• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአቶ ዠ የልማታዊ አርቲስትነት ደብዳቤ

December 6, 2015 11:34 pm by Editor Leave a Comment

አቶ ዠ ደብዳቤ ጻፉ። 40 አመት ሙሉ መፈክር ሲጽፉ ኖረው፣ ኖረው፣ ኖረው አሁን አርቲስት ለመሆን የሚያበቃውን ዝግጅት የጨረሱ መስሎ ተሰማቸው። ሰሞኑን ለወጣው ማስታወቂያ “ብቁ ነኝ” ብለው አሰቡ።

ይድረሥ፣ ለ“ኢሃዲግ ፍቅር” ቴአትር ቤት “ሥራ አስቀማጭ”፣ ይቅርታ በቀድሞ ሥሙ የሃገር ፍቅር ቴአትር ቤት በመባል ለሚታወቀው … ሥራ አስኪያጅ፣

ጉዳዩ፣ በ 23/2/2008 የወጣውን ማስታወቂያ አስመልክቶ፣ ከታች እንደሚታየው፣ የተለያዩ ኪነጥበባዊ ሥራዎችን ለማቅረብ “ልማታዊ” ፍላጎትን ሥለመግለጽ።

የወጣውን ማስታወቂያ አስታኮ የተለያዩ ልማታዊ ኪነጥበባዊ ሥራዎችን ለማቅረብ 40 አመታት ሙሉ ተዘጋጅቻለሁ፣ ብቃት ያለኝም ነኝ። ከዚህ ኪነጥበባዊ ሥራ የሚገኘው ገቢም በከፊል ለታላቁ “ውዳሴ” ግድብ ቦንዳ (ይቅርታ “ቦንድ”) መግዣ እንዲውል ለመስማማት በገዛ ፍላጎቴ እገደዳለሁ። ይቅርታ ህዳሴ ማለቴ ነው። እኔ ዠ “ግድቡ ገና ሳይጀመር እራሳችሁን ለማወደስ ትጠቀሙበታላችሁ፣ ማለቁን እስኪ ለማየት ‘ገብረ እግዚሃብሄር’ ያብቃን” ብዬ በመጻፍ አልሳሳትም።hager fiqir

እነዚህ ኪነጥበባዊ ሥራዎቼን ለመከተብ የምጠቀምባቸው እስክሪብቶዎች ከዶማ ባለተናነሰ ወረቀቴን እየቆፈሩ ልማታዊ አርቲስት ለመሆን መነሳሳቴን ይመሰክራሉ ብል መንግሥታችን “ጣምራ ዲጂት እድገት አስመዘገብኩ” እንደሚለው አይነት መልካም ምኞት እንጂ አንዳንድ ኢ-ልማታዊ አሸባሪዎች እንደሚያቀርቡት ለዛ ቢስ ትችት እንደማይታይብኝ የሥራ አስቀማጭነትዎ የሰላ አይምሮ አይስተውም ብዬ ልጽፍ አልደፍርም።

ከውዳሴው ግድብ ተጨማሪ ስለሴቶች ተጠቃሚነትም ለመጻፍም ልማታዊ ምኞቴ ነው። መንግስታችን ሴቶች እህቶቻችንና እራሱን ተጠቃሚ ለማድረግ ልማታዊ ፈቃዱ በመሆኑ እልፍ አእላፍ ሴቶች ወደየአረብ ሃገራት እንዲሄዱና የእነዚህን ሃገራት ጓዳዎች እንዲያለሙ “መንገዱን ጨርቅ ያርግላችሁ” ብሏል። እነዚህ የሚሄዱት ሴቶች ደግሞ ድሆች በመሆናቸው በሌላ መልኩ መንግስታችን ድህነትን ለመቅረፍ የተጠቀመበት፣ በጣም የታሰበበት የተራቀቀ የGrowth and Transformation Plan – GTP እንጂ የGet out and Transform to slave Plan ተሰደጂና ባሪያ ሁኝ ስትራተጂ አለመሆኑን ለነዚህ ኢ-ልማታዊ አርቲስቶች ማን በነገራቸው? ክቡር ሥራ አስቀማጭነትዎ እንደሚገነዘቡት ለዚህ ነው የመፈክር መጻፊያ ብዕሬን ወደ ኪነጥበባዊ ብዕር ለመቀየር የተነሳሳሁት።

ደግሞ፣ ልማታዊው መንግሥታችን ወጣቶችን ተጠቃሚ አርቲስት ለማድረግ ከፍተኛ እቅድ በመያዙ ለምሳሌ ያክል ድንጋይ መልካም ቅርጽ እንዲኖረው በመጥረብ ኮብል ስቶን እንዲያነጥፉ ቤቶችን በማፈራረስ ጎዳናዎችን አዘጋጅቷል። እንግዲህ ይህ ጥበባዊ ሥራ ነው። እነማይክል አንጀሎ ድንጋይ በመጥረብ አይደለም እንዴ ታዋቂ የሆኑትና ጣልያንን ገናና ያደረጉት?

በሌላ መልኩ ደግሞ መንግስታችን ገደላ ገደል፣ በረሃ ሳይፈራ የባቡርና የመኪና መንገድ እያስፋፋ ነው። ክቡር ሥራ አስቀማጭነትዎ ደብዳቤዬን ከማጠቃለሌ በፊት አንድ የባቡር ሃዲድ ታሪክ ታሪክ ልጻፍልዎ።

ሃዲዱ የሺምላ ካልካ የባቡር ሃዲድ ነው። ህንድ ውስጥ የሚገኝ፣ በእንግሊዞች የተሰራ። ደልሂ ከተማን ከሂማልያ ተራሮች እግር የሚያገናኝ የባቡር ሃዲድ። ይህ ሃዲድ ሲዘረጋ እጅግ አስቸጋሪ ነበር። ተራሮችን ሰርስሮ መሿለኪያ መሥራት ያስፈልግ ነበር። ከሁሉም ረጅሙ መሿለኪያ 1143 ሜትር ይረዝማል።

ይህንን መሿለኪያ(tunnel)የቀየሰው የእንግሊዝ መሃንዲስ ባሮግ ይባላል። ኢንጂነር ባሮግ ሥራውን በቶሎ ለማጠናቀቅ ይረዳው ዘንድ ተራራው በሁለት በኩል እንዲቦረቦር ያቅዳል። እቅዱም ከሁለት አቅጣጫ መሿለኪያዎች ሲቦረቡሩ መሃል ላይ ይገጣጠማሉ የሚል ነበር። ሆኖም ግን ቅያሱ ትንሽ ስህተት ስለነበረበት ከሁለት አቅጣጫ የተቦረቦሩት መሿለኪያዎች እንደታቀደው ሳይገናኙ ቀሩ። በዚህ የተናደደው የብሪታንያ መንግሥት ኢንጂነር ባሮግን አንድ ሩፒ ቀጣው። ሩፒ የህንድ ገንዘብ ነው።የተጣለበትን ሃላፊነት አለመወጣቱን የተገነዘበውና ይህ ፕሮፌሽናል ሥህተት ያበሣጨው ኢንጂነር ባሮግ ደግሞ እራሱን ገደለ። ዛሬ ያ መሿለኪያ የባሮግ መሿለኪያ – Barog Tunnel በመባል ይታወቃል።

እንግዲህ እንደዚህ ያሉ ትላልቅ ፕሮጄክቶችን፣ ለምሳሌ የሥኳር ፋብሪካዎችን፣ የሚወጥነው ልማታዊው መንግሥታችን፣ ብዙ ገንዘብ አፍስሶ ውጥኑ ሳይሳካለት ቢቀር እራሱን ያጥፋ የሚል አመለካከት ያላቸው ኢ-ልማታዊ የሆኑ፣ ጥቂት ግለሰቦች ሊኖሩ ይችላሉና በልማታዊ ብዕር ልንዋጋቸው ይገባል ባይ ነኝ።

ፊርማ

ዠ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ፡፡ ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am
  • በትግራይ የሰላም ስምምነቱን መሠረት ያደረገ የሽግግር ፍትሕ እንደሚፈጸም ተገለጸ December 13, 2022 09:20 am
  • ከ30 ሚሊየን ብር በላይ በሚሆን ሌብነት የተከሰሱት የደኅንነት መ/ቤት ሠራተኞች ክስ ተመሰረተ December 13, 2022 09:06 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule