• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሐጃጆች ሞት

September 25, 2015 12:06 am by Editor Leave a Comment

ለሐጅ ጉብኝት የተጓዙ በብዙ መቶ የሚቆጠሩ ምዕመናን ትናንት ሚና-ሳዑዲ አረቢያ ዉስጥ ድንገት በመሞታቸዉ የሐገራት መሪዎችና የድርጅት ተጠሪዎች የሚያስተላልፉት የሐዘን መግለጫ፤ የሐይማኖት መሪዎች ፀሎት ዛሬም እንደቀጠለ ነዉ። በአደጋዉ 717 ሰዎች ሞተዋል፤ ከ800 በላይ ቆስለዋል። የሳዑዲ አረቢያ ገዢዎች የአደጋዉ ትክክለኛ መንሥኤ እንዲጣራ አዘዋል።ኢራን ግን ለአደጋዉ የሪያድ ነገሥታት ሐላፊነቱን እንዲወስዱ አሳስባለች።በሐጂ ጉብኝት ወቅት ተደጋጋሚ አደጋዎች ቢደርሱም በርካታ ሠዉ የሞተበት አደጋ ሲደርስ በሃያ-አምስት ዓመት ዉስጥ የትናንቱ የመጀመሪያዉ ነዉ።

ከመካዉ ዓል-ሐራም እስከ ሞስኮዉ ካቴድራል፤ ከምሥራቅ ለንደኑ እስከ ካይሮዉ አል-አዝሐር፤ ከካምፓላዉ ቃዛፊ፤ እስከ እየሩሳሌሙ ዓል-አቅሳ፤ ከዓለም መሳጂዶች የሚንቆረቆረዉ ዱዓ፤ምልጃ ዛሬም እንደቀጠለ ነዉ።ከዋይት ሐዉስ እስከ ክሬምሊን ያሉ አብያተ-መንግሥታትም የሐዘን መግለጫዉን እያጎረፉት ነዉ።የሐገራት፤የድርጅቶችና የሐይማኖት መሪዎችም እንዲሁ።

በዱዓ፤ ሐዘን፤ የመፅናናት ምኞቱ መሐል ብቅ፤ ጥልቅ፤ የሚለዉ ጥያቄ ግን እስካሁን ትክክለኛ መልስ አላገኘም። በዚሕ ዘመን፤ ባንዴ፤ ያን ያሕል ሕዝብ እንዴት አለቀ? የአይን ምሥክሩም አልገባቸዉም።

«ምንም ሊገባኝ አይችልም። እንዲሕ አይነት አደጋ የሚደርስበት ምንም ምክንያት ሊኖር አይገባም። ባካባቢዉ ሰዉ የሚያድሩባቸዉ ድንኳኖች ናቸዉ ያሉት። (ጀመራት) ድልድይንም መጓዝ ያለባቸዉ ባንድ አቅጣጫ ነዉ።ባንድ አቅጣጫ ነዉ የሚዞሩት፤ ወደ ኋላ መመለስ፤ መቆምም አይችሉም።» ሌሎች እንዲሕ ይተርካሉ ድንኳች የተተከሉባቸዉ ጎዳና ቁጥር 204 እና ጎዳና ቁጥር 223-ጀምራት ድልድይ አጠገብ ይገናኛሉ።

እንደ ትናንቱ ባይሆን ኖሮ፤ ምዕመናን ድልድዩ ላይ ሆነዉ ሰይጣንን ለመደብደብ ተምሳሌት ጠጠር ይጥሉበታል። ትናንት ግን ከቁጥር 204 ጎዳና የተነሳዉ የሕዝብ ማዕበል እና ከቁጥር 223 የሚተመዉ ሌላ ማዕበል ሁለቱ ጎዳኖች እሚገጥሙበት ሥፍራ-ሲደርሱ ይላታማሉ።ከዚያ–ትርምስ፤ ግጭት፤ ጩኸት—እና እልቂት።

በሕዝብ መጨናነቅ፤ መገፋፋት፤ መረጋጋጥ፤ በቃጠሎ፤ ሌላ ቀርቶ በግንባታ ክሬን መዉደቅ -በዚያ ቅዱስ ሥፍራ፤ ሰዉ ሲሞት ሲቆስል ያሁኑ በርግጥ የመጀመሪያዉ አይደለም። ሰኔ 1982 በደረሰ አደጋ 1426 ሐጃጆች ካለቁ ወዲሕ በርካታ ሰዉ ሲሞት ግን የትናንቱ የመጀመሪያዉ ነዉ።717 ሰዉ—-ለዚያራ በተከናነባት ጨርቅ እንደ ምሳሌዉ ተከፈነባት። 8 መቶ ቆሠለ።

የዛሬ ዘጠኝ ዓመት ግድም 364 ሰዉ በተመሳሳይ አደጋ ከሞተ ወዲሕ የሁለቱ ቅዱስ ሥፍራዎች የበላይ ጠባቂ የሚባሉት የሳዑዲ አረቢያ ነገስታት በተለይ መጨናነቁን ለማስተንፈስ፤ ተጨማሪ ድልድዮች፤ መንገዶችና መሿለኪያዎች ማስራታቸዉን፤ የኮሚፒዉተር መቆጣጠሪዎች ማስተከላቸዉን፤ በርካታ የአደጋ ተከላካይ ሠራተኞች ማስማራታቸዉን በየዓመቱ ይናገራሉ። ትናት የሆነዉ-ለምን ሆነ ታዲያ?

ንጉስ ሳልማን ይጣራል ነዉ መልሳቸዉ። «አሳዛኝ አደጋ ነው። የሚመለከታቸው አካላት ጉዳዩን በተቻለ ፍጥነት አጣርተዉ ውጤቱን እንዲያሳውቁን አዘናል። የምዕመናን ደህነነት ለማስጠበቅ የተቻለንን ሁሉ እናደርጋለን ።» የንጉሱ የጤና ሚንስትር ግን «የጉዞዉን ደንብና ሥርዓት ያላከበሩ ምዕመናን የፈጠሩት ትርምስ» የሚል መልስ ሰጥተዋል። በየዓመቱ ሁለት ሚሊዮን ሕዝብ የሚያስተናግድ መንግሥት ጥንቃቄ፤ ምክር፤ ዝግጅቱ እልቂት አለማስቀረቱ ብዙዎችን ማሳዘኑ አልበቃ ያለ ይመስል፤ ባለሥልጣናቱ በምዕመኑ ማሳበባቸዉ ማስተዛዘቡ አልቀረም። የኢራን መሪዎች ከመታዘብም አልፈዉ የሪያድ ነገስታት የመካና መዲና «የበላይ ጠባቂ ነን» እንደሚሉት ሁሉ ለአደጋዉም በበላይ ሐላፊነት መጠየቅ አለባቸዉ ባዮች ናቸዉ።

ታዛቢዉ ደግሞ፤ «በቂ ፀጥታ አስከባሪ ወይም ሥርዓት አሲያዥ ቢኖር ኖሮ፤ ሕይወት አድን ሠራተኞች ፈጥነዉ ቢደርሱ፤ ከሁሉም በላይ ተጨማሪ ማስፋፋት ቢደረግ ኖሮ-ያ ሁሉ ሕዝብ ባላለቀ ነበር» ይላሉ።«ሚና ተጨማሪ የማስፋፊያ ግንባታ ያስፈልገዋል። መንገዶቹ መስፋፋት፤ ድንኳኖቹም ተራርቀዉ የሚተከሉበት ሥልት ሊኖር ይገባ ነበር። (ከእንግዲሕም) የሆነ የምሕንድስና ሥራ-መሠራት አለበት።» የሟቾቹ ዜግነትና ብዛት ቀስበቀስ ይፋ እየሆነ ነዉ።

እስካሁን የመጀመሪያዉን ሥፍራ የያዙት ኢራኖች ናቸዉ። 131 ሞሮኮ 87 ሕንድ 14። ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ እንዳለዉ ኢትዮጵያዉያንም ሞተዋል። ቁጥራቸዉ ግን ገና በይፋ አልተነገረም።

(Deutsche Welle: ነጋሽ መሐመድና አርያም ተክሌ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am
  • የኦነግ ሸኔ አባላትን ዕድሜ ለማሳጠር የጂፒኤስ ቴክኖሎጂ ጥቅም ላይ እየዋለ ነው December 7, 2020 12:38 am
  • የቆሰሉ ወታደሮች በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጎበኙ December 6, 2020 11:41 pm
  • “ከዚህ በኋላ ይዘን እንታገላለን እንጂ ሠጥተን አንጠይቅም” ኮሎኔል ደመቀ December 2, 2020 12:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule