• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በአፋር በየቀኑ እስከ 100 የሚደርሱ ከብቶች ይሞታሉ

August 12, 2015 05:38 am by Editor Leave a Comment

* እንደተለመደው ኢህአዴግ የድርቅ አደጋና የምግብ እጥረት ስጋት የለም እያለ ነው

ባለፉት ሁለት ወራት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተከሰተው የዝናብ እጥረት የድርቅ አደጋ እንዳይከሰት ስጋት የፈጠረ ሲሆን ግብርና ሚኒስቴር በበኩሉ፤ የዝናብ እጥረት ቢኖርም የድርቅ አደጋና የምግብ እጥረት ስጋት የለም ብሏል፡፡

በአፋር ክልል ግን ሁኔታው ተባብሷል፡፡ በየቀኑ እስከ 100 የሚደርሱ ከብቶች በመኖና በውሃ እጥረት እየሞቱ መሆኑን ምንጮቻችን ጠቁመዋል፡፡

የአፋር ክልልን አቋርጠው ወደ ጅቡቲ ወደብ ከሚጓዙ ሹፌሮች አንዱ ለአዲስ አድማስ እንደገለፀው፤ በመንገድ ዳርና ዳር በርካታ በጎችና ፍየሎች ሞተው ይታያሉ፡፡

በክልሉ ካለፈው ዓመት ሰኔ ወር ጀምሮ እስካሁን ድረስ ዝናብ የጣለባቸው ቀናት በጣት የሚቆጠሩ መሆናቸውን የጠቆሙት ምንጮች፤ የድርቁ ሁኔታ እየተባባሰ ቢሆንም በመንግስት በኩል ፈጣን እርምጃ አልተወሰደም ሲሉ ቅሬታቸውን ገልጸዋል። የግብርና ሚኒስቴር ግን በዚህ አይስማማም። የዝናብ እጥረቱ የፈጠረው ድርቅ በእንሰሳቱ ላይ የከፋ ጉዳት እንዳያደርስ ከክልሉ መንግስት ጋር በመቀናጀት የመጠጥ ውሃና መኖ በማቅረብ ላይ መሆኑን ጠቁሞ ከብቶች እየሞቱ ነው ስለሚባለው ግን መረጃው እንደሌለው ገልጿል፡፡

በክልሉ የተከሰተው ድርቅ የሚያደርሰውን ጉዳት ለመከላከል አስፈላጊው ሁሉ እየተደረገ ነው ያሉት የሚኒስትሩ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ም/ኃላፊ አቶ ወንድሙ ፍላቴ፤ “ሀገሪቱ በቂና አስተማማኝ የአደጋ መከላከል ዝግጁነት አላት” ብለዋል፡፡

ምንጮቻችን እንደሚሉት፤ በተለይ በአማራ ክልል በወሎ እንዲሁም በሐረር አካባቢ በተከሰተው የዝናብ እጥረት የድርቅ ስጋት አንዣቧል፡፡

ዘንድሮ በአገሪቱ የሰሜንና ምስራቅ እንዲሁም መካከለኛ ክፍሎች በአየር ፀባይ ለውጥ (ኤሊኖ) የተነሳ የዝናብ እጥረት መፈጠሩን የጠቆመው ግብርና ሚኒስቴር፤ በሰኔና በሐምሌ ይጠበቅ የነበረው ዝናብ መቆራረጥ ቀድሞ የተዘሩ ሰብሎች እንዳይበቅሉ ቢያደርግም ከነሐሴ ጀምሮ መዝነብ መጀመሩንና ቀጣይነት እንደሚኖረውም ገልጿል፡፡

“ገበሬዎች ዝናብ ሲዘንብ ጠብቀው ውሃውን በማቆር ለሰብሎቻቸው እንዲጠቀሙ እየተደረገ ነው፤ የግብርና ልማት ጣቢያ ሰራተኞችም የወትሮው የግብርና ስራ እንዳይስተጓጎል ያልተቋረጠ ድጋፍ እያደረጉ ነው” ብለዋል ም/ኃላፊው፡፡

በአሁኑ ወቅት ግብርና ሚኒስቴር የዝናብ እጥረቱን መቋቋም የሚችሉ የድንች፣ ስንዴ፣ ማሽላ፣ ጤፍና የመሳሰሉ ሰብሎችን ምርጥ ዘር በማቅረብ ችግሩን ለመከላከል ጥረት እያደረገ መሆኑንም ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡  በተለይ የሰብል አምራች በሆኑ አካባቢዎች የተከሰተው የዝናብ እጥረት በቀጣይ ዓመት የሃገሪቱ የምርት አቅም ይቀንሳል፣ ረሃብም ሊፈጠር ይችላል የሚል ስጋት እንዳላቸው ምንጮቻችን የገለፁ ሲሆን ግብርና ሚኒስቴር በበኩሉ፤ የተፈጥሮ ክስተቱ ፈታኝ ቢሆንም ሃገሪቱ በቂ የአደጋ መከላከል ዝግጁነት እንዳላት ጠቁሞ፣ በቂ ምርት ማግኘት እንደሚቻልና የምግብ እጥረት ስጋት እንደማይኖር አስታውቋል፡፡ (ምንጭ: አዲስ አድማስ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule