• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሃና ላላንጎ ጉዳይ በዝግ ችሎት ታየ

December 4, 2014 10:17 am by Editor Leave a Comment

* “አሸባሪዎችን” ለይቶ የመያዝ “ልዩ ችሎታና ብቃት” ያለው ፖሊስ ያልያዘው ተጠርጣሪ አለ

ሃና ላላንጎ የተባለችውን ተማሪ በሚኒባስ ታክሲ አፍነው በመውሰድ፣ በቡድን በመድፈርና ሕይወቷ እንዲያልፍ አድርገዋል በሚል ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙትን አምስት ተጠርጣሪዎች የፍርድ ቤት ጉዳይ በዝግ ችሎት መታየት ጀመረ፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ለሦስተኛ ጊዜ ኅዳር 22 ቀን 2007 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤት፣ ቂርቆስ ምድብ ችሎት የቀረቡ ሲሆን፣ ፖሊስ ቀደም ባለው ቀጠሮ እንደሚሠራቸው ያስመዘገበውን ቀሪ የምርመራ ሒደት፣ ለችሎቱ ያስረዳበትና ተጠርጣሪዎቹን ያቀረበበት ሰዓት፣ ከሌሎች ቀናት የተለየ ነበር፡፡

ሟች ሃና ላላንጎ በቡድን ተደፍራ ሕይወቷ ማለፉ በመገናኛ ብዙኃን ከተሰራጨበት ጊዜ አንስቶ እያነጋገረ ከመሆኑም በተጨማሪ፣ በየቀጠሮው ፍርድ ቤት የሚገኘው ታዳሚ ቁጥር ጨምሯል፡፡ ኅዳር 22 ቀን 2007 ዓ.ም. እንደተለመደው ፖሊስ ዘግየት ብሎ ከ4፡30 ሰዓት በኋላ እንደሚመጣ በማሰብ፣ ሕዝቡ ወደ ፍርድ ቤት መድረስ የጀመረው በአብዛኛው ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት ጀምሮ ነበር፡፡

የጠዋቱ ጊዜ ወደ እኩለ ቀን እየተቃረበ በመሄዱ፣ ሕዝቡ እርስ በራሱ “አራዳ አቅርበዋቸዋል አሉ፤ አይ አይደለም ልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ክስ መሥርተዋልና ፖሊስ እንጂ ተጠርጣሪዎቹ አይቀርቡም፤” የሚሉና ሌሎች መላምቶችን በመነጋገር ላይ እያለ፣ ፖሊስ ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ላይ ተጠርጣሪዎቹን ይዞ ቀርቦ፣ ማንም ወደ ችሎት ሳይገባ በዝግ ችሎት፣ የሠራውን የምርመራ ሒደት ለፍርድ ቤቱ ካስረዳ በኋላ፣ ለሚቀረው ተጨማሪ ምርመራ 14 ቀናትን ጠይቆ እንደተፈቀደለት ተሰማ፡፡ ለታኅሣሥ 6 ቀን 2007 ዓ.ም. መቀጠሩም ታወቀ፡፡

የተነገረውን ለማረጋገጥና ተጨማሪ መረጃ ለመስማት ቀጠሮውን ወደሰጡት ዳኛ የሟች ዘመዶችና የመገናኛ ብዙኃን በመሄድ ሲጠይቁ፣ ጠዋት በሥራ ሰዓት ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ይዞ በመቅረብ፣ ችሎቱ በዝግ እንዲታይለት ባመለከተው መሠረት ፍርድ ቤቱም ስላመነበት በዝግ ችሎት መታየቱ ተረጋገጠ፡፡

በሕገ መንግሥቱም ሆነ በፍርድ ቤቶች አሠራር በዝግ መታየት ያለባቸው የወንጀል ድርጊቶች መኖራቸው እንዳለ ሆኖ፣ ተማሪ ሃና ላላንጎን ሕይወቷ እንዲያልፍ አድርገዋል የተባሉት ተጠርጣሪዎች ጉዳይ፣ ለሁለት ጊዜያት በግልጽ ችሎት ከታየ በኋላ፣ በየትኛው የሕግ መሠረት ሦስተኛው ቀጠሮ በዝግ ሊታይ እንደቻለ ማብራሪያ እንዲሰጡ ዳኛው ተጠይቀው ነበር፡፡

የሃና ጉዳይ በዝግ ችሎት እንዲታይ የተወሰነው፣ ፖሊስ ምርመራውን ሳይጨርስ የተለያዩ የመገናኛ ብዙኃንና ድረ ገጾች፣ የሆነውንና ያልሆነውን ዘገባ በማሰራጨት ለምርመራው እንቅፋት እየፈጠሩበት መሆኑን አስረድቶ፣ ምርመራውን እስከሚያጠናቅቅ ድረስ በዝግ ችሎት እንዲታይለት መጠየቁ አሳማኝ ሆኖ በመገኘቱ በዝግ ችሎት እንዲታይ መፈቀዱን አስረድተዋል፡፡

hana 2ፖሊስ ኅዳር 22 ቀን 2007 ዓ.ም. ተጠርጣሪዎቹን በችሎት አቅርቦ ቀደም ባለው ችሎት ያስመዘገበውን ቀሪ የምርመራ ሒደት ምን ያህሉን እንደሠራና ምን ያህሉ እንደቀረው ማወቅ ባይቻልም፣ ቀደም ባለው ቀጠሮ ተጨማሪ 14 ቀናትን ጠይቆ፣ ፍርድ ቤቱ ‹‹10 ቀናት ይበቃሃል›› በማለት ከጠየቀው ቀናት ላይ አራት ቀናትን የቀነሰ ከመሆኑ አንፃር፣ ኅዳር 22 ቀን 2007 ዓ.ም. የጠየቀውን 14 ቀናት ሙሉውን መፍቀዱ፣ ሌላ ተጨማሪ ተጠርጣሪ የመያዝና በርካታ ቀሪ ምርመራ ሳይኖረው እንዳልቀረ ጥርጣሬ አሳድሯል፡፡

የሟች ተማሪ ሃና ወላጅ አባት አቶ ላላንጎ አይሶ ኅዳር 21 ቀን 2007 ዓ.ም. በየሳምንቱ እሑድ ምሽት ላይ በኢቢኤስ በሚቀርበው “ሰይፉ ፋንታሁን ሾው” ላይ ቀርበው ፖሊስ አንድ ተጠርጣሪን መያዝ እንደሚቀረው በመናገራቸው፣ ኅዳር 22 ቀን 2007 ዓ.ም. ጉዳዩ በዝግ መታየቱንና 14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ መፍቀዱን ተከትሎ ጥርጣሬውን አጠናክሮታል፡፡

አቶ ላላንጎ ሟች ልጃቸው መስከረም 21 ቀን 2007 ዓ.ም. ታፍና መወሰዷንና ለ20 ቀናት አስታመዋት፣ በደረሰባት ከባድ ጉዳት ልትተርፍ አለመቻሏን ገልጸዋል፡፡ እንደ አቶ ላላንጎ ገለጻ፣ ልጃቸው ጦር ኃይሎች ሙሉ ወንጌል ቤተ ክርስቲያን አካባቢ ተጥላ ከተገኘች በኋላ፣ ወዲያውኑ ወደ አለርት ሆስፒታል ወስደዋታል፡፡ የአለርት ሆስፒታል ዶክተሮች ተመልክተዋት በስለት በመወጋቷና በደረሰባት የመደፈር አደጋ ሕይወቷን ልታጣ እንደምትችል በመናገር፣ ሕይወቷ ከማለፉ በፊት ቃሏን ለፖሊስ እንድትሰጥ በመናገራቸው ቃሏን እንድትሰጥ ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡

የሃና ላላንጎ ወላጅ አባት ስለልጃቸው ስቃይ እንዳብራሩት፣ አለርት ሆስፒታል ከአቅሙ በላይ መሆኑን ገልጾ ወደ ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል ሪፈር ተብለው ሲወስዷት፣ ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል ደግሞ ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በሪፈር እንዲወስዷት እንደነገራቸው አስረድተዋል፡፡ ያለምንም ሕክምና ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል፣ መልሶ ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል ሲልካቸው ተስፋ የቆረጡት አቶ ላላንጎ፣ ልጃቸውን በቀጥታ ወደ ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል መውሰዳቸውን ትተው፣ ወደ መኖሪያ ቤታቸው በመውሰድ አንድ ቀን አድራና ቤተሰቦቿን ተሰናብታ፣ በማግስቱ ወደ ጋንዲ ሆስፒታል እንደወሰዷት ገልጸዋል፡፡ ለሁለተኛ ጊዜ ጋንዲ ሆስፒታል በሪፈር የሄደችው ሟች ሃና፣ ይኸ ሁሉ ውጣ ውረድ ሲደረግ ደም እየፈሰሳትና ቁስሏም ወደ ሌላ ሕመም እየተቀየረ መሆኑን የገለጹት አባቷ፣ ሙሉቀን በጋንዲ ሆስፒታል ከቆየች በኋላ፣ ዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል አልጋ ተገኝቶላት መተኛት መቻሏን ተናግረዋል፡፡

የዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል ሐኪሞች የሃናን ጉዳትና ሕመም ሲመለከቱ፣ በከፍተኛ ሐዘንና እንባ ታጅበው ለማትረፍ የተረባረቡ ቢሆንም፣ ችግሩ ወደ ሌላ ነገር ተቀይሮ የነበረ በመሆኑ ሕይወቷ ሊተርፍ አለመቻሉን ገልጸዋል፡፡

አቶ ላላንጎ የልጃቸውን ስቃይ በሐዘን ሲገልጹ፣ ሐኪሞችንና ፖሊሶችን ወቅሰዋል፡፡ “ሁሉንም ሐኪምና ሁሉንም ፖሊስ በጅምላ መውቀስ አልፈልግም፤” ብለው፣ መልካምና ሥራቸውን የሚወዱ፣ ኃላፊነታቸውን የሚወጡ ሐኪሞችና ፖሊሶች ስላሉ እነሱን ማመስገን እንደሚፈልጉ ገልጸዋል፡፡ ልጃቸው ደም እየፈሰሳት በሄዱበት ሆስፒታሎች “አልጋ የለም፣ ውጭ አስመርምሯት” ማለትና ችላ ማለት ተገቢና የገቡለትም ቃል ኪዳን ባለመሆኑ፣ ተገቢ አለመሆኑን በመናገር፣ መንግሥትም ሊከታተለው እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ ፖሊሶችም ቢሆኑ፣ ጉዳዩን በትጋት ተከታትለውና ራሳቸው የሚሆነውን እንደማድረግ “እዚያ ውሰድ እኛ ጋ አይደለም” በማለት እንዲንገላቱ ማድረጋቸው ተገቢ ባለመሆኑ መንግሥትም ሊያየው የሚገባ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ (ምንጭ ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am
  • አገር አፍራሹ ትህነግ ለቀለብ፣ መድኃኒትና ሥራ ማስኬጃ 76 ቢሊዮን ብር ቀርጥፏል May 16, 2022 08:30 am
  • እየተባባሰ ከመጣው የማህበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች ዜጎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ ተጠየቀ May 15, 2022 09:38 am
  • የትህነግና ሸኔ መሠልጠኛ የምትባለው ዩጋንዳ መከላከያ ሚ/ር ከኤታማዦር ሹሙ ጋር ተወያዩ May 13, 2022 09:55 am
  • በትግራይ የውጊያ ምልመላው ጉዳይ May 11, 2022 02:37 am
  • መከላከያ በተጨማሪ ድሮን፣ በሥልጠና፣ በዝግጅት ራሱን አብቅቷል May 11, 2022 01:35 am
  • ትህነግ ለሌላ ውጊያ እየተዘጋጀ ነው ተባለ May 10, 2022 01:04 pm
  • ኤርትራ 8 ሩስያ ሠራሽ ድሮኖችን ተረክባለች May 10, 2022 12:37 am
  • ሙስሊምና ክርስቲያን በአንድነት የሚያከብረው የአኾላሌ ባሕላዊ ጭፈራ May 9, 2022 01:46 pm
  • በወልዲያ ፋኖዎች ተመረቁ May 9, 2022 12:51 pm
  • “ሠራዊታችን ድልን በአስተማማኝ መልኩ ማምጣት በሚችል ቁመና ላይ” ጀኔራል ጌታቸው May 9, 2022 11:57 am
  • ዋጋው 64 ሚሊዮን ብር የሚሆን (16 ኪሎ) ሕገወጥ ወርቅ ተያዘ May 9, 2022 11:51 am
  • አብን ክርስቲያን ታደለን ለመጨረሻ ጊዜ አስጠነቀቀ፤ 10 አባላቱን አገደ May 9, 2022 08:58 am
  • ራሱ አቡክቶ፣ ራሱ አሟሽሾ፣ ራሱ ጋግሮ በሰዓት 460 እንጀራ የሚያወጣ ፈጠራ May 9, 2022 08:17 am
  • በህገ ወጥ መንገድ 19 ህጻናትን ሲያዘዋወሩ የነበሩ 6 ሴቶች ተያዙ May 8, 2022 12:39 am
  • በአርሲ ሙስሊሞች ለቤ/ክ ማሠሪያ 3 ሚሊዮን ብርና 20 የቀንድ ከብት ሰጡ May 6, 2022 09:35 am
  • በአዲስ አበባ የሚኖረው የትህነግ ደጋፊ ማንነት በማስረጃ May 4, 2022 11:04 pm
  • ሙስሊም ወንድማማች የቤ/ክ ዘራፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋሉ May 4, 2022 09:04 am
  • ከ6 ሺህ የዓሳ ጫጩት ወደ 80 ሺህ May 4, 2022 08:57 am
  • ተስፋቢሱ ቴድሮስ May 3, 2022 12:16 pm
  • ከሽፏል! April 6, 2022 11:58 am
  • “ሩሲያ ዩክሬይንን ወረረች” እየተባለ ስለሚነዛው ወሬ ጥቂት እውነታዎች March 8, 2022 11:30 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule