• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አምባገነናዊነትን እያስታመሙ መቅበርም ይቻላል!

June 6, 2018 06:09 am by Editor Leave a Comment

የአንባገነናዊ ሥርዓት ሞት ሁለት መልክ ያለው ነው። አንደኛው ከሱ የፈረጠመ ጡንቻ ባለው ወይም በሕዝባዊ አመጽ ድባቅ ተመቶ በሱ መቃብር ሌላ ጉልበተኛ ወይም ሕዝባዊ መንግሥት የሚሾምበት ሁኔታ ሲፈጠር ነው። ሁለተኛው ሞት ደግሞ እያዋዛ እና ረዥም ጊዜ የሚወስድ በረዥም ጣርና የስቃይ ጉዞ ውስጥ የሚመጣ ሞት ነው። በሰው ብንወስደው የመጀመሪያው በድንገተኛ አደጋ ወይም በቀናቶች ህመም የሚሞት ሰው ሲሆን ሁለተኛው ሞት ደግሞ እያንዳንዱ የሰውነት ክፍሉ አንድ በአንድ እየከዳውና ከጥቅም ውጭ እየሆነ በስቃ ውስጥ ለተራዘመ ጊዜ ወይም ለአመታት ቆይቶ የሚሞት ሰው ነው።

የአንድን አንባገነናዊ ሥርዓት የሞት ፍጥነት የሚለካው ለሥርዓቱ መሞት ምክንያት በሆነው ገፊ ኃይል መጠንና ፍጥነት ነው። አዝጋሚና ደክም ያለ ግፊት ሲሆን ሥርዓቱን መግደሉ ባይቀርም ሞቱን አዝጋሚ ያደርገዋል። በተቃራኒው ግፊቱ ፈጣን እና ከተገፊው ሥርዓት አቅም ጋሪ ሲነጻጸርም እጅግ የገዘፈ ከሆነ የተገፊው ሥርዓት ሞት ፈጣን ይሆናል። ለዚህም በቅርቡ በአንዳንድ የአረብ አገሮች የታዩ ሥር ነቀል ለውጦች ጥሩ ምስክሮች ናቸው።

በአገራችን የቅርብ ጊዜ ታሪክ ውስጥ የታዩትን መንግስታዊ ለውጦች የተመለከትን እንደሆን ሥር ነቀል ስለሆኑ በአንዱ ሥርዓት መቃብር ሌላው እየተተካ ነው የመጣነው። በእነዚህ ለውጦች አገርን የበደሉ ብቻ ሳይሆኑ ለአገር መልካም የሰሩ በርካቶች ጭምር የለውጦቹ ሰለባ ሆነዋል። ሂደቱም ሥርነቀል የአንባገነኖች መተካካት ነው የሆነው። በቅርቡ በአገራችን እየታየ ያለው የመንግስት ሳይሆን የፖለቲካ ለውጥ ይህን አዙሪት የሰበረ ይመስላል። ምንም እንኳን የለውጥ ግፊቱ የመጣው ከሕዝብ ቢሆንም የለውጡን ሂደት ሊቆጣጠር የሚችልና በቂ አቅም የገነባ የተደራጀ የፖለቲካ ኃይል ባለመኖሩ የተነሳ የለውጥ ሂደቱን የተቆጣጠረው እራሱ የአገዛዝ ሥርዓቱ ነው። ይህ ደግሞ ስር ነቀል በሆነ ለውጥ በሌላ የለውጥ ኃይል የመተካት እድሉ እንዲጨናገፍ ተደርጓል። ስለዚህ ለውጡ የሥርዓት ሳይሆን ፖለቲካ ብቻ እንዲሆን አድርጎታል። ይህ የፖለቲካ ለወጥ የሥርዓቱን አንባገነናዊ ባህሪ እያስታመሙ በሂደት እንዲሞት እና በሚደረጉትም ለውጦች በአንባገነናዊነት ቦታ ዲሞክራሲያዊነት እንዲያብብ ማድረግ ነው።

አንድ አንባገነናዊ ሥርዓት በሕዝብ ግፊት እራሱን እንዲያርቅ ሲገደድ እና የመጣውን የሕዝብ ግፊት ተቋቁሞ በሥልጣን መቆየት ሲችል ሁለት እድሎች ይኖሩታል። አንደኛው እራሱን አርቆና አስተካክሎ ሕዝብ በሚፈልገው መልክና ቅርጽ በማስተካከል በቀጣዩ የአገሪቱ የፖለቲካ ሂደት ውስጥ ዋና ተሳታፊ መሆን ነው። ሁለተኛው ደግሞ Aristotle ከብዙ አመታት በፊት እንዳለው “. . . tyranny can also change into tyranny. . .” ሥርዓቱ ወደ ከፋ አንባገነናዊነት በመቀየር የሕዝቡን ግፊትና የለውጥ ተነሳሽነት ማጨናገፍና ማዳፈን ነው።

ዛሬ ኢትዮጵያ ያለችበት ሁኔታ አንባገነናዊ ሥርዓትን እያስታመሙ መቅበር ነው። ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ወደ ሥልጣን ከመጡበት ጊዜ አንስቶ የወሰዷቸውን እርምጃዎች ከስሜታዊነት በጸዳ በጥንቃቄ የታዘብን ከሆነ ይህንን ነው የሚያሳየው። ጠ/ሚኒስትር አብይ የተጋፈጡት የ27 አመት የወያኔን አንባገነናዊነትን ብቻ ሳይሆን በአገሪቱ ውስጥ ለዘመናት ከአንዱ አንባገነን ወደ ሌላኛው አንባገነን እየተሸጋገረ ከመጣው የፈላጭ ቆራጭነት አስተሳሰብ ግር ጭምር ነው። ብዙ ተቺዎቻቸው ይህን ይህን አላክናወኑም እያሉ ሲዘረዝሩ፤ ቀሪዎቹ ደግሞ እስከ አሁን ያከናወኗቸውን ሁሉ በዜሮ እያባዙ ድካማቸውን መና ለማስቀረት ሲሞክሩ ይስተዋላል። እንዳንዴም የተወሰኑትን ለውጦች በመቀብለ ይልቅስ የለውጡ ባለቤት እኔ ወይም እኛ ነን ሲሉም የሚስተዋሉ አሉ። ለማንኛውም ጠ/ሚኒስትሩ የሚመሩት አስተዳደር ከዚህ የሚከተሉት አንኳር ለውጦችን አስመዝግቧል። እያንዳንዱ ለውጥ ለአገር ሰላም፣ ለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ፣ ለኢኮኖሚ መሻሻል እና ለአገር አንድነት ያለውን ፋይዳ መመዘን ይቻላል። ለአሁን የታዩትን አንኳር ለውጦች ልጥቀስ።

  • የፖለቲከኛ እስረኞች መፈታት፣
  • በመንግሥት ተቋማት ውስጥ በተለይም በመከላከያ እና በደህንነት ተቋማት ውስጥ እየታዩ ያሉት ለውጦች፣
  • ሥርዓቱ ለአፈና መዋቅሩ እና ለምዝበራ ይጠቀምባቸው የነበሩ ትቋማትን ማጽዳት እና አንዳንዶቹንም በከፊልም ቢሆን በግል ባለኃብቶች እንዲያዙ መወሰናቸው፣
  • ከኤርትራ ጋር ያለውን ፍጥጫ ለመቋጨት ለረዥም ጊዜ በህውሃት ተዘግቶ የነበረውን የእርቅ መንገድ መክፈታቸው፣
  • ጎምቱ የሚባሉ የህውኃት የጦር ጀነራሎች እና የደህንነት አመራሮች ሂደቱን እንዳያደናቅፉ ከመንገዳቸው ላይ ገሸሽ ማድረጋቸው፣
  • የወያኔ ጥርስ ውስጥ የገቡና በመፈንቅለ መንግስት ተጠርጥረው የታሰሩ የጦር ጀነራሎችን በምህረት ለቆ፣ ማእረጋቸው እንዲመለስ እና ጡረታቸው እንዲጠበት ማድረግ፣
  • ዋና ዋና ለሚባሉ የተቃዋሚ ድርጅቶች የድርድር ጥሪ ማቅረባቸው እና

ሌሎች እየወሰዷቸው ያሉ ተመሳሳይና ቀላል ግምት የማይሰጣቸው እርምጃዎች ሥርዓቱ ውስጥ ቀንድ ያበቀለውን አንባገነናዊነት ቀስ በቀስ እየገደሉ ለመሆኑ ከበቂ በላይ ማሳያዎች ናቸው።

አንባገነናዊነትን አንዴ መግደል እንጂ ማስታመም ለምን አስፈለገ የሚል ጥያቄ ይነሳ ይሆናል። ይህ አይነቱ ሥር ነቀል ለውጥ በምኞት አይገኝም። እጅግ ከፍ ያለ የሰው ሕይወት እና የአገር ሃብት ያስከፍላል። በቃኝ የማያውቅ የአገዛዝ ሥርዓት ሽንፈትን የሚቀበለው ሲሞት ብቻ ነው። ያ ባይሆን እማ ጋዳፊ እና ሳዳም ሁሴን የአውሬ ሞት ባልሞቱ ነበር። አገራቸው ወድሞና ሕዝባቸው ተሰዶ የወንበዴዎች መፈንጫ ባልሆነ ነበር። ከአንባገነኖች ጋር አብራ የምትሞት አገር እንድትኖረው የሚፈልግ ሰው ያለ አይመስለኝም። ስለዚህ እያስታመሙም ቢሆን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ አንባገነናዊ ሥርዓትን ከኢትዮጵያ ለመሸኘትና ታሪክ ሆኖ እንዲቀር ለማድረግ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድን ስህተታቸውን እያረሙም በጀመሩት የለውጥ ጉዞ እንዲገፉበት ከማበረታታት የተሻለ አማራጭ ያለ አይመስለኝም።

የፖለቲካል ሳይንስ ፕሮፌሰር እና የአልበርት አንስታይን የምርምር ተቋም መስራች የሆነው Gene Sharp “From Dictatorship to Democracy” (1993) በሚለው ድንቅ መጽሐፉ ውስጥ አንባገነናዊነትን በሂደት እያስታመሙ ስለመግደል ያሰፈረውን ነገር ጠቅሼ ጽሑፌን ልደምድም

“No one should believe that with the downfall of the dictatorship an ideal society will immediately appear. The disintegration of the dictatorship simply provides the beginning point, under conditions of enhanced freedom, for long-term efforts to improve the society and meet human needs more adequately. Serious political, economic, and social problems will continue for years, requiring the cooperation of many people and groups in seeking their resolution. The new political system should provide the opportunities for people with varying outlooks and favored measures to continue constructive work and policy development to deal with problems in the future.”

ቸር እንሰንብት

ያሬድ ኃይለማርያም (yhailema@gmail.com)
ሰኔ 6፣ 2018 እ.አ.አ


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule