• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሐጃጆች ሞት

September 25, 2015 12:06 am by Editor Leave a Comment

ለሐጅ ጉብኝት የተጓዙ በብዙ መቶ የሚቆጠሩ ምዕመናን ትናንት ሚና-ሳዑዲ አረቢያ ዉስጥ ድንገት በመሞታቸዉ የሐገራት መሪዎችና የድርጅት ተጠሪዎች የሚያስተላልፉት የሐዘን መግለጫ፤ የሐይማኖት መሪዎች ፀሎት ዛሬም እንደቀጠለ ነዉ። በአደጋዉ 717 ሰዎች ሞተዋል፤ ከ800 በላይ ቆስለዋል። የሳዑዲ አረቢያ ገዢዎች የአደጋዉ ትክክለኛ መንሥኤ እንዲጣራ አዘዋል።ኢራን ግን ለአደጋዉ የሪያድ ነገሥታት ሐላፊነቱን እንዲወስዱ አሳስባለች።በሐጂ ጉብኝት ወቅት ተደጋጋሚ አደጋዎች ቢደርሱም በርካታ ሠዉ የሞተበት አደጋ ሲደርስ በሃያ-አምስት ዓመት ዉስጥ የትናንቱ የመጀመሪያዉ ነዉ።

ከመካዉ ዓል-ሐራም እስከ ሞስኮዉ ካቴድራል፤ ከምሥራቅ ለንደኑ እስከ ካይሮዉ አል-አዝሐር፤ ከካምፓላዉ ቃዛፊ፤ እስከ እየሩሳሌሙ ዓል-አቅሳ፤ ከዓለም መሳጂዶች የሚንቆረቆረዉ ዱዓ፤ምልጃ ዛሬም እንደቀጠለ ነዉ።ከዋይት ሐዉስ እስከ ክሬምሊን ያሉ አብያተ-መንግሥታትም የሐዘን መግለጫዉን እያጎረፉት ነዉ።የሐገራት፤የድርጅቶችና የሐይማኖት መሪዎችም እንዲሁ።

በዱዓ፤ ሐዘን፤ የመፅናናት ምኞቱ መሐል ብቅ፤ ጥልቅ፤ የሚለዉ ጥያቄ ግን እስካሁን ትክክለኛ መልስ አላገኘም። በዚሕ ዘመን፤ ባንዴ፤ ያን ያሕል ሕዝብ እንዴት አለቀ? የአይን ምሥክሩም አልገባቸዉም።

«ምንም ሊገባኝ አይችልም። እንዲሕ አይነት አደጋ የሚደርስበት ምንም ምክንያት ሊኖር አይገባም። ባካባቢዉ ሰዉ የሚያድሩባቸዉ ድንኳኖች ናቸዉ ያሉት። (ጀመራት) ድልድይንም መጓዝ ያለባቸዉ ባንድ አቅጣጫ ነዉ።ባንድ አቅጣጫ ነዉ የሚዞሩት፤ ወደ ኋላ መመለስ፤ መቆምም አይችሉም።» ሌሎች እንዲሕ ይተርካሉ ድንኳች የተተከሉባቸዉ ጎዳና ቁጥር 204 እና ጎዳና ቁጥር 223-ጀምራት ድልድይ አጠገብ ይገናኛሉ።

እንደ ትናንቱ ባይሆን ኖሮ፤ ምዕመናን ድልድዩ ላይ ሆነዉ ሰይጣንን ለመደብደብ ተምሳሌት ጠጠር ይጥሉበታል። ትናንት ግን ከቁጥር 204 ጎዳና የተነሳዉ የሕዝብ ማዕበል እና ከቁጥር 223 የሚተመዉ ሌላ ማዕበል ሁለቱ ጎዳኖች እሚገጥሙበት ሥፍራ-ሲደርሱ ይላታማሉ።ከዚያ–ትርምስ፤ ግጭት፤ ጩኸት—እና እልቂት።

በሕዝብ መጨናነቅ፤ መገፋፋት፤ መረጋጋጥ፤ በቃጠሎ፤ ሌላ ቀርቶ በግንባታ ክሬን መዉደቅ -በዚያ ቅዱስ ሥፍራ፤ ሰዉ ሲሞት ሲቆስል ያሁኑ በርግጥ የመጀመሪያዉ አይደለም። ሰኔ 1982 በደረሰ አደጋ 1426 ሐጃጆች ካለቁ ወዲሕ በርካታ ሰዉ ሲሞት ግን የትናንቱ የመጀመሪያዉ ነዉ።717 ሰዉ—-ለዚያራ በተከናነባት ጨርቅ እንደ ምሳሌዉ ተከፈነባት። 8 መቶ ቆሠለ።

የዛሬ ዘጠኝ ዓመት ግድም 364 ሰዉ በተመሳሳይ አደጋ ከሞተ ወዲሕ የሁለቱ ቅዱስ ሥፍራዎች የበላይ ጠባቂ የሚባሉት የሳዑዲ አረቢያ ነገስታት በተለይ መጨናነቁን ለማስተንፈስ፤ ተጨማሪ ድልድዮች፤ መንገዶችና መሿለኪያዎች ማስራታቸዉን፤ የኮሚፒዉተር መቆጣጠሪዎች ማስተከላቸዉን፤ በርካታ የአደጋ ተከላካይ ሠራተኞች ማስማራታቸዉን በየዓመቱ ይናገራሉ። ትናት የሆነዉ-ለምን ሆነ ታዲያ?

ንጉስ ሳልማን ይጣራል ነዉ መልሳቸዉ። «አሳዛኝ አደጋ ነው። የሚመለከታቸው አካላት ጉዳዩን በተቻለ ፍጥነት አጣርተዉ ውጤቱን እንዲያሳውቁን አዘናል። የምዕመናን ደህነነት ለማስጠበቅ የተቻለንን ሁሉ እናደርጋለን ።» የንጉሱ የጤና ሚንስትር ግን «የጉዞዉን ደንብና ሥርዓት ያላከበሩ ምዕመናን የፈጠሩት ትርምስ» የሚል መልስ ሰጥተዋል። በየዓመቱ ሁለት ሚሊዮን ሕዝብ የሚያስተናግድ መንግሥት ጥንቃቄ፤ ምክር፤ ዝግጅቱ እልቂት አለማስቀረቱ ብዙዎችን ማሳዘኑ አልበቃ ያለ ይመስል፤ ባለሥልጣናቱ በምዕመኑ ማሳበባቸዉ ማስተዛዘቡ አልቀረም። የኢራን መሪዎች ከመታዘብም አልፈዉ የሪያድ ነገስታት የመካና መዲና «የበላይ ጠባቂ ነን» እንደሚሉት ሁሉ ለአደጋዉም በበላይ ሐላፊነት መጠየቅ አለባቸዉ ባዮች ናቸዉ።

ታዛቢዉ ደግሞ፤ «በቂ ፀጥታ አስከባሪ ወይም ሥርዓት አሲያዥ ቢኖር ኖሮ፤ ሕይወት አድን ሠራተኞች ፈጥነዉ ቢደርሱ፤ ከሁሉም በላይ ተጨማሪ ማስፋፋት ቢደረግ ኖሮ-ያ ሁሉ ሕዝብ ባላለቀ ነበር» ይላሉ።«ሚና ተጨማሪ የማስፋፊያ ግንባታ ያስፈልገዋል። መንገዶቹ መስፋፋት፤ ድንኳኖቹም ተራርቀዉ የሚተከሉበት ሥልት ሊኖር ይገባ ነበር። (ከእንግዲሕም) የሆነ የምሕንድስና ሥራ-መሠራት አለበት።» የሟቾቹ ዜግነትና ብዛት ቀስበቀስ ይፋ እየሆነ ነዉ።

እስካሁን የመጀመሪያዉን ሥፍራ የያዙት ኢራኖች ናቸዉ። 131 ሞሮኮ 87 ሕንድ 14። ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ እንዳለዉ ኢትዮጵያዉያንም ሞተዋል። ቁጥራቸዉ ግን ገና በይፋ አልተነገረም።

(Deutsche Welle: ነጋሽ መሐመድና አርያም ተክሌ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am
  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule