀንዱን አሹሎ ጦርነት የሚያሻ ድንቅ ሀገርና ሕዝብ! ግን እኛ በሰው ሀገር ሉዓላዊነት ጣልቃ አንገባም ብለን አልነበር!? ህወአት አቶ ኢሳያስን ራዕይ ሲያስፈፅም ኤርትራ ተቃዋሚ የአቶ መለስን ራዕይ ሊያስፈፅም ነው!?
    **Ethiopia and Ertiria “one-party state which is considered as one of the most repressive regimes in the world.

    **the regimes in Asmara and in Addis Ababa have failed to bring democracy, human rights and freedom to its people and they don’t want to see the regime prolonging its grip on power.

    ***During the past 23 years become the victim of executions, imprisonment, disappearances, harassment and intimidation.(source awramba times bay Tesfa-Alem Tekle)

    ***In Ethiopia alone, there are 92,460 Eritrean refugees at end of April,2014 Kisut Gebregzabiher a United Nations refugee agency (UNHCR) representative in Addis Ababa told Sudan Tribune.Ethiopia had 150,000refugees only in soudi Arabia.

    ***An average of 2,000 Eritreans cross into Ethiopia every month fleeing political repression or to escape military service which is mandatory to all citizens aged between 18 and 50 and can last a lifetime.(what about Ethiopians in four directions fleed the country every day ?)

    ***International human rights organisations say that Eritrea and Ethioia stands amongst world’s top worst human rights and press freedom records. The regimes are also accused of turning the country into a “giant prison”.(kaliti,klinto)Ethiopia bekage!

    >>>welcome to famaily, group, collective ledereship,the same teacher one book many kaders and blood suckers opportunist (elite) abusing innocent and poor people.(ከኢሳያስ አፈወርቂ ጋር ተቀምጦ መነጋጋር አንድ ቤተ መፃሕፍት ቤት ውስት ውሎ እንደማደር ነው” ያለው የህወአት ሊቅ፣ የኢህአዴግ አዛዥ፣ የብሔር ብሔረሰቦች ፈጣሪ ማን ነበር?

    ***In Ertirea there are up to 10,000 political prisoners languishing in the country’s harsh and secret detention centers, which are sometimes shipping containers.(wow! እሥር ቤቱ ኦሮምኛ ይናገራል ያለው የህወአት ፈላስፋ ማን ነበር!?)
    ***The Eritrean refugees in Ethiopia further called up on those forces of change within the Eritrean(Ethiopian) ruling party, including the army to join them in the struggle to topple the regime so that democratic change is achieved.the two nations will be free. peace love a better life for mutul benefit in 21st centuary.
    **ራሳችን አንቅልፍ ተኝተን ለጎረቤት ኤርትራ፣ ሱዳን፣ ጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ሱማልያ እንቅልፍ ያጣነው፣ለራሳችን የሻማና የጧፍ ጉልበት ለእነሱ የኤሌትሪክ ኀይል ሆነን ሕዝባችንን የምናሸብረው ለመሆኑ አሜሪካና አውሮፓውያን ስንት ቢከፍሉን ነው? ሰበር ዜና “ግንቦት ፳ ሺ፳ የአካባቢው አሸባሪና የቀጣናው አተራማሽ አቶ ኢሳያስ አፈወርቂ የኅያለመለስን ራዕይ አፈፃፀም ተቃውመው ለብሔር ብሄረሰቦች እና በሊዝና በኢንቨስትመንት ሀገሪቷን ለተቀራመቱ(ሕዝቦች) እንዲሁም ከትጥቅ ትግሉ ጀምሮ አሁንም በኢህአዴግ ከፍተኛ አመራር ላይ ላሉ ለኤርትራውያንና ትውልደ ኤርትራውያን ዕድገትና ብልፅግና ሲባል እራሳቸው ለማስቀጠል በቁጭት ተነሰሳስተው ከዛሬ ጀምሮ የምኒሊክን ቤተመንግስት የራሳቸው አድርገው ተቆጣጥረውታል።ታዘበኝ በለው!!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule