• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የግብጽ ፍርድቤት 530 በሚሆኑ የሙስሊም ወንድማማች አባላት ላይ ሞት ፈረደ

March 25, 2014 08:18 am by Editor 1 Comment

* ውሳኔው የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን አስደንግጧል

በሕዝብ ከተመረጡ በኋላ በመፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣናቸው የተወገዱትን የቀድሞ የግብጽ ፕሬዚዳንት መሐመድ ሙርሲን በመደገፍ በፖሊስ ጣቢያ ላይ አደጋ አድርሰው የነበሩ 529 ተጠርጣሪዎች ትላንት ሰኞ ዕለት የሞት ቅጣት ተበየነባቸው፡፡ የብይኑ ፍጥነትና የተፈረደባቸው ተከሳሾች ብዛት አምነስቲ ኢንተርናሽናልን ጨምሮ በርካታ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችን አስደንግጧል፡፡ አሶሺየትድ ፕሬስ እንደዘገበው ከሆነ ውሳኔው ለይግባኝ የሚቀርብ ሲሆን በሙስሊም ወንድማማች ላይ ሆን ተብሎ የተነጣጠረ ጥቃት እንደሆነ ዘግቧል፡፡

egypt 3በዓለማችን በቅርብ ጊዜያት ከተካሄዱ የሞት ፍርድ ብያኔዎች በብዛትም ሆነ በፍጥነት ለየት ያለ እንደሆነ የተጠቀሰለት ይህ የፍርድ ሂደት በግብጽ የሕግ የበላይነት እየከሰመ የሄደ መሆኑን የሚያመላክት ነው ሲሉ በርካታ የሕግ ምሁራን አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ ተከሳሾቹ በሙሉ የሙስሊም ወንድማማች አባላትና የቀድሞው ፕሬዚዳንት መሐመድ ሙርሲ ደጋፊ መሆናቸው ብያኔው እውነተኛ የፍርድ ሂደት የተከተለ ሳይሆን ወደፊት ሊነሳ ለሚችል ተቃውሞ ማስተማሪያ እንዲሆን ታቅዶ የተከናወነ ነው ሲል የፍትሕ ባለሥልጣናትን ጠቅሶ አሶሺየትድ ፕሬስ በተጨማሪ ዘግቧል፡፡

ተከሳሾቹ የቀረበባቸው ክስ ባለፈው ነሐሴ ወር ሚኒያ በተባለች የግብጽ ከተማ በሚገኝ የፖሊስ ጣቢያ ላይ በተሰነዘረ ጥቃት በተከናወነ የነፍስ ግድያ፣ የግድያ ሙከራ፣ መንግሥትን ለመገልበጥ ሕገወጥ ቡድንን መቀላቀል እና የመንግሥትን የጦር መሣሪያ መስረቅ በሚሉ ወንጀሎች ናቸው፡፡ በወቅቱ በፖሊስ ጣቢያው ላይ በደረሰ ጥቃት የሚኒያ ከተማ ምክትል የፖሊስ ኃላፊ ሞሐመድ አል-አታር መገደላቸው ይታወቃል፡፡ ከዚህ ጥቃት በኋላ በመፈንቅለ መንግሥት ሥልጣን የያዘው ወታደራዊው አገዛዝ በሙስሊም ወንድማማች ደጋፊና አባላት ላይ እጅግ ከፍተኛ የሆነና አሰቃቂ ጥቃት በማድረስ በዚያን ወቅት ብቻ ከ600 በላይ ሰዎች መገደላቸው ይታወሳል፡፡

ከ545 ተከሳሾች ውስጥ 528ቱ ጥፋተኞች ሆነው በመገኘታቸው የሞት ፍርድ እንደተበየነባቸው የመንግሥት ሚዲያ ሲያስታውቅ አንዳንድ ባለሥልጣናት ቁጥሩ 529 እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ 150 በሌሉበት ፍርዱ የተበየነባቸው ሲሆን የተቀሩት ግን በነጻ ተለቅቀዋል፡፡ በግድያው የተሳተፉት ብቻ ፍርድ ሊበየንባቸው ይገባል በማለት የሚከራከሩ ወገኖች እንደሚሉት በማስረጃነት የቀረቡት 20 የሚሆኑ የቪዲዮ ምስሎች እንደሚያሳዩት የተወሰኑ ሰዎች የፖሊስ አዛዡን በብረት በትር ሲደበድቡ እና አንድ ሐኪም ደግሞ በእሣት ማጥፊያ የኦክስጂን ሲሊንደር (ካንስተር) የፖሊሱ ጭንቅላት ሲፈረክስ ታይቷል ይላሉ፡፡

መሐመድ ሙርሲ
መሐመድ ሙርሲ

ሁለት ቀናት ብቻ በፈጀው በዚህ የፍርድ አሠጣጥ ሥርዓት ላይ የተከሳሽ ጠበቆች በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ የማስረጃ ሰነዶችን ለመመልከትም ሆነ በቂ ጊዜ አግኝተው የደንበኞቻቸውን ጉዳይ ለፍርድቤቱ ለማስረዳት እንዳልቻሉ ተናግረዋል፡፡ ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ ከፍተኛ ባለስልጣን ለአሶሺየትድ ፕሬስ እንደገለጹት ከዚህ ዓይነቱ የሞት ብያኔ በኋላ ማንም በተመሳሳይ እንቅስቃሴ ውስጥ እንደማይሳተፍ ጠቁመዋል፡፡ የፍርዱን አካሄድ ሲገልጹም “ሁኔታው እጅግ ለየት ያለ ነው፤ እያንዳንዱን ተከሳሽ እየጠራን ክሱን እንዲከራከር፣ ጠበቃ እንዲያቆም፣ ወዘተ ለማድረግ በቂ ጊዜ የለንም” ብለዋል፡፡ በፍርዱ ሂደት ላይ ተጨማሪ ጊዜ እንዲሰጣቸው በጠየቁ ጠበቆች ላይ ችሎቱ የመሩት ዳኛ ሰዒድ ዩሱፍ ጠበቆቹን በቁጣ መዝለፋቸው አብሮ ተዘግቧል፡፡

የሞት ፍርዱ በግብጽ ሙፍቲ (የአገሪቱ ከፍተኛ እስላማዊ ባለሥልጣን) መጽደቅ ያለበት ሲሆን በአሁኑ ጊዜ የተከሳሽ ጠበቆች ይግባኝ በማለት ፍርዱን ለማስቀየር እየሠሩ መሆናቸው ተገልጾዋል፡፡

ሞሐመድ ባዴይ
ሞሐመድ ባዴይ

ሌሎች ወደ 700 የሚጠጉ የሙስሊም ወንድማማች ተከሳሾች ዛሬ ማክሰኞ ለፍርድ ይቀርባሉ፡፡ ከእነዚህም መካከል የወንድማማቹ ከፍተኛ ባለሥልጣን የሆኑት ሞሐመድ ባዴይ እና ሌሎች ከፍተኛ ኃላፊዎች ይገኙበታል፡፡ በመፈንቅለ መንግሥት ከሥልጣን የተወገዱት የቀድሞው ፕሬዚዳንት ሞሐመድ ሙርሲም በቅርቡ ለፍርድ የሚቀርቡ ሲሆን ዛሬ የሚቀርቡትን ጨምሮ ሙርሲም ሞት ሊፈረድባቸው ይችላል የሚል አስተያየት እየተሰጠ ይገኛል፡፡ ሆኖም ግን ዓለምአቀፍ ተጽዕኖን በመፍራት ሙርሲ ላይ ሞት የመፈረዱ ጉዳይ አጠራጣሪ እንደሆነ ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ አመልክተዋል፡፡

የሰኞ ዕለቱን ብያኔ ተቃውሞ የቀረበበበትን ያህል የፍርዱን ትክክለኛነት የደገፉ ግብጻውያንም አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ አሚን ፍቱሕ የተባሉ የካይሮ ነዋሪ ለአሶሺየትድ ፕሬስ እንደተናገሩት “ቁርዓን እንደሚለው ገዳዮች ሞት ይገባቸዋል፤ እነዚህ ሰዎች ግድያ ስለፈጸሙ በአጸፋው መገደል ይገባቸዋል” ብለዋል፡፡

ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ሂውማን ራይትስ ዎችና አምነስቲ ኢንተርናሽናል በሰኞው ዕለት ፈጣን የሁለት ቀን ብያኔና በቀጣይ የሚደረጉት የፍርድ ሂደቶች እጅግ ያሳሰቧቸው መሆኑ ገልጸዋል፡፡ አምነስቲ ብያኔውን “በቅርብ ዓመታት በዓለማችን ከተካሄዱ የሞት ብያኔዎች በዓይነቱ ብቸኛው” በማለት ሲገልጸው ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብት ድርጅት ደግሞ “ኅሊናን የሚያስደነግጥና የፍትሕ ውርጃ የታየበት” ነው ብሎታል፡፡ (ፎቶ: AP እና BBC)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. kindeya says

    March 25, 2014 12:57 pm at 12:57 pm

    it is absolutely in human

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am
  • ከያቤሎ አዲስ አበባ የተላከ ኮንትሮባንድ ጉለሌ ተያዘ September 7, 2023 01:40 pm
  • “እንኳን ተለያይተንና እርስ በርስ ተባልተን በአንድነት ቆመንም ወጀቡን መሻገር አቅቶናል” September 7, 2023 01:31 am
  • ራሱን መሪ አልባ የሚያደርገው አማራ ክልል August 24, 2023 11:50 pm
  • ጀብደኛው August 24, 2023 10:06 am
  • ጎንደርና ባሕር ዳር ከተሞች ወደ ቀድሞ ሰላማቸው ተመልሰዋል August 13, 2023 10:55 pm
  • ኢትዮጵያ በታሪኳ የመጀመሪያውን ግዙፍ ወታደራዊ ኃይል አስመረቀች August 13, 2023 10:26 pm
  • ሪፖርተር የፓርላማ ወንበር አስልቶ የአስቸኳይ አዋጁ በፓርላማ እንዳይደገፍ አቅጣጫ አመላከተ August 13, 2023 09:11 pm
  • ወደ ኤርትራ በኮንትሮባንድ የሚሻገሩ ቆሳቁሶች እየተያዙ ነው August 11, 2023 12:52 pm
  • የአማራ ክልል ትልልቅ ከተሞች ተኩስ ዓልባ ሆነው ውለዋል August 10, 2023 04:31 pm
  • “አንድ ሰው ለመግደል ኅንፃውን ማቃጠል” የኢ-ዲሞክራሲና ጽንፈኛ ኃይሎች ቅዠት፤ (ክፍል ሁለት) August 10, 2023 09:44 am
  • “አርበኛ” መሳይ – “የድል ዜና” ሳይበርድ 50ሺህ ዶላር በጎፈንድሚ August 10, 2023 09:08 am
  • በሕዝቡ ድጋፍ ከተሞች ከዘራፊው መንጋ ሥጋት ነጻ መሆናቸው ይፋ ሆነ August 9, 2023 11:47 am
  • ትህነግ አራተኛውን ሞት ሞተ  August 8, 2023 05:47 pm
  • “ሃሳብ ሲነጥፍ ነፍጥ አንግቤ እዋጋለሁ” የሚሉ አካላት ላይ እርምጃ ይወሰዳል – የመከላከያ ሠራዊት August 1, 2023 09:25 am
  • ደቡብ አፍሪካ የመሸጉ ወንጀለኞች ለሕግ ተላልፈው ሊሰጡ ነው July 31, 2023 09:27 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule