• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በትግራይ ድርቅ ህይወት እየቀጠፈ ነው!

September 23, 2015 09:43 pm by Editor Leave a Comment

* “ከብቶቻችሁን ሸጣችሁ ተገላገሉ” ህወሃት ለነዋሪዎች

የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) በሚገዛት ትግራይ ድርቅ በአስከፊ ሁኔታ ህይወት እየቀጠፈ መሆኑ ተገለጸ፡፡ ለእንስሳትም ሆነ ለሰው ዕርዳታ መስጠት ገና ባይጀመርም በሚደረገው ዕርዳታ የመስጠት ዕቅድ ውስጥ የዓረና-መድረክ አባላት የሆኑ ነዋሪዎች “ዓረና ይርዳህ” በመባል ከዕርዳታው አሠጣጥ ዕቅድ ውጪ ተደርገዋል፡፡ የህወሃት ካድሬዎች ነዋሪ ገበሬዎችን “ከብቶቻችሁን ሸጣችሁ ተገላገሉ” በማለት መመሪያ እየሰጡ ነው፡፡ አምዶም ገብረሥላሴ በፌስቡክ ገጹ ላይ ያወጣው መረጃ እንዲህ ይነበባል፡-

ድርቅ በትግራይ አስከፊ ሁኔታ ላይ በመድረሱ የቤት እንስሳ ህይወት እየቀጠፈ ነው። በትግራይ አብዛኛው ወረዳዎች የድርቅ አደጋ የተጠቁ ሲሆኑ እጅግ አስከፊ የሚባል ጉዳት ያደረሰባቸው ወረዳዎች ግን አፅቢ ወንበርታ 12 ቀበሌዎች፣ የክልተ አውላዕሎ በርካታ ቀበሌዎች፣ አብዛኛው ራያ ዓዘቦና ራያ አለማጣ ቀበሌዎች፣ የኦፍላ ግማሽ ቀበሌዎች፣ አብዛኛው ሕንጣሎ ወጀራት፣ ከግማሽ በላይ ሳምረ ሰሓርቲ፣ አብዛኛው ጣንቋ አበርገለ ወረዳ፣ የምዕራባዊ ዞን የርካታ ቀበሌዎች ናቸው።

በተጠቀሱት ወረዳዎች በድርቁ ምክንያት የእንስሳት ምግብ እጥረት አጋጥሞ በርካታ የቤት እንስሳት ለሞት ተዳርገዋል።

የትግራይ ክልል መስተዳድር ምንም ዓይነት የህይወት አድን ስራ መስራት አልቻለም። በጣም የሚያሳዝነው (አገዛዙ) ሃላፊነቱን በመዘንጋት በድርቅ ለተጠቁ አካባቢ ነዋሪ ገበሬዎች “በድርቁ ምክንያት ከብቶቻችሁን ሸጣቹችሁ ተገላገሉ” የሚል መመሪያ መስጠቱ ነው።

በጣም የሚገርመው እስካሁን ለእንስሳም ይሁን ለሰው እርዳታ ማቅረብ ያልተጀመረ ሲሆን በድርቅ የተጠቁ ቀበሌዎች ነዋሪ የሆኑት የዓረና አባላት ከጥናቱ ውጭ እያደረጓቸው ይገኛሉ።

ለምሳሌ በኦፍላ ወረዳ ዓረና-መድረክን ወክሎ ለክልል ምክር ቤት እጩ ተወዳዳሪ የነበረው አቶ ጡዕማይ ስዩም “ዓረና ይርዳህ” በማለት ከእርዳታው ውጭ በማድረግ ከነፍስ ማጥፋት የማይተናነስ ወንጀል እየፈፀሙ ይገኛሉ።

ከድርቅ አደጋ በተጨማሪ በርካታ ቀበሌዎች በበረዶና በጎርፍ አደጋ ሰብላቸው ከጥቅም ውጭ ሆኖባቸዋል። የህወሓት አገዛዝ ለእነዚህ ተጎጂዎች “እርዳታ ስጡኝ” ብሎ ለልመና ለዓለም ማህበረሰብ እጁ ዘርግቷል።

ይሁን እንጂ አስቸኳይ እርዳታው ለፖለቲካዊ ጥቅሙ እያዋለው ይገኛል። የዚህ ወንጀል ሰለባ ከሆኑት በዓብይ ዓዲ-ሃገረሰላም ምርጫ ክልል የዓረና-መድረክ የክልል ምክርቤት እጩ ተወዳዳሪ የነበሩት አቶ ኪሮስ ታደስ እንደሌሎች የደጉዓ ተምቤን ወረዳ ደጎል ወያነ ቀበሌ ነዋሪዎች ሰብላቸው በበረዶ ከጥቅም ውጭ የሆነባቸው ሲሆኑ ለዚህ ጉዳት ለመከላከል ጥናት የሚያደርጉ የወረዳው ሹመኞች የቀበሌው ህዝብ እንደተሰበሰበ “ዓረና ይርዳህ” ተብለው ከነቤተሰባቸው ከሞት የማይተናነስ ፖለቲካዊ ውሳኔ ተወስኖባቸዋል።

ይህ ስራ በ1977 አስከፊው ድርቅ ወቅት በትግራይ ህዝብ ላይ ሻእብያ የወሰደው አስነዋሪ ውሳኔ በህወሓት እየተደገመ መሆኑ የሚያመላክት ነው።

የትግራይ ክልል መንግስት በድርቅ ለተጠቁ አከባቢዎች የውሃና ሳር ድጋፍ እስካሁን አላደረገምና እየጠፋ ያለው የእንስሳ ህይወትና በጠኔና ረሃብ ነፍስ ውጪ ነፍስ ግቢ እያለ ያለው ህዝብ አስቸኳይ እርዳታ ማድረግ ይገባዋል።

ከኦሮምያና ዓፋር ክልሎች ተሞክሮ እንዲወስድም እንጠይቃለን።

ነፃነታችን በእጃችን ነው…!

IT IS SO…!

(ፎቶ፡ ከቀድሞው ድርቅ ለማሳያነት የቀረበ)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule