• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

48 ሰዓት ሳይሞላ በአቶ ዳውድ የሚመራው “ኅብረት” ወደ ዘጠኝ ወረደ

December 8, 2019 02:19 am by Editor 1 Comment

አርብ ዕለት በአቶ ዳውድ ኢብሣ የሚመራ “የአስር ድርጅቶች” ኅብረት ፈጸሙ መባሉ ብዙም ሳይቆይ ስምምነቱን ከፈረሙት መካከል አንዱ ነው የተባለለት የአገው አገር አቀፍ ሸንጎ በስምምነቱ ላይ እንደሌለበት አስታውቋል።

ሸንጎው ባወጣው መረጃ መሠረት ሸንጎው ውኅደት ማድረጉን አስመልክቶ ደጋፊዎቻቸው ጥያቄ ያቀረቡ መሆኑን በመጥቀስ የሰጠው ምላሽ “በዚህ ዙሪያ ከብሔራዊ ሥራ አስፈጻሚ ጀምሮ እስከ ዞንና ወረዳ ውይይት” ያልተደረገበት መሆኑን በመጥቀስ በኅብረት ስምምነቱ ላይሸንጎው እንዳልተገኘ ገልጾዋል።

በተመሳሳይ ዜና ህወሓት “የፌዴራሊስት” ጉባዔ በማለት በመቀሌ ጠርቶት በነበረ ስብሰባ ላይ ከደብረጽዮን በስተቀኝ አንድ ወንበር ቀጥሎ ተቀምጦ የሚታየው በፊት ለፊቱ “የአገው ተወካይ” የሚል ቢሆንም ስብሰባው ከመጀመሩ በፊት የአገው ማኅበረሰብ ተሰብስቦ ተወካይ እንደማይልክ መግለጫ ማውጣቱ ይታወሳል።   

በዚሁ የመቀሌ ስብሰባ ላይ “ኦነግን ወክዬ ነው የመጣሁት” ያለውን ግለሰብ የአውራምባ ታይምስ ባለቤት ዳዊት ከበደ ቃለመጠይቅ ካደረገለት በኋላ በእርግጥ የኦነግ ተወካይ መሆኑን ለማጣራት ወደ ኦነግ ደውሎ ያገኘውን ተስፋ የሚያስቆርጥ ምላሽ በትግሪኛ በፌስቡክ ገጹ ላይ እንዲህ ብሎ ማስፈሩ ዘግበን እንደነበር ይታወሳል፤

የትግሪኛው ትርጉም እንዲህ ይላል፤ “ኦነግን ወክየ ነው የመጣሁት ያለኝ ኣንድ ወጣት ፖለቲከኛን ቃለመጠይቅ ኣድርጌ ነበር፤ ሆኖም ግን ቪድዮውን ከማስተላለፌ በፊት የተላከው ወኪል በትክክል የኦነግ ወኪል መሆኑን ለማረጋገጥ ወደ ኦነግ ጽህፈትቤት ደውዬ ያገኘሁት መልስ በጣም የሚያሳዝን ሆኖ ኣገኘሁት። እንደዚህ የሚባል ስም በአመራር ደረጃም ይሁን በኣባል ደረጃ የለንም፣ በመሠረቱ ወደ መቀለ ስብሰባ አንዲሳተፍ የላክነው ወኪል የለንም ብለው ኣሳፈሩኝ፤ ህውከት፣ ድካም ብቻ ነው ያተረፍኩት። በሉ ኣበሉን ስጡትና ላኩት”።

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: 10 parties, Left Column, tplf

Reader Interactions

Comments

  1. ዘለቀ says

    December 9, 2019 05:39 am at 5:39 am

    በቲፒልፈም ሆነ በኦነግ የተሰባሰበው ስብስብ የሸ ፍጥ የቂም በቀልና ተንኮል አዘል በመሆኑ እንደ ባቢሎን ግንብ በጧቱ መደርመስ መጀመሩ ለኢትዮጵያ ህዝብ ትልቅ ተሰፋ ነው፡፡ በ እውነትና በእወቀት ላይ የተመሰረቱ ፓርቲዎች ሊበረታቱ ሊጎለምሱ ይገባል እንጂ ሽፈጥ አዘል ፓርቲዎች በአይነ ቁራኛ ሊታዩ ይገባል፡፡ ምክንያቱም አለመረጋጋትን የህዝብ መፈናቀልን የ እርስበ እርስ ጦርነትን በመጨረሻም ርሃብን ስደትን ማስከተላቸው ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “የገቡበት ገብተን አንድ ሰው አናስቀርም – በተለይ አመራሩን” ጄኔራል ብርሃኑ ጁላ February 15, 2021 11:46 pm
  • የትግራይ ገበሬና የከተማ ነዋሪ በሠራዊታችን ላይ አንድ ጥይት አልተኮሰም – ሪር አድሚራል ክንዱ February 4, 2021 01:51 pm
  • ኢንተርፖል፤ የህወሃት ሳምሪዎች የማይካድራ ጭፍጭፋ ከቦኮሃራም የከፋ ነው February 4, 2021 11:10 am
  • ጄኔራሎች “ተገድለዋል” በሚል የሀሰት መረጃ ሲያሰራጭ የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ February 4, 2021 08:48 am
  • በትግራይ ክልል በሴቶች ላይ ተፈጸመ የተባለውን ጥቃት የሚያጣራ ግብረ ኃይል መቀሌ ገባ February 3, 2021 12:06 pm
  • ፓርቲዎች የምርጫ መወዳደሪያ ምልክቶቻቸውን ወሰዱ February 3, 2021 10:29 am
  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule