• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው?

March 9, 2020 10:18 am by Editor 5 Comments

በቡራዩ ብር የማይሰጥ አገልግሎት አያገኝም

በአዲስ አበባ ዙሪያና ውስጥ የባዶ መሬትና የኮንዶሚኒየም ቤቶች ገበያ ደርቷል። በርካቶች እንደሚሉት ይህ የደራ ገበያ ምሥጢር ባለመሆኑ ከከንቲባ ታከለ ኡማ አስተዳደር የተሰወረ አይደለም። ምን አልባትም የአዲስ አበባ መሬትና የኮንዶሚኒየም ቤቶች የጠራራ ጸሃይ ገበያና የባለቀንነት ሽሚያ፣ በማኅበራዊ ጉዳዮች ባላቸው ተሳትፎ ሰፊ ተቀባይነት ላላቸው ታከለ ኡማ ጉዞ ጋሬጣ እንዳይሆንባቸው የሚፈሩም አሉ። በተመሳሳይ በቡራዩ ነዋሪዎች ከመሬት ጋር በተያያዘ ሰፊ ቅሬታ ያሰማሉ። በቡራዩ ብር የማይጠበቅበት አገልግሎት እንደሌለም አመልክተዋል።

የአየር ጤና ነዋሪ መሆናቸውን የገለጹ ለጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ እንዳስታወቁት ለውጡን ተከትሎ በርካታ ቦታዎች ታጥረውና ሳይታጠሩ ባለቤት አልባ ሆነዋል። እንደ እነሱ ገለጻ ባለቤቶቻቸው ጠፍተዋል፣ ተሸሽገዋል፣ ወይም በፍርሃቻ ቀን እየጠበቁ ነው፤ አለያም ህጋዊ ሰነድ ያልነበራቸው ነበሩ።

በዚሁ መነሻ ማንነታቸው የማይታወቁ ሰዎች ባለቤት አልባ የሆኑትን ቦታዎች እያጠሩ፣ የታጠረም ከሆነ እየወረሱ ከክፍለከተማ አመራሮች ጋር በመመሳጠር የግል እያደረጓቸው ነው። በዚህ አግባብ በርካታ እንግዳ የሆኑ አዳዲስ ሰዎችና ደላሎች ተደራራቢ መሬት እየወሰዱ መሆናቸውን ነው ነዋሪዎቹ የሚናገሩት።

የባዶ መሬት ንግድና ወረራ በሚገርም ደረጃ መጧጧፉን የሚገልጹት ነዋሪዎች ድርጊቱ የቡድን መልክ እንዳለውም ጠቁመዋል። የቀደሙት ጥለው ሲሄዱ የአሁኖቹ እየተረከቡ ነው። ለመቆጣጠርና ለማስቆም የሚሞክር አካልም አይታየም። እንደ ጥቆማ ሰጪዎቹ ከሆነ የመሬት መቀራመቱና ንግዱ የሚከናወነው በአደባባይ ነው።

ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የአዲስ አበባ አስተዳደር የመካከለኛ እርከን ሠራተኛ “ዓለም ባንክ፣ አየር ጤና፣ ቤቴልና ዙሪያውን እንዲሁም ወደ ቃሊቲ መሬት የመቀራመት ጉዳይ አለ። ይታወቃል። ችግሩ ሥራው የሚሠራው በቡድን መሆኑ ነው። አስተዳደሩ ቁርጥ አቋም ሊወስድ ይገባል” ሲሉ የውሳኔ ሰጪው አካል ድክመት እንዳለ አስታውቀዋል።

በተመሳሳይ 40/60 መርሃ ግብር ገንዘብ ቆጥበው የኮንዶሚኒየም ቤት የደረሳቸውና በመጠባበቅ ላይ ያሉ ምሬት እያሰሙ ነው። እኒህ ዜጎች ከዕለት ጉሮሮ ቀንሰው በቆጠቡት ገንዘብ የተገነባን ቤት ኃላፊነት የጎደላቸው ወገኖች አላግባብ በመመሪያ እያከፋፈሉት መሆኑንን ይናገራሉ። “ለማን አቤት እንበል?” የሚሉት ወገኖች ደላሎች የአሳዛኙ ድራማ ዋና ተዋንያን መሆናቸውን አስታውቀዋል።

የጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ እንደሰማው ዕጣ እንዳይወጣባቸው የተደረጉት የኮንዶሚኒየም ቤቶች ምንም እንኳን ለሽግግሩ ወቅት ለሚመደቡ ኃላፊዎች እንደ መጠባበቂያ ማስቀመጡ አግባብ ቢሆንም አሁን እየታየ ያለው ተግባር ግን አሳፋሪ ሆኖባቸዋል።

“በመመሪያ፣ በደብዳቤና በቃል ይታዘዛል” የሚሉት እነዚህ ክፍሎች “ጉዳዩን የሚያስፈጽሙት ደላሎች ናቸው። ካስፈጸሙና የቤቱ ዝውውር ካለቀ በኋላ አየር በአየር የሚያገበያዩትም እነሱው ናቸው። ይህ ዓይነቱ ንግድ በግልጽ የሚታይ ሆኖ ሳለ እርምጃ የሚወስድና የሚያስተካክል አካል መጥፋቱ ደግሞ ከሁሉም ጉዳዩን አሳዛኝ ያደርገዋል” ሲሉ ጥቆማ ሰጪዎች ያስረዳሉ።

ይህንኑ ከሚያስፈጽሙት መካከል አንዳንድ የክፍለ ከተማ አመራሮች በዚሁ በትዕዛዝ በሚከናወን የቤት ሽሚያ መሰላቸታቸውን ተመዝግበው፣ ገንዘብ ቆጥበው፣ ወረፋ ጠብቀው፣ ዕጣ ደርሷቸው እየተንከራተቱ ያሉ ለአቤቱታ ቢሯቸው በሄዱበት ወቅት እንደገለጹላቸው አስረድተዋል።

ዕጣ ከወጣላቸው በኋላ ቤታቸውን እንዳይረከቡ የተደረጉት ዜጎች ጉዳይ ምንም እልባት ሳያገኝ መቆየቱ ብቻ ሳይሆን ከስር ከስር ቤቶቹ ለሌላ አካል እየተዘዋወሩ መሆኑ ከሕግም ሆነ ከሞራል አንጻር የኢንጂነር ታከለ ኡማን አመራር እያደር ተጠያቂ ማድረጉ እንደማይቀር የደራውን ንግድ የሚከታተሉ እየገለጹ ነው።  በድሆች ላይ እየተከናወነ ያለውን ዘረፋ እያዩ ዝም ማለት ለታከለ ኡማም ሆነ በዙሪያቸው ላሉ ደላሎች ስለማይጠቅም ከዛ በፊት ነገሮችን ቢያጸዱ እንደሚሻልም እነዚሁ ክፍሎች መክረዋል።

በአዲስ አበባ መሬት መቀራመትና በውድ ዋጋ ማስተላለፍን በተመለከት አፍ ውስጥ የገቡ ኃላፊዎች ጉዳይ ምርመራ እየተደረገበት እንደሆነ፣ አንዳንዶችም በአካል ተጠርተው ቢመከሩም ሊሰሙ አለመቻላቸው የጎልጉል የመረጃ ሰዎች ተናግረዋል።

በሹመት ወደ አዲስ አበባ መምጣቷን የምትገልጽ አንዲት ሴት፣ የተሰጣትን የኮንዶሚኒየም ቤት ሸጣለች። ሽያጩን ያከናወኑትና የፈጸሙት ደላሎች ናቸው። ሽያጩ ከተጠናቀቀ በኋላ “አሁን ቤት ሸጠሽ የት ትኖሪያለሽ?” በሚል ስትጠየቅ “ሌላ እወስዳለሁ። እንደገና እወስዳለሁ” ማለቷን ምስክሮች ለጎልጉል አመልክተዋል።

አርቲስቶች፣ ጋዜጠኞች፣ ከክልል የሚመጡ ባለሥልጣናት የኮንዶሚኒየም ቤቶችን እንዲወስዱ መመሪያ የሚሰጥ ሲሆን፣ መመሪያ ሰጪዎቹ አብረው አየር በአየር ደላሎቹ በሚያቀርቡት መሠረት የቤት ዕደላውና የአየር በአየር ንግዱ ፈር የለቀቀበት ደረጃ ደርሷል። የቁጠባ ደብተር ይዘው፣ ከገቢያቸው ቆጥበውና ዕጣ ደርሷቸው የሚጠብቁ ወገኖች ወደኋላ ተብለው ደላሎች ቤታቸውን እንዲቸበችቡት እየተደረገ ነው።

መረጃ አቅራቢዎቹ የደላሎቹን ስምና እስከ አዲስ አበባ አስተዳደር ከንቲባ ቢሮ ድረስ እጃቸው ረዥም የሆኑትን ወገኖች በስም፣ በሰፈርና በግንኙነት ደረጃ ለይተው ለጎልጉል አስታውቀዋል። ከፍተኛ የሚባሉት የአስተዳደሩ ሰው የሸጡትን ስፍራም ለይተው አስታውቀዋል። ይሁን እንጂ ጎልጉል ለጊዜው ከማተም ተቆጥቧል። በተለይም ከከንቲባው ቢሮ ጋር ትሥሥር ፈጥረው እየሠሩ ያሉትን ደላሎች በተመለከተ ጎልጉል በቂ መረጃ የሰበሰበ ሲሆን እንደ አስፈላጊነቱ ይፋ ያደርጋል። ይህ አዲስ አበባን ሊደፋ የተነሳው የደላላ ኃይል ላይ ክትትልና መረጃ ተሰብስቦ መጠናቀቁን ጎልጉል ስለሚያውቅ የመንግሥትን የክትትል ሥራ ላለማበላሸት ነው ማንነትን ጠቅሰን ለማተም ያለውደድነው። ይሁን እንጂ አዲስ አበባ ላይ ተራ ጮሌነት የትም እንደማያደርስ ጎልጉል ለማስታወቅ ይወዳል።

በተመሳሳይ ዜና በቡራዩ ከመሬት ጋር በተያያዘ ካርታ ለማውጣት፣ ለማደስና የይዞታ ማረጋገጫ ለመውሰድ በግልጽ ገንዘብ የሚጠየቅ መሆኑንን ነዋሪዎች ለጎልጉል አስታውቀዋል። ነዋሪዎች እንደሚሉት ብር የማይሰጥ አገልግሎት አያገኝም። ገንዘብ የሚጠየቀውም በግልጽ በአደባባይ ነው።

ለየአገልግሎት ዓይነቱ የተቀመጠ የገንዘብ መጠን መኖሩን የሚናገሩት ወገኖች፣ መንግሥትንና ሕዝብን የሚያቃቅሩት እንዲህ ያሉ ዜጎች በመሆናቸው የኦሮሚያ ክልል ቢያስብበት ሲሉ ጥቆማቸውን አቅርበዋል። የኦሮሚያ ክልል የበታች መዋቅሩን ባስቸኳይ ማስተካከል እንዳለበት በተደጋጋሚ አስተያየት ይሰጣል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Filed Under: Middle Column, News, Social Tagged With: addis condo, Full Width Top, Middle Column, takele uma

Reader Interactions

Comments

  1. golgul-aba-gora says

    March 9, 2020 07:24 pm at 7:24 pm

    እንዲህ ስትሉ ምን ማለታችሁ ይሆን?

    “ከፍተኛ የሚባሉት የአስተዳደሩ ሰው የሸጡትን ስፍራም ለይተው አስታውቀዋል። ይሁን እንጂ ጎልጉል ለጊዜው ከማተም ተቆጥቧል። በተለይም ከከንቲባው ቢሮ ጋር ትሥሥር ፈጥረው እየሠሩ ያሉትን ደላሎች በተመለከተ ጎልጉል በቂ መረጃ የሰበሰበ ሲሆን እንደ አስፈላጊነቱ ይፋ ያደርጋ”

    ለመሆኑ ጊዜ ካለፈ በኋላ “ይፋ” ልታወጡት ነው መረጃውን ወይስ “በመረጃው” ጥራትና አስተማማኝነት አላመናችሁበትም? ወይስ “መረጃው” በማስረጃ ያልተደገፈ ነው? በትኖሩበት የምዕራብ አገራት ምን እንደሚደረግ የምታውቁ ናችሁ፤ እንዲህ ዓይነት በማስረጃ የተደገፈ “መረጃ” ልፖሊስ/አቃቤ ሕግ/ ፓርላማ ወይም አግባብ ባለው ሚንስት/ባለሥልጣን/ኮሚሽን/ኤጀንሲ የኦዲትና ፖሊሲ አስፈፃሚ አክል ይተላለፋል፤ ታልሆነም የታክለ ዑማ ያለመመረጥ – ምርጫ ታለ ለዛውም – ዕድልን ማስፋቱ ይሆናል ያሳሰባችሁ፤ በደል ከሚደርስበት ዜጋ በላይ፤ ለነዚህ ዜጎች ስትሉ እባካችሁ “ይፋ” ባታደርጉትም የሰበሰባችሁትን “መረጃ” ለሚመለከተው ክፍል አስተላልፉ፤

    ደሞ እንዲህ ተባልን ብላችሁ አትበሳጩ መልዕቱን እንጂ መልዕከተኛው ተዉት – ተወዲህ ለማሳሰብ ያህል

    Reply
    • Editor says

      March 11, 2020 06:06 am at 6:06 am

      በጽሁፉ ውስጥ የተጠቀሰውን በትክክል ወይም በጽሞና ባለማንበብ የተሰጠ አስተያየት ነው፤ ዜናው ላይ ይህንን ብለናል፤

      ” . . . ይህ አዲስ አበባን ሊደፋ የተነሳው የደላላ ኃይል ላይ ክትትልና መረጃ ተሰብስቦ መጠናቀቁን ጎልጉል ስለሚያውቅ የመንግሥትን የክትትል ሥራ ላለማበላሸት ነው ማንነትን ጠቅሰን ለማተም ያለውደድነው። . . .”

      የጎልጉል አርታኢ

      Reply
  2. golgul-aba-gora says

    March 10, 2020 07:00 pm at 7:00 pm

    ለመጨመር ያህል፤ “መረጃ” ደርሶኛ ወይም ሰብስቤያለሁ ግን ይፋ አላደርገውም ማለት፤ አንድ – ወንጀል ሲሠራ አይቶ እንድማለፍ ያለ የዜግነትና ሕጋዊ ግዴታን አለመወጣት ነው፤ ሁለተኛ – ጠፋጥኞችን ተጠንቀቁ የሚል ደወል እንደ ማሰማት ነው፤ ማንኛውንም የገንዘብ ይዞታቸውን፤ የተጭበረበሩ ዶኪውመንቶቻቸውን፤ የግንኙነት መረባቸውን እንዲሰውሩ፤ ምናልባትም ራሳቸውን እንዲሰውሩ ማንቂያ ይሆናል፤ ትክክለኛው አሠራር የመረጃ ዶሴያችሁን ለፖሊስ ወይ ዐቃቤ ሕግ መጀመሪያ አቅርባችሁ ከሚከተለው ምርመራን ወይም የክሥ ሂደትን በማይጣረስ ብኩል ዜናው ማቅረብ ነው፤ ያንጊዜ መረጃ አለን ይፋ አናደርግም ሳይሆን መረጃውን ቀደም ብለን ለሚመለከተው ክፍል አስተላልፈናል ትሉና አንባቢም ያደንቅችሁአል፤

    Reply
    • Editor says

      March 11, 2020 06:05 am at 6:05 am

      በጽሁፉ ውስጥ የተጠቀሰውን በትክክል ወይም በጽሞና ባለማንበብ የተሰጠ አስተያየት ነው፤ ዜናው ላይ ይህንን ብለናል፤

      ” . . . ይህ አዲስ አበባን ሊደፋ የተነሳው የደላላ ኃይል ላይ ክትትልና መረጃ ተሰብስቦ መጠናቀቁን ጎልጉል ስለሚያውቅ የመንግሥትን የክትትል ሥራ ላለማበላሸት ነው ማንነትን ጠቅሰን ለማተም ያለውደድነው። . . .”

      የጎልጉል አርታኢ

      Reply
  3. wakeup says

    March 11, 2020 07:51 am at 7:51 am

    The following website is one
    of the most trustworthy
    alternative media world
    wide.Read it to know about
    the Covid and other deadly
    vaccines.
    http://www.globalresearch.ca/theme/science-and-medicine

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule