• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

በትግራይ ድርቅ ህይወት እየቀጠፈ ነው!

September 23, 2015 09:43 pm by Editor Leave a Comment

* “ከብቶቻችሁን ሸጣችሁ ተገላገሉ” ህወሃት ለነዋሪዎች

የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) በሚገዛት ትግራይ ድርቅ በአስከፊ ሁኔታ ህይወት እየቀጠፈ መሆኑ ተገለጸ፡፡ ለእንስሳትም ሆነ ለሰው ዕርዳታ መስጠት ገና ባይጀመርም በሚደረገው ዕርዳታ የመስጠት ዕቅድ ውስጥ የዓረና-መድረክ አባላት የሆኑ ነዋሪዎች “ዓረና ይርዳህ” በመባል ከዕርዳታው አሠጣጥ ዕቅድ ውጪ ተደርገዋል፡፡ የህወሃት ካድሬዎች ነዋሪ ገበሬዎችን “ከብቶቻችሁን ሸጣችሁ ተገላገሉ” በማለት መመሪያ እየሰጡ ነው፡፡ አምዶም ገብረሥላሴ በፌስቡክ ገጹ ላይ ያወጣው መረጃ እንዲህ ይነበባል፡-

ድርቅ በትግራይ አስከፊ ሁኔታ ላይ በመድረሱ የቤት እንስሳ ህይወት እየቀጠፈ ነው። በትግራይ አብዛኛው ወረዳዎች የድርቅ አደጋ የተጠቁ ሲሆኑ እጅግ አስከፊ የሚባል ጉዳት ያደረሰባቸው ወረዳዎች ግን አፅቢ ወንበርታ 12 ቀበሌዎች፣ የክልተ አውላዕሎ በርካታ ቀበሌዎች፣ አብዛኛው ራያ ዓዘቦና ራያ አለማጣ ቀበሌዎች፣ የኦፍላ ግማሽ ቀበሌዎች፣ አብዛኛው ሕንጣሎ ወጀራት፣ ከግማሽ በላይ ሳምረ ሰሓርቲ፣ አብዛኛው ጣንቋ አበርገለ ወረዳ፣ የምዕራባዊ ዞን የርካታ ቀበሌዎች ናቸው።

በተጠቀሱት ወረዳዎች በድርቁ ምክንያት የእንስሳት ምግብ እጥረት አጋጥሞ በርካታ የቤት እንስሳት ለሞት ተዳርገዋል።

የትግራይ ክልል መስተዳድር ምንም ዓይነት የህይወት አድን ስራ መስራት አልቻለም። በጣም የሚያሳዝነው (አገዛዙ) ሃላፊነቱን በመዘንጋት በድርቅ ለተጠቁ አካባቢ ነዋሪ ገበሬዎች “በድርቁ ምክንያት ከብቶቻችሁን ሸጣቹችሁ ተገላገሉ” የሚል መመሪያ መስጠቱ ነው።

በጣም የሚገርመው እስካሁን ለእንስሳም ይሁን ለሰው እርዳታ ማቅረብ ያልተጀመረ ሲሆን በድርቅ የተጠቁ ቀበሌዎች ነዋሪ የሆኑት የዓረና አባላት ከጥናቱ ውጭ እያደረጓቸው ይገኛሉ።

ለምሳሌ በኦፍላ ወረዳ ዓረና-መድረክን ወክሎ ለክልል ምክር ቤት እጩ ተወዳዳሪ የነበረው አቶ ጡዕማይ ስዩም “ዓረና ይርዳህ” በማለት ከእርዳታው ውጭ በማድረግ ከነፍስ ማጥፋት የማይተናነስ ወንጀል እየፈፀሙ ይገኛሉ።

ከድርቅ አደጋ በተጨማሪ በርካታ ቀበሌዎች በበረዶና በጎርፍ አደጋ ሰብላቸው ከጥቅም ውጭ ሆኖባቸዋል። የህወሓት አገዛዝ ለእነዚህ ተጎጂዎች “እርዳታ ስጡኝ” ብሎ ለልመና ለዓለም ማህበረሰብ እጁ ዘርግቷል።

ይሁን እንጂ አስቸኳይ እርዳታው ለፖለቲካዊ ጥቅሙ እያዋለው ይገኛል። የዚህ ወንጀል ሰለባ ከሆኑት በዓብይ ዓዲ-ሃገረሰላም ምርጫ ክልል የዓረና-መድረክ የክልል ምክርቤት እጩ ተወዳዳሪ የነበሩት አቶ ኪሮስ ታደስ እንደሌሎች የደጉዓ ተምቤን ወረዳ ደጎል ወያነ ቀበሌ ነዋሪዎች ሰብላቸው በበረዶ ከጥቅም ውጭ የሆነባቸው ሲሆኑ ለዚህ ጉዳት ለመከላከል ጥናት የሚያደርጉ የወረዳው ሹመኞች የቀበሌው ህዝብ እንደተሰበሰበ “ዓረና ይርዳህ” ተብለው ከነቤተሰባቸው ከሞት የማይተናነስ ፖለቲካዊ ውሳኔ ተወስኖባቸዋል።

ይህ ስራ በ1977 አስከፊው ድርቅ ወቅት በትግራይ ህዝብ ላይ ሻእብያ የወሰደው አስነዋሪ ውሳኔ በህወሓት እየተደገመ መሆኑ የሚያመላክት ነው።

የትግራይ ክልል መንግስት በድርቅ ለተጠቁ አከባቢዎች የውሃና ሳር ድጋፍ እስካሁን አላደረገምና እየጠፋ ያለው የእንስሳ ህይወትና በጠኔና ረሃብ ነፍስ ውጪ ነፍስ ግቢ እያለ ያለው ህዝብ አስቸኳይ እርዳታ ማድረግ ይገባዋል።

ከኦሮምያና ዓፋር ክልሎች ተሞክሮ እንዲወስድም እንጠይቃለን።

ነፃነታችን በእጃችን ነው…!

IT IS SO…!

(ፎቶ፡ ከቀድሞው ድርቅ ለማሳያነት የቀረበ)


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Filed Under: Opinions Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule