• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የዛሬዎቹ ‹‹አበባ አየሽ ሆይ›› እና ‹‹ሆያሆዬ››

September 11, 2013 05:37 am by Editor Leave a Comment

ኢትዮጵያውያን ልዩ ልዩ በዓሎቻቸውን ስለየበዓላቱ ትርጉም ባላቸው ዝማሬዎችና ጭፈራዎች ያደምቁታል፡፡ ከእነዚህ አንዱ የሆነው የዘመን መለወጫንም ‹‹እንቁጣጣሽ››ን በ‹‹አበባ አየሽ ሆይ›› ያደምቁታል፡፡

እንቁጣጣሽ ሲመጣ ልጃገረዶች ከበሯቸውን ይዘው በየቤቱ እየዞሩ ‹‹አበባ አየሽ ሆይ›› እያሉ ሲጨፍሩ፣ ድምፃዊቷ ዘሪቱ ጌታነህም በየራዲዮ ጣቢያው ‹‹እንቁጣጣሽ እንኳን መጣሽ…›› እያለች በቀጭኑ ድምጿ የምታቀነቅነው ዘፈን ሲሰማ በዓሉን ለመቀበል ያለውን ስሜት ሞቅ ሞቅ ያደርጋል፡፡

ቀደም ሲል ልጃገረዶች ‹‹አበባ አየሽ ሆይን›› ለመጨፈር ተቧድነው እንግጫ ይዘው፣ ከበሯቸውን እየመቱ ከዋዜማ እስከ በዓሉ ዕለት ይጨፍራሉ፡፡ ያኔ የነበረው ጭፈራ የግጥምና የዜማ መፋለስ ችግር አልነበረበትም፡፡ ጨፋሪዎቹም ለዓይን ሞላ ያሉ ነበር፡፡ ጨፍረው ሲያበቁም በዋናነት የሚሸለሙት ቤት ያፈራውን ስለነበር ለሳንቲምና ለብር ብዙም ቦታ አልነበራቸውም፡፡ ልጆቹም ‹‹አበባ አየሽ ሆይ…›› ሲሉ የሚጨፈርላቸው ሰዎችም ትእግስቱ ነበራቸው፣ ለባህሉም ቦታ ይሰጡ ነበር፡፡

ዘንድሮስ? የዘንድሮዎቹ የአዲስ አበባ ጨፋሪዎች ቁጥር ለዓይን የጎደሉ፣ ግጥሙንና ጭፈራውን በተሟላ መልኩ የማይገልጹ እንደሚበዙባቸው ይነገራል፡፡ ልጆቹም እየተዘዋወሩ ሲጨፍሩ የሚጨፈርላቸው ሰዎች ሊለመኑ የተመጣባቸው ስለሚመስላቸው ‹‹አድርሰናል›› ወይም ደግሞ ‹‹አያስፈልግም ሂዱ›› ተብለው ልጆቹ ይመለሳሉ፣ ይባረራሉ፡፡ በምርቃት የሚሸኙ ጨፋሪዎች ካሉ እድለኞች ናቸው፡፡

የዘንድሮዎቹ ልጆች ሙሉውን ጭፈራ እንዲጨፍሩ ዕድሉ ቢሰጣቸውም፣ ሽልማቱ ዳቦ ይሆናል የሚል ግምት አያድርባቸውም፣ ሸላሚዎቹም ‹‹ዳቦ መች ይፈልጉና›› ብለው አቅም የፈቀደውን ሳይሆን ‹‹ይሄ ይበቃቸዋል›› በሚል ስሜት ገንዘብ ይሰጧቸዋል፡፡ ከሦስት ሳምንት በፊት የተከበረው ቡሄም እንደዚያው፡፡ የቡሄንና የእንቁጣጣሽን ጭፈራ በቀደሙት ጊዜያት ጠንቅቀው የሚያውቁ ሰዎች አሁን ላይ ያለው ጭፈራ ግጥሙም ዜማውም የተራራቀ እንደሆነ የሚናገሩትም ለዚሁ ነው፡፡

እነዚህ ባህላዊ እሴቶች ዘመን እየተለወጠ ሲሄድና ሥልጣኔ ሲመጣ አብረው የሚቀየሩ፣ የሚጠፉ ወይም የሚረሱ መሆን የለባቸውም፡፡ እነዚህ ጭፈራዎች በዓላቱ ሲመጡ ሁሌም መከናወን የሚገባቸው ኢትዮጵያዊነትን የሚገልፁ ናቸው፡፡

ለዘመናት የቆየን ባህል ስለማስተዋወቅና ለትውልድ ስለማስተላለፍ ሲወሳ የትግራይ፣ የላስታ ላሊበላና የሰቆጣ አሸንዳ (ሻዳይ) እንዲሁም የኦሮሞ ተወላጆች እያሴን ማስታወስ ተገቢ ነው፡፡ የትግራይ ልጃገረዶች ወገባቸውን በቄጤማ ሸብ አድርገው ከበሯቸውን እየደለቁ ከቦታ ቦታ እየተዘዋወሩ የሚጨፍሩት እዚያው ትግራይ ብቻ አይደለም፡፡ አሸንዳ በተከበረበት ያለፈው ሰሞን አንዳንድ የአዲስ አበባ ጎዳናዎች አሸንዳን የሚጨፍሩ ልጃገረዶችን ሲያስተናግዱ ነበር፡፡ ምሽት ላይም እንደልጅነታቸው ጸጉራቸውን የተላጩ፣ አብዛኛውን ተላጭተው የተወሰኑ ቦታዎች ላይ ጸጉራቸውን ጉች ጉች ያደረጉ ጎረምሶች በየምሽት ክበቡ እየገቡ በሚያስተጋባ ጭብጨባቸው፣ በኃይለኛ በሚደልቁት ከበሯቸው ድምፅ እንዲሁም ዝላይ እየታጀቡ ሲጨፍሩ ነበር፡፡

መስቀልንም በተመለከተ የኦሮሚያ ተወላጆች የእያሴ ጭፈራን እርጥብ ሣር በመያዝ ዱላቸውን ወደ ሰማይ ቀስረው በእግራቸው መሬቱን እየደበደቡና እየዘለሉ ሁሌ በየዓመቱ ይጨፍራሉ፡፡ ልክ እንደ እያሴና አሸንዳ የአበባ አየሽ ሆይ እና ሆያሆዬ ጭፈራዎች ባህሉንና ታሪኩን በጠበቀ መልኩ ለተተኪው ትውልድ ሲተላለፉ ግን አይታዩም፡፡

ፈረንጆቹ የሃሎዊን በዓልን ሲያከብሩ ልጆቻቸው የተለያዩ አልባሳትን በመልበስ በየቤቱ እያንኳኩ ከረሜላና ሌሎች ጣፋጮችን ሲሰበስቡ ይታያሉ፡፡ ይህ ልማድ በእነርሱ ዘንድ በፊትም ነበር፣ አሁንም አለ፡፡

ብዙዎች እንደሚያምኑት የኢትዮጵያ ብቻ የሆኑት ‹‹አበባ አየሽ ሆይ›› እና ‹‹ሆያ ሆዬ››ም ለትውልድ እየተላለፉ በፊት ወደነበራቸው የግጥምና የዜማ ወግና ባህል መመለስ ሲገባቸው ይህ ሲሆን አይታይም፡፡ በርካታ ዘመናትን ተሻግረው የመጡትን ባህሎች የማሠልጠን ስሜትም ሆነ የጊዜ መለወጥ ተጽዕኖ ሊያደርግባቸው ቢገባም አጨፋፈሩ እየተቃኘ ያለው በሥልጣኔ ሳይሆን ጭራሽ ሊጣጣም በማይችል ግጥምና ዜማ ነው፡፡ ashenda

በኢትዮጵያ በፌዴራል ደረጃ፣ ክልሎችም እንደ ክልል አበባ አየሽ ሆይንም ሆነ ሆያ ሆዬን የቱሪስት መስህብ የማድረግና ባህልና ታሪኩን የማስጠበቅ ኃላፊነት አለባቸው፡፡ የትግራይ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጠፍቶ የነበረውን የአሸንዳ ባህል ለመመለስ በዕድሜ የገፉትን እናቶች አሳትፎ ባህሉ ለዛሬዎቹ ሕፃናትና ታዳጊዎች እንዲመለስ አድርጓል፡፡ የቱሪስት መስህብ ለማድረግም ጠንክሮ እየሠራ ነው፡፡

የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ በሚዲያዎችና በተለያዩ አጋጣሚዎች ሆያ ሆዬም ሆነ አበባ አየሽ ሆይ ፈር መልቀቃቸው ሲነገር ዓመታት ቢያልፉም ጆሮ ሲሰጥ አልተስተዋለም፡፡ በመሆኑም የቱሪስት መስህብ ሊሆን የሚገባው ባህል እንደዋዛ እየተሸረሸረ ይዘቱን ለቋል፡፡

በጉዳዩ ላይ የተለያዩ ጥናቶችና መፍትሔዎች ቢቀርቡም ወደ ተግባር ሲለወጡም አይታዩም፡፡ በመሆኑም እንደነበረው ሳይሆን ከዓመት ዓመት ለዛቸውን ሲያጡና ማስተላለፍ የሚገባቸውን መልዕክት ሲሳቱ ይስተዋላሉ፡፡(ምዕራፍ ብርሃኔ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule