• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያ ጣምራ ፌደራሊዝም ተቋም

January 28, 2020 05:52 am by Editor Leave a Comment

ኢትዮጵያ ወደ ፍጹም ህብረት! Towards a Perfect Union! ቀን 1/27/20

የኢትዮጵያ ጣምራ ፌደራሊዝም ተቋም የመጀመሪያ ሰሚናሩን አጠናቀቀ!

የኢትዮጵያ ጣምራ ፌደራሊዝም ተቋም (DFIE Dual Federalism Institute for Ethiopia) በ January 18, 2020, በኢትዮጵያ ኤምባሲ አዳራሽ ውስጥ ክቡር አምባሳደር ፍጹም አረጋን ጨምሮ የተለያዩ የፖለቲካና ሲቪክ ድርጅት ተወካዮችና ምሁራን በተገኙበት የአንድ ቀን ሙሉ ሰሚናር አድርጓል።

በዚህ ሰሚናር ላይ ለኢትዮጵያ ተብሎ የተዘጋጀውን አዲስ ቅርጸ መንግስት (Government Structure) አስተዋውቋል። ይህ አዲስ ቅርጸ መንግስት የኢትዮጵያ ጣምራ ፌደራሊዝም ይሰኛል። በዚሁ እለት የኢትዮጵያውያንን ህብረት ታሪካዊ ጉዞ በመገምገም ህብረታችንን ወደ ፍጹም ህብረት ሊያደርስ ይችላል በተባለው በዚሁ በጣምራ ፌደራሊዝም እሳቤ ዙሪያ ሰፊ ገለጻና ውይይት ተደርጓል። ኢትዮጵያ ያለፈችባቸው የሃገረ መንግስት ግንባታ (Nation Building) ሂደቶች በጥልቀት ተገምግመዋል። በዚሁ መሰረት ከምስለት ጀምሮ “ኢትዮጵያ ትቅደም!” ከዚያም “ብሄር ይቅደም!” ከዚያም አፍርሶ ማነጽ (deconstruct identities in order to construct identities) የተከተልናቸው የህብረታችን ወይም የሃገረ መንግስት ግንባታ ጥበቦቻችን ሲሆኑ እነዚህ ጥበቦቻችን በሙሉ ችግሮች ያሉባቸውና ህብረታችንን የሚፈታተኑ አደጋዎች እንደሆኑ ተገልጿል።

ስለሆነም ኢትዮጵያ በሀገር ግንባታ ሂደቷ ኣዲስ የተሻለ ሃገረ መንግስት የማነጽ መንገድ ልትከተል እንደሚገባ በተቋሙ መሪዎች በአጽኖት ተገልጿል። ስለሆነም ጣምራ ፌደራሊዝም እስከዛሬ የሄድንባቸውን መንገዶች አሻሽሎ ማንነቶችን አጣምሮ ብዝሃነትን የሚያስተናግድ ዘዴ እንደሆነ በጥልቀት ትንታኔ ተሰጥቶበታል። የጣምራ ፌደራሊዝምን አደረጃጀት በሚመለከት ሲገለጽ ጣምራ ፌደራሊዝም የጣምራ ፌደራል ስቴት ግንባታ እንደሆነ ተተንትኗል። ጣምራ ፌደራሊዝም ማለት “የብሄር ባህላዊ ፌደራል ስቴትና የዜግነት ፌደራል ስቴት በመመስረት እነዚህን ሁለት ስቴቶች በሃገራዊ ኪዳን ስር በማጣመር በራሳቸው ምህዋር ላይ እየዞሩ ብዝሃነትን ጠብቀው ለጋራው በጎነታችን (common good) የሚሰሩበት ቅርጸ መንግስት ማለት ነው!“ ሲሉ የጥናት ወረቀት አቅራቢዎች የጣምራ ፌደራሊዝምን ብያኔ አስረድተዋል::

ጣምራ ፌደራሊዝም የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታዎች፣ ታሪክ፣ የፖለቲካ ጥያቄዎችና ብዝሃነትን ያገናዘበ ሁነኛ ቅርጸ መንግስት መሆኑ ተብራርቷል። ይህ ተቋም ዓላማው ይህ ሃገር በቀል ቅርጸ መንግስት ብሄራዊ ፍኖተ ካርታ ሆኖ የፖለቲካ ሃይላትና መላው ኢትዮጵያዊ ተስማምቶበት ለመድብለ ፓርቲ ስርዓት መጫወቻ ሜዳ እንዲሆን ብሎም ጣምራ ፌደራሊዝም ብዝሃነትንና ዴሞክራሲን ለማስተናገድ ምቹ የሆነ ስርዓት ስለሆነ ሃገራችን ይህንን ስርዓት ተክላ በፍጥነት ወደ ዴሞክራሲና ልማት እንድታመልጥ ነው። በዚህ ስብሰባ ወቅት አሁን ያለው የፌደራል ስርዓት ያሉት ህጸጾች በጥልቀት ተገልጸዋል። ባህልና ፖለቲካን አደባልቆ መኖር ችግሮቹ ብዙ እንደሆኑ በአንክሮት ተገልጿል። ባህል ከፖለቲካ ተለይቶ ለሃገር ሁለንተናዊ እድገት የራሱን ሚና መጫወት እንዳለበት በሰፊው ትንታኔ ተሰጥቶበታል።

በመጨረሻም የጣምራ ፌደራሊዝም ተቋም ንቅናቄ ዓላማ ህብረታችንን በጣምራ ፌደራሊዝም ስርዓት ወደ ፍጹም ህብረት ማሳደግ ነው ተብሏል። የተቋሙ መስራቾች ሲናገሩ በአሁኑ ወቅት ያለው የኢትዮጵያውያን ህብረት ፍጹምነት የጎደለው በመሆኑ ህብረታችን ፈራሽ ሳይሆን ፍጹምና ዘላለማዊ ሆኖ በሌላ በኩል ደግሞ ብዝሃነትን የሚያስተናግድ እንዲሆን ኢትዮጵያ ጣምራ ፌደራሊዝም ስርዓትን መትከል እንደሚገባት ምክር ቀርቧል። ኢትዮጵያ በዚህ ኣዲስ የፌደራል ስርዓት አማካኝነት ወደ ፍጹም ህብረት ልታድግ ይገባል ተብሏል። ተሰብሳቢዎች በቡድን በቡድን እየሆኑ በእሳቤው ላይ በስፋት የተወያዩ ሲሆን ገንቢ ሃሳቦችን ሰጥተዋል። በቀውጢ ወቅት የደረሰ ችግር ፈቺ ነው የተባለው ይህ ሃገር በቀል የፌደራል ስርዓት ወይም ቅርጸ መንግስት እሳቤ ወደፊት ተከታታይ ውይይቶች ተደርገውበት ብሄራዊ ፍኖተ ካርታ እንዲሆን ጥረት እንደሚደረግ የጣምራ ፌደራሊዝም ተቋም መሪዎች እስረድተዋል። ኢትዮጵያ ካሉባት ስርዓታዊ ችግሮች ዘ-ጸዓት አውጃ ከችግሮቿ ልትወጣ እንደሚገባ አቋም ተወስዷል።

በመጨረሻም የጣምራ ፌደራሊዝም ዓላማው ተሳክቶ፣ ኢትዮጵያ ይህንን ስርዓት ተክላ፣ የስርዓት ችግሮቿን እድትፈታ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የሲቪክ ድርጅቶች፣ ምሁራንና መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ድጋፉን እንዲቸር ተጠይቋል።

የኢትዮጵያ ጣምራ ፌደራሊዝም ተቋም!


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule