• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

48 ሰዓት ሳይሞላ በአቶ ዳውድ የሚመራው “ኅብረት” ወደ ዘጠኝ ወረደ

December 8, 2019 02:19 am by Editor 1 Comment

አርብ ዕለት በአቶ ዳውድ ኢብሣ የሚመራ “የአስር ድርጅቶች” ኅብረት ፈጸሙ መባሉ ብዙም ሳይቆይ ስምምነቱን ከፈረሙት መካከል አንዱ ነው የተባለለት የአገው አገር አቀፍ ሸንጎ በስምምነቱ ላይ እንደሌለበት አስታውቋል።

ሸንጎው ባወጣው መረጃ መሠረት ሸንጎው ውኅደት ማድረጉን አስመልክቶ ደጋፊዎቻቸው ጥያቄ ያቀረቡ መሆኑን በመጥቀስ የሰጠው ምላሽ “በዚህ ዙሪያ ከብሔራዊ ሥራ አስፈጻሚ ጀምሮ እስከ ዞንና ወረዳ ውይይት” ያልተደረገበት መሆኑን በመጥቀስ በኅብረት ስምምነቱ ላይሸንጎው እንዳልተገኘ ገልጾዋል።

በተመሳሳይ ዜና ህወሓት “የፌዴራሊስት” ጉባዔ በማለት በመቀሌ ጠርቶት በነበረ ስብሰባ ላይ ከደብረጽዮን በስተቀኝ አንድ ወንበር ቀጥሎ ተቀምጦ የሚታየው በፊት ለፊቱ “የአገው ተወካይ” የሚል ቢሆንም ስብሰባው ከመጀመሩ በፊት የአገው ማኅበረሰብ ተሰብስቦ ተወካይ እንደማይልክ መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል።   

በዚሁ የመቀሌ ስብሰባ ላይ “ኦነግን ወክዬ ነው የመጣሁት” ያለውን ግለሰብ የአውራምባ ታይምስ ባለቤት ዳዊት ከበደ ቃለመጠይቅ ካደረገለት በኋላ በእርግጥ የኦነግ ተወካይ መሆኑን ለማጣራት ወደ ኦነግ ደውሎ ያገኘውን ተስፋ የሚያስቆርጥ ምላሽ በትግሪኛ በፌስቡክ ገጹ ላይ እንዲህ ብሎ ማስፈሩ ዘግበን እንደነበር ይታወሳል፤

የትግሪኛው ትርጉም እንዲህ ይላል፤ “ኦነግን ወክየ ነው የመጣሁት ያለኝ ኣንድ ወጣት ፖለቲከኛን ቃለመጠይቅ ኣድርጌ ነበር፤ ሆኖም ግን ቪድዮውን ከማስተላለፌ በፊት የተላከው ወኪል በትክክል የኦነግ ወኪል መሆኑን ለማረጋገጥ ወደ ኦነግ ጽህፈትቤት ደውዬ ያገኘሁት መልስ በጣም የሚያሳዝን ሆኖ ኣገኘሁት። እንደዚህ የሚባል ስም በአመራር ደረጃም ይሁን በኣባል ደረጃ የለንም፣ በመሠረቱ ወደ መቀለ ስብሰባ አንዲሳተፍ የላክነው ወኪል የለንም ብለው ኣሳፈሩኝ፤ ህውከት፣ ድካም ብቻ ነው ያተረፍኩት። በሉ ኣበሉን ስጡትና ላኩት”።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: 10 parties, Left Column, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. ዘለቀ says

    December 9, 2019 05:39 am at 5:39 am

    በቲፒልፈም ሆነ በኦነግ የተሰባሰበው ስብስብ የሸ ፍጥ የቂም በቀልና ተንኮል አዘል በመሆኑ እንደ ባቢሎን ግንብ በጧቱ መደርመስ መጀመሩ ለኢትዮጵያ ህዝብ ትልቅ ተሰፋ ነው፡፡ በ እውነትና በእወቀት ላይ የተመሰረቱ ፓርቲዎች ሊበረታቱ ሊጎለምሱ ይገባል እንጂ ሽፈጥ አዘል ፓርቲዎች በአይነ ቁራኛ ሊታዩ ይገባል፡፡ ምክንያቱም አለመረጋጋትን የህዝብ መፈናቀልን የ እርስበ እርስ ጦርነትን በመጨረሻም ርሃብን ስደትን ማስከተላቸው ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule