
በስውር የሚንቀሳቀሱ የኢትዮጵያ ህዝብ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ)አባላት በአዲስ አበባ በርካታ ቦታዎች ረቡዕ ሌሊት ሰኔ 5/2005 ዓ.ም. /June 12, 2013/ “ተነሥ“ በሚል ርዕስ የተዘጋጁ ቀስቃሽ ፅሑፎችን የበተኑ ሲሆን በዋናነት በቦሌ፣በካዛንቺስ፣በአራት ኪሎ፣በሽሮ ሜዳ፣በቄራ፣በፈረንሳይ ለጋሲዪን፣በሜክሲኮ፣በፒያሳ፣በመገናኛ፣በኮልፌ፣በመርካቶ፣በጎፋ እና በመሳሰሉት ዋና ዋና የከተማዋ ክፍል በሚገኙ የማስታወቂ ቦርዶች ላይ ተለጥፈው የታዩ ሲሆን በተለይ ሐሙስ ሰኔ 6/2005 ዓ.ም. በርካታ ነዋሪዎች ጽሑፉን ማንበብ ችለዋል።ይሁን እንጂ ይህ ዜና የደረሳቸው የገዢው ፓርቲ አመራሮች ወዲያው የፌደራል ፖሊሶችን እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አባላትን በማሰማራት በዋና ዋና ቦታዎች ላይ የሚገኙትን ያነሱ ሲሆን በአንዳንድ አካባቢ ግን ጽሑፎቹ እስከ ቀትር ሳይነሱ በበርካታ ሰዎች መነበብ ችለዋል።
የአዲስ አበባ ነዋሪዎችን በ5ለ1 አደረጃጀት ጠርንፎ እንደያዘ የሚነገርለት ኢህአዴግ ይህ አይነቱ ድንገተኛ ክስተት ዛሬም ድረስ ከህዝብ ጋር ሆድ እና ጀርባ እንደሆነ የሚያሳይ ነው ሲሉ አንዳንድ የከተማዋ ነዋሪዎች ትዝብታቸውን የገለፁ ሲሆን የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ የአዲስ አበባ ጽ/ቤት እና የአዲስ አበባ የወጣቶች ሊግ አመራሮች አስቸኳይ ስብሰባ ሐሙስ ዕለት እንደተቀመጡ ከስፍራው መረዳት ተችሏል።
“ተነሥ“ በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀው የዚህ ጽሑፍ ይዘት የሚከተለው ነው፦ “እጅግ የተከበርከው የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ፦ የአኩሪ ታሪክ ባለቤት፤ይልቁንም ለጥቁር ህዝቦች የነፃነት ጮራን የፈነጠቅህ ፋና ወጊ የነፃነት አርበኛ መሆንህ የአደባባይ ምስጢር ነው።ይሁን እንጂ የዚህ ሁሉ ጥንካሬህ መሠረት የሆነው አንድነትህ በጎጠኛው የወያኔ ቡድን የዘውጌ አስተዳደር ተሸርሽሮ ዛሬ በሀገርህ ተንቀሳቅሰህ የመስራት መብትህ ተገድቦ፣ከችሎታህና ከግለሰባዊ ክህሎትህ ይልቅ በዘር ማንነትህ እየተመዘንክ የኢኮኖሚ መገለል እየደረሰብህ ህይወት ብርቱ ሠልፍ ሆናብህ ሀገርህን ጥለህ እንድትሰደድ በተሰላ ስሌት በመኖርና ባለመኖር ቅርቃር ውስጥ እንድትባዝን ተደርገህ፣ሰብዓዊና ዴሞክራሲዊ መብትህ ተገፎ የመናገርና ሃሳብህን በነፃነት የማራመድ መብትህን ከመነጠቅህ ባሻገር በአጠቃላይ ህልውናህ በወያኔ የግፍ መዳፍ ውስጥ ወድቋል።ስለሆነም እንደመዥገር በላይህ ላይ ተጣብቆ በደምህ የሰባውን ይህን ዘረኛ ቡድን ከጫንቃህ ላይ አራግፈህ በፍትህ አደባባይ የምታቆምበት ጊዜው አሁን ነው።ሀገርህንና ራስህን ለማዳን ተነሥ!!!”
By: Beyene Mesfin
Dear brothers,
It is good to hear this information!!! But, we should think over and over not to repeat the previous weakness and loss of life. This means a very systematic care must be taken for the safety of participants’ life of within the country. If I were them, I really don’t know what to decide in taking such kind of action where everything is very tight. I always praise our heroes who usually determined to do such things. When I say this, I am not sending the spirit of fear for the truth, but this is just to remind you on what action should be taken to be very successful. Lets learn from our past weakness.
God bless Ethiopia!!!
Tenager