• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የዛሬዎቹ ‹‹አበባ አየሽ ሆይ›› እና ‹‹ሆያሆዬ››

September 11, 2013 05:37 am by Editor Leave a Comment

ኢትዮጵያውያን ልዩ ልዩ በዓሎቻቸውን ስለየበዓላቱ ትርጉም ባላቸው ዝማሬዎችና ጭፈራዎች ያደምቁታል፡፡ ከእነዚህ አንዱ የሆነው የዘመን መለወጫንም ‹‹እንቁጣጣሽ››ን በ‹‹አበባ አየሽ ሆይ›› ያደምቁታል፡፡

እንቁጣጣሽ ሲመጣ ልጃገረዶች ከበሯቸውን ይዘው በየቤቱ እየዞሩ ‹‹አበባ አየሽ ሆይ›› እያሉ ሲጨፍሩ፣ ድምፃዊቷ ዘሪቱ ጌታነህም በየራዲዮ ጣቢያው ‹‹እንቁጣጣሽ እንኳን መጣሽ…›› እያለች በቀጭኑ ድምጿ የምታቀነቅነው ዘፈን ሲሰማ በዓሉን ለመቀበል ያለውን ስሜት ሞቅ ሞቅ ያደርጋል፡፡

ቀደም ሲል ልጃገረዶች ‹‹አበባ አየሽ ሆይን›› ለመጨፈር ተቧድነው እንግጫ ይዘው፣ ከበሯቸውን እየመቱ ከዋዜማ እስከ በዓሉ ዕለት ይጨፍራሉ፡፡ ያኔ የነበረው ጭፈራ የግጥምና የዜማ መፋለስ ችግር አልነበረበትም፡፡ ጨፋሪዎቹም ለዓይን ሞላ ያሉ ነበር፡፡ ጨፍረው ሲያበቁም በዋናነት የሚሸለሙት ቤት ያፈራውን ስለነበር ለሳንቲምና ለብር ብዙም ቦታ አልነበራቸውም፡፡ ልጆቹም ‹‹አበባ አየሽ ሆይ…›› ሲሉ የሚጨፈርላቸው ሰዎችም ትእግስቱ ነበራቸው፣ ለባህሉም ቦታ ይሰጡ ነበር፡፡

ዘንድሮስ? የዘንድሮዎቹ የአዲስ አበባ ጨፋሪዎች ቁጥር ለዓይን የጎደሉ፣ ግጥሙንና ጭፈራውን በተሟላ መልኩ የማይገልጹ እንደሚበዙባቸው ይነገራል፡፡ ልጆቹም እየተዘዋወሩ ሲጨፍሩ የሚጨፈርላቸው ሰዎች ሊለመኑ የተመጣባቸው ስለሚመስላቸው ‹‹አድርሰናል›› ወይም ደግሞ ‹‹አያስፈልግም ሂዱ›› ተብለው ልጆቹ ይመለሳሉ፣ ይባረራሉ፡፡ በምርቃት የሚሸኙ ጨፋሪዎች ካሉ እድለኞች ናቸው፡፡

የዘንድሮዎቹ ልጆች ሙሉውን ጭፈራ እንዲጨፍሩ ዕድሉ ቢሰጣቸውም፣ ሽልማቱ ዳቦ ይሆናል የሚል ግምት አያድርባቸውም፣ ሸላሚዎቹም ‹‹ዳቦ መች ይፈልጉና›› ብለው አቅም የፈቀደውን ሳይሆን ‹‹ይሄ ይበቃቸዋል›› በሚል ስሜት ገንዘብ ይሰጧቸዋል፡፡ ከሦስት ሳምንት በፊት የተከበረው ቡሄም እንደዚያው፡፡ የቡሄንና የእንቁጣጣሽን ጭፈራ በቀደሙት ጊዜያት ጠንቅቀው የሚያውቁ ሰዎች አሁን ላይ ያለው ጭፈራ ግጥሙም ዜማውም የተራራቀ እንደሆነ የሚናገሩትም ለዚሁ ነው፡፡

እነዚህ ባህላዊ እሴቶች ዘመን እየተለወጠ ሲሄድና ሥልጣኔ ሲመጣ አብረው የሚቀየሩ፣ የሚጠፉ ወይም የሚረሱ መሆን የለባቸውም፡፡ እነዚህ ጭፈራዎች በዓላቱ ሲመጡ ሁሌም መከናወን የሚገባቸው ኢትዮጵያዊነትን የሚገልፁ ናቸው፡፡

ለዘመናት የቆየን ባህል ስለማስተዋወቅና ለትውልድ ስለማስተላለፍ ሲወሳ የትግራይ፣ የላስታ ላሊበላና የሰቆጣ አሸንዳ (ሻዳይ) እንዲሁም የኦሮሞ ተወላጆች እያሴን ማስታወስ ተገቢ ነው፡፡ የትግራይ ልጃገረዶች ወገባቸውን በቄጤማ ሸብ አድርገው ከበሯቸውን እየደለቁ ከቦታ ቦታ እየተዘዋወሩ የሚጨፍሩት እዚያው ትግራይ ብቻ አይደለም፡፡ አሸንዳ በተከበረበት ያለፈው ሰሞን አንዳንድ የአዲስ አበባ ጎዳናዎች አሸንዳን የሚጨፍሩ ልጃገረዶችን ሲያስተናግዱ ነበር፡፡ ምሽት ላይም እንደልጅነታቸው ጸጉራቸውን የተላጩ፣ አብዛኛውን ተላጭተው የተወሰኑ ቦታዎች ላይ ጸጉራቸውን ጉች ጉች ያደረጉ ጎረምሶች በየምሽት ክበቡ እየገቡ በሚያስተጋባ ጭብጨባቸው፣ በኃይለኛ በሚደልቁት ከበሯቸው ድምፅ እንዲሁም ዝላይ እየታጀቡ ሲጨፍሩ ነበር፡፡

መስቀልንም በተመለከተ የኦሮሚያ ተወላጆች የእያሴ ጭፈራን እርጥብ ሣር በመያዝ ዱላቸውን ወደ ሰማይ ቀስረው በእግራቸው መሬቱን እየደበደቡና እየዘለሉ ሁሌ በየዓመቱ ይጨፍራሉ፡፡ ልክ እንደ እያሴና አሸንዳ የአበባ አየሽ ሆይ እና ሆያሆዬ ጭፈራዎች ባህሉንና ታሪኩን በጠበቀ መልኩ ለተተኪው ትውልድ ሲተላለፉ ግን አይታዩም፡፡

ፈረንጆቹ የሃሎዊን በዓልን ሲያከብሩ ልጆቻቸው የተለያዩ አልባሳትን በመልበስ በየቤቱ እያንኳኩ ከረሜላና ሌሎች ጣፋጮችን ሲሰበስቡ ይታያሉ፡፡ ይህ ልማድ በእነርሱ ዘንድ በፊትም ነበር፣ አሁንም አለ፡፡

ብዙዎች እንደሚያምኑት የኢትዮጵያ ብቻ የሆኑት ‹‹አበባ አየሽ ሆይ›› እና ‹‹ሆያ ሆዬ››ም ለትውልድ እየተላለፉ በፊት ወደነበራቸው የግጥምና የዜማ ወግና ባህል መመለስ ሲገባቸው ይህ ሲሆን አይታይም፡፡ በርካታ ዘመናትን ተሻግረው የመጡትን ባህሎች የማሠልጠን ስሜትም ሆነ የጊዜ መለወጥ ተጽዕኖ ሊያደርግባቸው ቢገባም አጨፋፈሩ እየተቃኘ ያለው በሥልጣኔ ሳይሆን ጭራሽ ሊጣጣም በማይችል ግጥምና ዜማ ነው፡፡ ashenda

በኢትዮጵያ በፌዴራል ደረጃ፣ ክልሎችም እንደ ክልል አበባ አየሽ ሆይንም ሆነ ሆያ ሆዬን የቱሪስት መስህብ የማድረግና ባህልና ታሪኩን የማስጠበቅ ኃላፊነት አለባቸው፡፡ የትግራይ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ጠፍቶ የነበረውን የአሸንዳ ባህል ለመመለስ በዕድሜ የገፉትን እናቶች አሳትፎ ባህሉ ለዛሬዎቹ ሕፃናትና ታዳጊዎች እንዲመለስ አድርጓል፡፡ የቱሪስት መስህብ ለማድረግም ጠንክሮ እየሠራ ነው፡፡

የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ በሚዲያዎችና በተለያዩ አጋጣሚዎች ሆያ ሆዬም ሆነ አበባ አየሽ ሆይ ፈር መልቀቃቸው ሲነገር ዓመታት ቢያልፉም ጆሮ ሲሰጥ አልተስተዋለም፡፡ በመሆኑም የቱሪስት መስህብ ሊሆን የሚገባው ባህል እንደዋዛ እየተሸረሸረ ይዘቱን ለቋል፡፡

በጉዳዩ ላይ የተለያዩ ጥናቶችና መፍትሔዎች ቢቀርቡም ወደ ተግባር ሲለወጡም አይታዩም፡፡ በመሆኑም እንደነበረው ሳይሆን ከዓመት ዓመት ለዛቸውን ሲያጡና ማስተላለፍ የሚገባቸውን መልዕክት ሲሳቱ ይስተዋላሉ፡፡(ምዕራፍ ብርሃኔ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule