• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያ ጣምራ ፌደራሊዝም ተቋም

January 28, 2020 05:52 am by Editor Leave a Comment

ኢትዮጵያ ወደ ፍጹም ህብረት! Towards a Perfect Union! ቀን 1/27/20

የኢትዮጵያ ጣምራ ፌደራሊዝም ተቋም የመጀመሪያ ሰሚናሩን አጠናቀቀ!

የኢትዮጵያ ጣምራ ፌደራሊዝም ተቋም (DFIE Dual Federalism Institute for Ethiopia) በ January 18, 2020, በኢትዮጵያ ኤምባሲ አዳራሽ ውስጥ ክቡር አምባሳደር ፍጹም አረጋን ጨምሮ የተለያዩ የፖለቲካና ሲቪክ ድርጅት ተወካዮችና ምሁራን በተገኙበት የአንድ ቀን ሙሉ ሰሚናር አድርጓል።

በዚህ ሰሚናር ላይ ለኢትዮጵያ ተብሎ የተዘጋጀውን አዲስ ቅርጸ መንግስት (Government Structure) አስተዋውቋል። ይህ አዲስ ቅርጸ መንግስት የኢትዮጵያ ጣምራ ፌደራሊዝም ይሰኛል። በዚሁ እለት የኢትዮጵያውያንን ህብረት ታሪካዊ ጉዞ በመገምገም ህብረታችንን ወደ ፍጹም ህብረት ሊያደርስ ይችላል በተባለው በዚሁ በጣምራ ፌደራሊዝም እሳቤ ዙሪያ ሰፊ ገለጻና ውይይት ተደርጓል። ኢትዮጵያ ያለፈችባቸው የሃገረ መንግስት ግንባታ (Nation Building) ሂደቶች በጥልቀት ተገምግመዋል። በዚሁ መሰረት ከምስለት ጀምሮ “ኢትዮጵያ ትቅደም!” ከዚያም “ብሄር ይቅደም!” ከዚያም አፍርሶ ማነጽ (deconstruct identities in order to construct identities) የተከተልናቸው የህብረታችን ወይም የሃገረ መንግስት ግንባታ ጥበቦቻችን ሲሆኑ እነዚህ ጥበቦቻችን በሙሉ ችግሮች ያሉባቸውና ህብረታችንን የሚፈታተኑ አደጋዎች እንደሆኑ ተገልጿል።

ስለሆነም ኢትዮጵያ በሀገር ግንባታ ሂደቷ ኣዲስ የተሻለ ሃገረ መንግስት የማነጽ መንገድ ልትከተል እንደሚገባ በተቋሙ መሪዎች በአጽኖት ተገልጿል። ስለሆነም ጣምራ ፌደራሊዝም እስከዛሬ የሄድንባቸውን መንገዶች አሻሽሎ ማንነቶችን አጣምሮ ብዝሃነትን የሚያስተናግድ ዘዴ እንደሆነ በጥልቀት ትንታኔ ተሰጥቶበታል። የጣምራ ፌደራሊዝምን አደረጃጀት በሚመለከት ሲገለጽ ጣምራ ፌደራሊዝም የጣምራ ፌደራል ስቴት ግንባታ እንደሆነ ተተንትኗል። ጣምራ ፌደራሊዝም ማለት “የብሄር ባህላዊ ፌደራል ስቴትና የዜግነት ፌደራል ስቴት በመመስረት እነዚህን ሁለት ስቴቶች በሃገራዊ ኪዳን ስር በማጣመር በራሳቸው ምህዋር ላይ እየዞሩ ብዝሃነትን ጠብቀው ለጋራው በጎነታችን (common good) የሚሰሩበት ቅርጸ መንግስት ማለት ነው!“ ሲሉ የጥናት ወረቀት አቅራቢዎች የጣምራ ፌደራሊዝምን ብያኔ አስረድተዋል::

ጣምራ ፌደራሊዝም የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታዎች፣ ታሪክ፣ የፖለቲካ ጥያቄዎችና ብዝሃነትን ያገናዘበ ሁነኛ ቅርጸ መንግስት መሆኑ ተብራርቷል። ይህ ተቋም ዓላማው ይህ ሃገር በቀል ቅርጸ መንግስት ብሄራዊ ፍኖተ ካርታ ሆኖ የፖለቲካ ሃይላትና መላው ኢትዮጵያዊ ተስማምቶበት ለመድብለ ፓርቲ ስርዓት መጫወቻ ሜዳ እንዲሆን ብሎም ጣምራ ፌደራሊዝም ብዝሃነትንና ዴሞክራሲን ለማስተናገድ ምቹ የሆነ ስርዓት ስለሆነ ሃገራችን ይህንን ስርዓት ተክላ በፍጥነት ወደ ዴሞክራሲና ልማት እንድታመልጥ ነው። በዚህ ስብሰባ ወቅት አሁን ያለው የፌደራል ስርዓት ያሉት ህጸጾች በጥልቀት ተገልጸዋል። ባህልና ፖለቲካን አደባልቆ መኖር ችግሮቹ ብዙ እንደሆኑ በአንክሮት ተገልጿል። ባህል ከፖለቲካ ተለይቶ ለሃገር ሁለንተናዊ እድገት የራሱን ሚና መጫወት እንዳለበት በሰፊው ትንታኔ ተሰጥቶበታል።

በመጨረሻም የጣምራ ፌደራሊዝም ተቋም ንቅናቄ ዓላማ ህብረታችንን በጣምራ ፌደራሊዝም ስርዓት ወደ ፍጹም ህብረት ማሳደግ ነው ተብሏል። የተቋሙ መስራቾች ሲናገሩ በአሁኑ ወቅት ያለው የኢትዮጵያውያን ህብረት ፍጹምነት የጎደለው በመሆኑ ህብረታችን ፈራሽ ሳይሆን ፍጹምና ዘላለማዊ ሆኖ በሌላ በኩል ደግሞ ብዝሃነትን የሚያስተናግድ እንዲሆን ኢትዮጵያ ጣምራ ፌደራሊዝም ስርዓትን መትከል እንደሚገባት ምክር ቀርቧል። ኢትዮጵያ በዚህ ኣዲስ የፌደራል ስርዓት አማካኝነት ወደ ፍጹም ህብረት ልታድግ ይገባል ተብሏል። ተሰብሳቢዎች በቡድን በቡድን እየሆኑ በእሳቤው ላይ በስፋት የተወያዩ ሲሆን ገንቢ ሃሳቦችን ሰጥተዋል። በቀውጢ ወቅት የደረሰ ችግር ፈቺ ነው የተባለው ይህ ሃገር በቀል የፌደራል ስርዓት ወይም ቅርጸ መንግስት እሳቤ ወደፊት ተከታታይ ውይይቶች ተደርገውበት ብሄራዊ ፍኖተ ካርታ እንዲሆን ጥረት እንደሚደረግ የጣምራ ፌደራሊዝም ተቋም መሪዎች እስረድተዋል። ኢትዮጵያ ካሉባት ስርዓታዊ ችግሮች ዘ-ጸዓት አውጃ ከችግሮቿ ልትወጣ እንደሚገባ አቋም ተወስዷል።

በመጨረሻም የጣምራ ፌደራሊዝም ዓላማው ተሳክቶ፣ ኢትዮጵያ ይህንን ስርዓት ተክላ፣ የስርዓት ችግሮቿን እድትፈታ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የሲቪክ ድርጅቶች፣ ምሁራንና መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ድጋፉን እንዲቸር ተጠይቋል።

የኢትዮጵያ ጣምራ ፌደራሊዝም ተቋም!


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣበ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “ሚካኤል ችግኝ ነው። … ችግኝ ይተክላል” ቴዲ አፍሮ June 29, 2022 03:30 am
  • “የእኔን ልጆችና የልጅ ልጆች (22ቱንም) የቀበርኩት እኔ ነኝ” አቶ መሀመድ የሱፍ ከምዕራብ ወለጋ June 28, 2022 01:07 pm
  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule