• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሃና ላላንጎ ጉዳይ በዝግ ችሎት ታየ

December 4, 2014 10:17 am by Editor Leave a Comment

* “አሸባሪዎችን” ለይቶ የመያዝ “ልዩ ችሎታና ብቃት” ያለው ፖሊስ ያልያዘው ተጠርጣሪ አለ

ሃና ላላንጎ የተባለችውን ተማሪ በሚኒባስ ታክሲ አፍነው በመውሰድ፣ በቡድን በመድፈርና ሕይወቷ እንዲያልፍ አድርገዋል በሚል ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙትን አምስት ተጠርጣሪዎች የፍርድ ቤት ጉዳይ በዝግ ችሎት መታየት ጀመረ፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ለሦስተኛ ጊዜ ኅዳር 22 ቀን 2007 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤት፣ ቂርቆስ ምድብ ችሎት የቀረቡ ሲሆን፣ ፖሊስ ቀደም ባለው ቀጠሮ እንደሚሠራቸው ያስመዘገበውን ቀሪ የምርመራ ሒደት፣ ለችሎቱ ያስረዳበትና ተጠርጣሪዎቹን ያቀረበበት ሰዓት፣ ከሌሎች ቀናት የተለየ ነበር፡፡

ሟች ሃና ላላንጎ በቡድን ተደፍራ ሕይወቷ ማለፉ በመገናኛ ብዙኃን ከተሰራጨበት ጊዜ አንስቶ እያነጋገረ ከመሆኑም በተጨማሪ፣ በየቀጠሮው ፍርድ ቤት የሚገኘው ታዳሚ ቁጥር ጨምሯል፡፡ ኅዳር 22 ቀን 2007 ዓ.ም. እንደተለመደው ፖሊስ ዘግየት ብሎ ከ4፡30 ሰዓት በኋላ እንደሚመጣ በማሰብ፣ ሕዝቡ ወደ ፍርድ ቤት መድረስ የጀመረው በአብዛኛው ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት ጀምሮ ነበር፡፡

የጠዋቱ ጊዜ ወደ እኩለ ቀን እየተቃረበ በመሄዱ፣ ሕዝቡ እርስ በራሱ “አራዳ አቅርበዋቸዋል አሉ፤ አይ አይደለም ልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ክስ መሥርተዋልና ፖሊስ እንጂ ተጠርጣሪዎቹ አይቀርቡም፤” የሚሉና ሌሎች መላምቶችን በመነጋገር ላይ እያለ፣ ፖሊስ ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ላይ ተጠርጣሪዎቹን ይዞ ቀርቦ፣ ማንም ወደ ችሎት ሳይገባ በዝግ ችሎት፣ የሠራውን የምርመራ ሒደት ለፍርድ ቤቱ ካስረዳ በኋላ፣ ለሚቀረው ተጨማሪ ምርመራ 14 ቀናትን ጠይቆ እንደተፈቀደለት ተሰማ፡፡ ለታኅሣሥ 6 ቀን 2007 ዓ.ም. መቀጠሩም ታወቀ፡፡

የተነገረውን ለማረጋገጥና ተጨማሪ መረጃ ለመስማት ቀጠሮውን ወደሰጡት ዳኛ የሟች ዘመዶችና የመገናኛ ብዙኃን በመሄድ ሲጠይቁ፣ ጠዋት በሥራ ሰዓት ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን ይዞ በመቅረብ፣ ችሎቱ በዝግ እንዲታይለት ባመለከተው መሠረት ፍርድ ቤቱም ስላመነበት በዝግ ችሎት መታየቱ ተረጋገጠ፡፡

በሕገ መንግሥቱም ሆነ በፍርድ ቤቶች አሠራር በዝግ መታየት ያለባቸው የወንጀል ድርጊቶች መኖራቸው እንዳለ ሆኖ፣ ተማሪ ሃና ላላንጎን ሕይወቷ እንዲያልፍ አድርገዋል የተባሉት ተጠርጣሪዎች ጉዳይ፣ ለሁለት ጊዜያት በግልጽ ችሎት ከታየ በኋላ፣ በየትኛው የሕግ መሠረት ሦስተኛው ቀጠሮ በዝግ ሊታይ እንደቻለ ማብራሪያ እንዲሰጡ ዳኛው ተጠይቀው ነበር፡፡

የሃና ጉዳይ በዝግ ችሎት እንዲታይ የተወሰነው፣ ፖሊስ ምርመራውን ሳይጨርስ የተለያዩ የመገናኛ ብዙኃንና ድረ ገጾች፣ የሆነውንና ያልሆነውን ዘገባ በማሰራጨት ለምርመራው እንቅፋት እየፈጠሩበት መሆኑን አስረድቶ፣ ምርመራውን እስከሚያጠናቅቅ ድረስ በዝግ ችሎት እንዲታይለት መጠየቁ አሳማኝ ሆኖ በመገኘቱ በዝግ ችሎት እንዲታይ መፈቀዱን አስረድተዋል፡፡

hana 2ፖሊስ ኅዳር 22 ቀን 2007 ዓ.ም. ተጠርጣሪዎቹን በችሎት አቅርቦ ቀደም ባለው ችሎት ያስመዘገበውን ቀሪ የምርመራ ሒደት ምን ያህሉን እንደሠራና ምን ያህሉ እንደቀረው ማወቅ ባይቻልም፣ ቀደም ባለው ቀጠሮ ተጨማሪ 14 ቀናትን ጠይቆ፣ ፍርድ ቤቱ ‹‹10 ቀናት ይበቃሃል›› በማለት ከጠየቀው ቀናት ላይ አራት ቀናትን የቀነሰ ከመሆኑ አንፃር፣ ኅዳር 22 ቀን 2007 ዓ.ም. የጠየቀውን 14 ቀናት ሙሉውን መፍቀዱ፣ ሌላ ተጨማሪ ተጠርጣሪ የመያዝና በርካታ ቀሪ ምርመራ ሳይኖረው እንዳልቀረ ጥርጣሬ አሳድሯል፡፡

የሟች ተማሪ ሃና ወላጅ አባት አቶ ላላንጎ አይሶ ኅዳር 21 ቀን 2007 ዓ.ም. በየሳምንቱ እሑድ ምሽት ላይ በኢቢኤስ በሚቀርበው “ሰይፉ ፋንታሁን ሾው” ላይ ቀርበው ፖሊስ አንድ ተጠርጣሪን መያዝ እንደሚቀረው በመናገራቸው፣ ኅዳር 22 ቀን 2007 ዓ.ም. ጉዳዩ በዝግ መታየቱንና 14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ መፍቀዱን ተከትሎ ጥርጣሬውን አጠናክሮታል፡፡

አቶ ላላንጎ ሟች ልጃቸው መስከረም 21 ቀን 2007 ዓ.ም. ታፍና መወሰዷንና ለ20 ቀናት አስታመዋት፣ በደረሰባት ከባድ ጉዳት ልትተርፍ አለመቻሏን ገልጸዋል፡፡ እንደ አቶ ላላንጎ ገለጻ፣ ልጃቸው ጦር ኃይሎች ሙሉ ወንጌል ቤተ ክርስቲያን አካባቢ ተጥላ ከተገኘች በኋላ፣ ወዲያውኑ ወደ አለርት ሆስፒታል ወስደዋታል፡፡ የአለርት ሆስፒታል ዶክተሮች ተመልክተዋት በስለት በመወጋቷና በደረሰባት የመደፈር አደጋ ሕይወቷን ልታጣ እንደምትችል በመናገር፣ ሕይወቷ ከማለፉ በፊት ቃሏን ለፖሊስ እንድትሰጥ በመናገራቸው ቃሏን እንድትሰጥ ማድረጋቸውን ተናግረዋል፡፡

የሃና ላላንጎ ወላጅ አባት ስለልጃቸው ስቃይ እንዳብራሩት፣ አለርት ሆስፒታል ከአቅሙ በላይ መሆኑን ገልጾ ወደ ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል ሪፈር ተብለው ሲወስዷት፣ ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል ደግሞ ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በሪፈር እንዲወስዷት እንደነገራቸው አስረድተዋል፡፡ ያለምንም ሕክምና ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል፣ መልሶ ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል ሲልካቸው ተስፋ የቆረጡት አቶ ላላንጎ፣ ልጃቸውን በቀጥታ ወደ ጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል መውሰዳቸውን ትተው፣ ወደ መኖሪያ ቤታቸው በመውሰድ አንድ ቀን አድራና ቤተሰቦቿን ተሰናብታ፣ በማግስቱ ወደ ጋንዲ ሆስፒታል እንደወሰዷት ገልጸዋል፡፡ ለሁለተኛ ጊዜ ጋንዲ ሆስፒታል በሪፈር የሄደችው ሟች ሃና፣ ይኸ ሁሉ ውጣ ውረድ ሲደረግ ደም እየፈሰሳትና ቁስሏም ወደ ሌላ ሕመም እየተቀየረ መሆኑን የገለጹት አባቷ፣ ሙሉቀን በጋንዲ ሆስፒታል ከቆየች በኋላ፣ ዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል አልጋ ተገኝቶላት መተኛት መቻሏን ተናግረዋል፡፡

የዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል ሐኪሞች የሃናን ጉዳትና ሕመም ሲመለከቱ፣ በከፍተኛ ሐዘንና እንባ ታጅበው ለማትረፍ የተረባረቡ ቢሆንም፣ ችግሩ ወደ ሌላ ነገር ተቀይሮ የነበረ በመሆኑ ሕይወቷ ሊተርፍ አለመቻሉን ገልጸዋል፡፡

አቶ ላላንጎ የልጃቸውን ስቃይ በሐዘን ሲገልጹ፣ ሐኪሞችንና ፖሊሶችን ወቅሰዋል፡፡ “ሁሉንም ሐኪምና ሁሉንም ፖሊስ በጅምላ መውቀስ አልፈልግም፤” ብለው፣ መልካምና ሥራቸውን የሚወዱ፣ ኃላፊነታቸውን የሚወጡ ሐኪሞችና ፖሊሶች ስላሉ እነሱን ማመስገን እንደሚፈልጉ ገልጸዋል፡፡ ልጃቸው ደም እየፈሰሳት በሄዱበት ሆስፒታሎች “አልጋ የለም፣ ውጭ አስመርምሯት” ማለትና ችላ ማለት ተገቢና የገቡለትም ቃል ኪዳን ባለመሆኑ፣ ተገቢ አለመሆኑን በመናገር፣ መንግሥትም ሊከታተለው እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ ፖሊሶችም ቢሆኑ፣ ጉዳዩን በትጋት ተከታትለውና ራሳቸው የሚሆነውን እንደማድረግ “እዚያ ውሰድ እኛ ጋ አይደለም” በማለት እንዲንገላቱ ማድረጋቸው ተገቢ ባለመሆኑ መንግሥትም ሊያየው የሚገባ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ (ምንጭ ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • በአዲስ አበባ የተወረረው መሬት፣ ባለቤት አልባ ቤቶችና ሕንጻዎች ይፋ ሆኑ January 26, 2021 11:16 am
  • የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አክቲቪስቶችን በሕግ ተጠያቂ አደርጋለሁ አለ January 26, 2021 10:32 am
  • የሰባት ቤት አገው የፈረሰኞች ማኅበር 81ኛ የምስረታ በዓል January 26, 2021 07:17 am
  • በጋምቤላ ህወሃትንና ኦነግ ሸኔን ትረዳላችሁ ተብለው የታሰሩ እንዲፈቱ ተጠየቀ January 25, 2021 03:07 pm
  • “…ሰብዓዊ እርዳታ እየቀረበ አይደለም የሚሉ አካላት የፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ነው” – ዶ/ር ሙሉ ነጋ January 25, 2021 01:02 pm
  • የሶማሌና ኦሮሚያ መሥተዳድሮች ወሰንን በተመለከተ የሰላምና የጋራ ልማት ስምምነት አደረጉ January 25, 2021 12:50 pm
  • 125ተኛውን የአድዋ ድል በዓል በድምቀት ሊከበር ነው January 25, 2021 09:34 am
  • በመቀሌ ከ350 ሚሊዮን ብር በላይ የህክምና ግብዓቶች ክምችት መኖሩ ታወቀ January 25, 2021 02:47 am
  • ዊንጉ አፍሪካ (wingu.africa) በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የመረጃ ማዕከል ሊገነባ ነው January 24, 2021 01:23 pm
  • ኢትዮጵያ ድሮኖችን ማምረት ልትጀምር ነው January 24, 2021 02:40 am
  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule