• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው?

March 9, 2020 10:18 am by Editor 5 Comments

በቡራዩ ብር የማይሰጥ አገልግሎት አያገኝም

በአዲስ አበባ ዙሪያና ውስጥ የባዶ መሬትና የኮንዶሚኒየም ቤቶች ገበያ ደርቷል። በርካቶች እንደሚሉት ይህ የደራ ገበያ ምሥጢር ባለመሆኑ ከከንቲባ ታከለ ኡማ አስተዳደር የተሰወረ አይደለም። ምን አልባትም የአዲስ አበባ መሬትና የኮንዶሚኒየም ቤቶች የጠራራ ጸሃይ ገበያና የባለቀንነት ሽሚያ፣ በማኅበራዊ ጉዳዮች ባላቸው ተሳትፎ ሰፊ ተቀባይነት ላላቸው ታከለ ኡማ ጉዞ ጋሬጣ እንዳይሆንባቸው የሚፈሩም አሉ። በተመሳሳይ በቡራዩ ነዋሪዎች ከመሬት ጋር በተያያዘ ሰፊ ቅሬታ ያሰማሉ። በቡራዩ ብር የማይጠበቅበት አገልግሎት እንደሌለም አመልክተዋል።

የአየር ጤና ነዋሪ መሆናቸውን የገለጹ ለጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ እንዳስታወቁት ለውጡን ተከትሎ በርካታ ቦታዎች ታጥረውና ሳይታጠሩ ባለቤት አልባ ሆነዋል። እንደ እነሱ ገለጻ ባለቤቶቻቸው ጠፍተዋል፣ ተሸሽገዋል፣ ወይም በፍርሃቻ ቀን እየጠበቁ ነው፤ አለያም ህጋዊ ሰነድ ያልነበራቸው ነበሩ።

በዚሁ መነሻ ማንነታቸው የማይታወቁ ሰዎች ባለቤት አልባ የሆኑትን ቦታዎች እያጠሩ፣ የታጠረም ከሆነ እየወረሱ ከክፍለከተማ አመራሮች ጋር በመመሳጠር የግል እያደረጓቸው ነው። በዚህ አግባብ በርካታ እንግዳ የሆኑ አዳዲስ ሰዎችና ደላሎች ተደራራቢ መሬት እየወሰዱ መሆናቸውን ነው ነዋሪዎቹ የሚናገሩት።

የባዶ መሬት ንግድና ወረራ በሚገርም ደረጃ መጧጧፉን የሚገልጹት ነዋሪዎች ድርጊቱ የቡድን መልክ እንዳለውም ጠቁመዋል። የቀደሙት ጥለው ሲሄዱ የአሁኖቹ እየተረከቡ ነው። ለመቆጣጠርና ለማስቆም የሚሞክር አካልም አይታየም። እንደ ጥቆማ ሰጪዎቹ ከሆነ የመሬት መቀራመቱና ንግዱ የሚከናወነው በአደባባይ ነው።

ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የአዲስ አበባ አስተዳደር የመካከለኛ እርከን ሠራተኛ “ዓለም ባንክ፣ አየር ጤና፣ ቤቴልና ዙሪያውን እንዲሁም ወደ ቃሊቲ መሬት የመቀራመት ጉዳይ አለ። ይታወቃል። ችግሩ ሥራው የሚሠራው በቡድን መሆኑ ነው። አስተዳደሩ ቁርጥ አቋም ሊወስድ ይገባል” ሲሉ የውሳኔ ሰጪው አካል ድክመት እንዳለ አስታውቀዋል።

በተመሳሳይ 40/60 መርሃ ግብር ገንዘብ ቆጥበው የኮንዶሚኒየም ቤት የደረሳቸውና በመጠባበቅ ላይ ያሉ ምሬት እያሰሙ ነው። እኒህ ዜጎች ከዕለት ጉሮሮ ቀንሰው በቆጠቡት ገንዘብ የተገነባን ቤት ኃላፊነት የጎደላቸው ወገኖች አላግባብ በመመሪያ እያከፋፈሉት መሆኑንን ይናገራሉ። “ለማን አቤት እንበል?” የሚሉት ወገኖች ደላሎች የአሳዛኙ ድራማ ዋና ተዋንያን መሆናቸውን አስታውቀዋል።

የጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ እንደሰማው ዕጣ እንዳይወጣባቸው የተደረጉት የኮንዶሚኒየም ቤቶች ምንም እንኳን ለሽግግሩ ወቅት ለሚመደቡ ኃላፊዎች እንደ መጠባበቂያ ማስቀመጡ አግባብ ቢሆንም አሁን እየታየ ያለው ተግባር ግን አሳፋሪ ሆኖባቸዋል።

“በመመሪያ፣ በደብዳቤና በቃል ይታዘዛል” የሚሉት እነዚህ ክፍሎች “ጉዳዩን የሚያስፈጽሙት ደላሎች ናቸው። ካስፈጸሙና የቤቱ ዝውውር ካለቀ በኋላ አየር በአየር የሚያገበያዩትም እነሱው ናቸው። ይህ ዓይነቱ ንግድ በግልጽ የሚታይ ሆኖ ሳለ እርምጃ የሚወስድና የሚያስተካክል አካል መጥፋቱ ደግሞ ከሁሉም ጉዳዩን አሳዛኝ ያደርገዋል” ሲሉ ጥቆማ ሰጪዎች ያስረዳሉ።

ይህንኑ ከሚያስፈጽሙት መካከል አንዳንድ የክፍለ ከተማ አመራሮች በዚሁ በትዕዛዝ በሚከናወን የቤት ሽሚያ መሰላቸታቸውን ተመዝግበው፣ ገንዘብ ቆጥበው፣ ወረፋ ጠብቀው፣ ዕጣ ደርሷቸው እየተንከራተቱ ያሉ ለአቤቱታ ቢሯቸው በሄዱበት ወቅት እንደገለጹላቸው አስረድተዋል።

ዕጣ ከወጣላቸው በኋላ ቤታቸውን እንዳይረከቡ የተደረጉት ዜጎች ጉዳይ ምንም እልባት ሳያገኝ መቆየቱ ብቻ ሳይሆን ከስር ከስር ቤቶቹ ለሌላ አካል እየተዘዋወሩ መሆኑ ከሕግም ሆነ ከሞራል አንጻር የኢንጂነር ታከለ ኡማን አመራር እያደር ተጠያቂ ማድረጉ እንደማይቀር የደራውን ንግድ የሚከታተሉ እየገለጹ ነው።  በድሆች ላይ እየተከናወነ ያለውን ዘረፋ እያዩ ዝም ማለት ለታከለ ኡማም ሆነ በዙሪያቸው ላሉ ደላሎች ስለማይጠቅም ከዛ በፊት ነገሮችን ቢያጸዱ እንደሚሻልም እነዚሁ ክፍሎች መክረዋል።

በአዲስ አበባ መሬት መቀራመትና በውድ ዋጋ ማስተላለፍን በተመለከት አፍ ውስጥ የገቡ ኃላፊዎች ጉዳይ ምርመራ እየተደረገበት እንደሆነ፣ አንዳንዶችም በአካል ተጠርተው ቢመከሩም ሊሰሙ አለመቻላቸው የጎልጉል የመረጃ ሰዎች ተናግረዋል።

በሹመት ወደ አዲስ አበባ መምጣቷን የምትገልጽ አንዲት ሴት፣ የተሰጣትን የኮንዶሚኒየም ቤት ሸጣለች። ሽያጩን ያከናወኑትና የፈጸሙት ደላሎች ናቸው። ሽያጩ ከተጠናቀቀ በኋላ “አሁን ቤት ሸጠሽ የት ትኖሪያለሽ?” በሚል ስትጠየቅ “ሌላ እወስዳለሁ። እንደገና እወስዳለሁ” ማለቷን ምስክሮች ለጎልጉል አመልክተዋል።

አርቲስቶች፣ ጋዜጠኞች፣ ከክልል የሚመጡ ባለሥልጣናት የኮንዶሚኒየም ቤቶችን እንዲወስዱ መመሪያ የሚሰጥ ሲሆን፣ መመሪያ ሰጪዎቹ አብረው አየር በአየር ደላሎቹ በሚያቀርቡት መሠረት የቤት ዕደላውና የአየር በአየር ንግዱ ፈር የለቀቀበት ደረጃ ደርሷል። የቁጠባ ደብተር ይዘው፣ ከገቢያቸው ቆጥበውና ዕጣ ደርሷቸው የሚጠብቁ ወገኖች ወደኋላ ተብለው ደላሎች ቤታቸውን እንዲቸበችቡት እየተደረገ ነው።

መረጃ አቅራቢዎቹ የደላሎቹን ስምና እስከ አዲስ አበባ አስተዳደር ከንቲባ ቢሮ ድረስ እጃቸው ረዥም የሆኑትን ወገኖች በስም፣ በሰፈርና በግንኙነት ደረጃ ለይተው ለጎልጉል አስታውቀዋል። ከፍተኛ የሚባሉት የአስተዳደሩ ሰው የሸጡትን ስፍራም ለይተው አስታውቀዋል። ይሁን እንጂ ጎልጉል ለጊዜው ከማተም ተቆጥቧል። በተለይም ከከንቲባው ቢሮ ጋር ትሥሥር ፈጥረው እየሠሩ ያሉትን ደላሎች በተመለከተ ጎልጉል በቂ መረጃ የሰበሰበ ሲሆን እንደ አስፈላጊነቱ ይፋ ያደርጋል። ይህ አዲስ አበባን ሊደፋ የተነሳው የደላላ ኃይል ላይ ክትትልና መረጃ ተሰብስቦ መጠናቀቁን ጎልጉል ስለሚያውቅ የመንግሥትን የክትትል ሥራ ላለማበላሸት ነው ማንነትን ጠቅሰን ለማተም ያለውደድነው። ይሁን እንጂ አዲስ አበባ ላይ ተራ ጮሌነት የትም እንደማያደርስ ጎልጉል ለማስታወቅ ይወዳል።

በተመሳሳይ ዜና በቡራዩ ከመሬት ጋር በተያያዘ ካርታ ለማውጣት፣ ለማደስና የይዞታ ማረጋገጫ ለመውሰድ በግልጽ ገንዘብ የሚጠየቅ መሆኑንን ነዋሪዎች ለጎልጉል አስታውቀዋል። ነዋሪዎች እንደሚሉት ብር የማይሰጥ አገልግሎት አያገኝም። ገንዘብ የሚጠየቀውም በግልጽ በአደባባይ ነው።

ለየአገልግሎት ዓይነቱ የተቀመጠ የገንዘብ መጠን መኖሩን የሚናገሩት ወገኖች፣ መንግሥትንና ሕዝብን የሚያቃቅሩት እንዲህ ያሉ ዜጎች በመሆናቸው የኦሮሚያ ክልል ቢያስብበት ሲሉ ጥቆማቸውን አቅርበዋል። የኦሮሚያ ክልል የበታች መዋቅሩን ባስቸኳይ ማስተካከል እንዳለበት በተደጋጋሚ አስተያየት ይሰጣል።


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ™ ንብረት ናቸው። ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Middle Column, News, Social Tagged With: addis condo, Full Width Top, Middle Column, takele uma

Reader Interactions

Comments

  1. golgul-aba-gora says

    March 9, 2020 07:24 pm at 7:24 pm

    እንዲህ ስትሉ ምን ማለታችሁ ይሆን?

    “ከፍተኛ የሚባሉት የአስተዳደሩ ሰው የሸጡትን ስፍራም ለይተው አስታውቀዋል። ይሁን እንጂ ጎልጉል ለጊዜው ከማተም ተቆጥቧል። በተለይም ከከንቲባው ቢሮ ጋር ትሥሥር ፈጥረው እየሠሩ ያሉትን ደላሎች በተመለከተ ጎልጉል በቂ መረጃ የሰበሰበ ሲሆን እንደ አስፈላጊነቱ ይፋ ያደርጋ”

    ለመሆኑ ጊዜ ካለፈ በኋላ “ይፋ” ልታወጡት ነው መረጃውን ወይስ “በመረጃው” ጥራትና አስተማማኝነት አላመናችሁበትም? ወይስ “መረጃው” በማስረጃ ያልተደገፈ ነው? በትኖሩበት የምዕራብ አገራት ምን እንደሚደረግ የምታውቁ ናችሁ፤ እንዲህ ዓይነት በማስረጃ የተደገፈ “መረጃ” ልፖሊስ/አቃቤ ሕግ/ ፓርላማ ወይም አግባብ ባለው ሚንስት/ባለሥልጣን/ኮሚሽን/ኤጀንሲ የኦዲትና ፖሊሲ አስፈፃሚ አክል ይተላለፋል፤ ታልሆነም የታክለ ዑማ ያለመመረጥ – ምርጫ ታለ ለዛውም – ዕድልን ማስፋቱ ይሆናል ያሳሰባችሁ፤ በደል ከሚደርስበት ዜጋ በላይ፤ ለነዚህ ዜጎች ስትሉ እባካችሁ “ይፋ” ባታደርጉትም የሰበሰባችሁትን “መረጃ” ለሚመለከተው ክፍል አስተላልፉ፤

    ደሞ እንዲህ ተባልን ብላችሁ አትበሳጩ መልዕቱን እንጂ መልዕከተኛው ተዉት – ተወዲህ ለማሳሰብ ያህል

    Reply
    • Editor says

      March 11, 2020 06:06 am at 6:06 am

      በጽሁፉ ውስጥ የተጠቀሰውን በትክክል ወይም በጽሞና ባለማንበብ የተሰጠ አስተያየት ነው፤ ዜናው ላይ ይህንን ብለናል፤

      ” . . . ይህ አዲስ አበባን ሊደፋ የተነሳው የደላላ ኃይል ላይ ክትትልና መረጃ ተሰብስቦ መጠናቀቁን ጎልጉል ስለሚያውቅ የመንግሥትን የክትትል ሥራ ላለማበላሸት ነው ማንነትን ጠቅሰን ለማተም ያለውደድነው። . . .”

      የጎልጉል አርታኢ

      Reply
  2. golgul-aba-gora says

    March 10, 2020 07:00 pm at 7:00 pm

    ለመጨመር ያህል፤ “መረጃ” ደርሶኛ ወይም ሰብስቤያለሁ ግን ይፋ አላደርገውም ማለት፤ አንድ – ወንጀል ሲሠራ አይቶ እንድማለፍ ያለ የዜግነትና ሕጋዊ ግዴታን አለመወጣት ነው፤ ሁለተኛ – ጠፋጥኞችን ተጠንቀቁ የሚል ደወል እንደ ማሰማት ነው፤ ማንኛውንም የገንዘብ ይዞታቸውን፤ የተጭበረበሩ ዶኪውመንቶቻቸውን፤ የግንኙነት መረባቸውን እንዲሰውሩ፤ ምናልባትም ራሳቸውን እንዲሰውሩ ማንቂያ ይሆናል፤ ትክክለኛው አሠራር የመረጃ ዶሴያችሁን ለፖሊስ ወይ ዐቃቤ ሕግ መጀመሪያ አቅርባችሁ ከሚከተለው ምርመራን ወይም የክሥ ሂደትን በማይጣረስ ብኩል ዜናው ማቅረብ ነው፤ ያንጊዜ መረጃ አለን ይፋ አናደርግም ሳይሆን መረጃውን ቀደም ብለን ለሚመለከተው ክፍል አስተላልፈናል ትሉና አንባቢም ያደንቅችሁአል፤

    Reply
    • Editor says

      March 11, 2020 06:05 am at 6:05 am

      በጽሁፉ ውስጥ የተጠቀሰውን በትክክል ወይም በጽሞና ባለማንበብ የተሰጠ አስተያየት ነው፤ ዜናው ላይ ይህንን ብለናል፤

      ” . . . ይህ አዲስ አበባን ሊደፋ የተነሳው የደላላ ኃይል ላይ ክትትልና መረጃ ተሰብስቦ መጠናቀቁን ጎልጉል ስለሚያውቅ የመንግሥትን የክትትል ሥራ ላለማበላሸት ነው ማንነትን ጠቅሰን ለማተም ያለውደድነው። . . .”

      የጎልጉል አርታኢ

      Reply
  3. wakeup says

    March 11, 2020 07:51 am at 7:51 am

    The following website is one
    of the most trustworthy
    alternative media world
    wide.Read it to know about
    the Covid and other deadly
    vaccines.
    http://www.globalresearch.ca/theme/science-and-medicine

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm
  • የተመሠረተው የፋኖ አደረጃጀት ዋነኛ ዓላማው ድርድር መሆኑ ተነገረ May 14, 2025 11:07 pm
  • ከፍተኛ የፋኖ አመራሮች መገደላቸው ተነገረ May 6, 2025 10:40 pm
  • ሃይማኖትን ለተራ የፖለቲካ ሸቀጥ ማዋል ውርደት ነው April 24, 2025 12:43 am
  •  የኬሪያ ኢብራሒም ኑዛዜ “ብትንትናችን ወጥቷል” April 22, 2025 12:08 am
  • ለወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን አመራሮች ወታደራዊ ሥልጠና ተሰጠ April 16, 2025 11:44 pm
  • ዓቅም እንደሌለው የገመገመው ሻዕቢያ ፊቱን ከጦርነት ወደ ዲፕሎማሲ እያዞረ ነው   April 15, 2025 12:32 am
  • “አንድ የፋኖ ተቋም (የእስክንድር) ተመሥርቷል፤ ሌሎቹ ደግሞ እንዲሁ አንድ ተቋም መሥርተው ወደዚህ ይመጡ” አበበ ጢሞ April 11, 2025 12:07 am
  • መለስ (ለገሰ) ዜናዊ – ተዋርዶ ያዋረደን! April 9, 2025 10:28 pm
  • የተከዜ ዘብ: የሉዓላዊነት መጠበቂያ April 8, 2025 11:49 pm
  • አዲስ አበባ አስተዳደር የሪፖርተርን የተዛባ መረጃ ኮነነ፤ ሕጋዊ እርምጃ እወስዳለሁ አለ April 8, 2025 10:06 pm
  • ሀሰተኛውን የሪፖርተር ዘገባ ንግድ ባንክ በጽኑ ተቃወመ፤ እርማትም ጠየቀ April 8, 2025 09:48 pm
  • “ኦሮሚያ ላይ ወይም ሌላ ቦታ ላይ ስታደርገው ከነበረ ትግራይ ወስጥም የማታደርግበት ምንም ምክንያት አይኖርህም” ነው ጌታቸው ረዳ April 7, 2025 10:22 pm
  • “TPLF’s belief in a strong federal government was always tied to its own dominance in Addis Ababa” April 7, 2025 10:15 pm
  • Counter-Video by EBC Challenges EBS Broadcast, Sparks Public Outcry Over Alleged Misinformation March 31, 2025 02:36 am
  • የኤሊያስ መሠረትን ፌክ መረጃ ማን ያጋልጥ? February 19, 2025 06:00 pm
  • አዘርባጃን፡ የሻዕቢያን ሸምቀቆ ማጥበቂያ?! February 19, 2025 12:29 am
  • የአሜሪካ ድምፅ/ቪኦኤ ይዘጋ ተባለ  February 12, 2025 03:37 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ሹመኛ ካድሬዎች February 3, 2025 11:07 am
  • ትግሉን የጎዳው የእስክንድር ነጋ አካሄድ February 3, 2025 10:29 am
  • ኤሊያስ መሠረት “ጭምብሉ ዛሬ ወለቀ”፤ ተከፋይ ነው! February 2, 2025 05:32 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule