እኅቴ ወ/ሮ ሚሊ ተስፋዬ እንደምን አለሽ በዚህ ዘመን የሚሠሩት የሀገራችን ፊልሞችና ድራማዎች (ምትርኢቶችና ትውንተ-ድርሰቶች) ከሞላ ጎደል ከሀገርና ከሕዝብ ጥቅም አንጻር ደርዝ፣ ጭብጥ፣ ትልም ያላቸው አይደሉምና፤ ፖለቲካዊ (እምነተ-አሥተዳደራዊ) እና ማኅበራዊ ጉዳዮች ከሀገር ጥቅም አንጻር በጥልቀትና በብስለት የሚዳሰስባቸው አይደሉምና ተከታታይ አይደለሁም፡፡ በመሆኑም በዚህ ኢንደስትሪ (ምግንባብ) ባለሽና በነበረሽ ሚና አላውቅሽም ነበር፡፡
በእንጨዋወት የኢ.ቢ.ኤስ የቴሌቪዥን (የምርዓዬ ኩነት) ትዕይንተ-ወግ (ቶክ ሾው) ዝግጅት ላይ እንግዳ ሆነሽ ቀርበሽ ያደረግሽውን ወግ ስመለከት ሃይማኖትሽን ስለ መቀየርሽ ስታወሪ “ክርስቲያን ሆንኩኝ፤ ክርስቲያን ከሆንኩ በኋላ…” እያልሽ የገለጽሽው አገላለጽ በጣም ስለገረመኝና የሠራሽው ስሕተት ከብዶ ቢታየኝ ነው ይህችን መልእክት ልጽፍ የተገደድኩት፡፡
እኅቴ በእርግጥ ይህ የተሳሳተ አገላለጽ ያንቺ ብቻ ሳይሆን በየ ብዙኃን መገናኛው ሃይማኖትን የቀየሩ ዜጎቻችን ሃይማኖታቸውን መቀየራቸውን ሲገልጹ ሆን ብለው የሚጠቀሙት ቃል ወይም አገላለጽ ነው፡፡ አንቺ የነበርሽበት ሃይማኖት (የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ) ውስጥ ያለን ምእመናን ሁሉ ክርስቲያኖች እንደሆንን እናውቃለን፡፡ አንቺ ግን እኛ ክርስቲያን እንዳልሆንንና አንቺም ክርስቲያን እንዳልነበርሽ ሁሉ ሃይማኖትሽን መቀየርሽን “ክርስቲያን ሆንኩ” በሚል ቃል ገለጽሽ፡፡ ሌሎችም እንዳንችው በሥነ-ኪን ዘርፍ ውስጥ ያሉ ወገኖቻችን ጥጋብና ዝና የሚሠሩትን ሲያሳጣቸው ለዚያ ባበቃቸው ሕዝብ ላይ ሲወረግጡ ምኑንም ሳያውቁት ሃይማኖታቸውን ይቀይሩና በብዙኃን መገናኛ ቀርበው አስቀድሞ በነበሩበት ሃይማኖት ያለን ክርስቲያኖች ጌታን እንዳልተቀበልን ሁሉ “ጌታን ተቀበልኩ” ሲሉ ይገልጻሉ፡፡
እነዚህ አገላለጾች ሳይታሰብባቸው በአጋጣሚ የሚባሉ ቃላቶች አይደሉም፡፡ ሆን ተብሎ ለማጥቃት የሚሰነዘሩ እኩይና አጥቂ ቃላቶች ናቸው እንጂ፡፡ እነዚህ ሰዎች ማንንም ማጥቃት ሳያስፈልጋቸው ፕሮቴስታንት (ተቃዋሚ) ሆንኩ በማለት ያላቸውን ለውጥ መግለጥ የሚችሉበት ዕድል ነበር፡፡ በጣም የሚገርመኝ ነገር ቢኖር የብዙኃን መገናኛዎቹ ለእነዚህ ሰዎች እንዴት ይሄንን ጥቃት ለመፈጸሚያ መገልገያ መጠቀሚያ ለመሆን እንደሚፈቅዱና ጥቃቱን እንደሚያስተናግዱ ነው፡፡ በእርግጥ አንዳንዴም ወያኔ ለኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ባለው ጥላቻና ጠላትነት ሆን ተብሎ የተቀነባበረ የጥቃት ሴራ እንደሚደረግ ይታወቃል፡፡ ከዚህ ውጪ ግን ምናልባት ሳይስተዋል ስሕተቱን የሚፈጽሙ ወገኖች ካሉ ስሕተቱ በተደጋጋሚ ለረጅም ጊዜ ሲፈጸም የኖረ ጉዳይ በመሆኑ በዚሁ ሊቀጥል ይችላል ከሚል ሥጋትም አንጻር ያለውን እውነት ፍርጥርጥ ባለ መልኩ ዳስሸ ለማስረዳት፣ ግንዛቤውን በመስጠት ስሕተቱ እንዳይደገም ከማድረግ አንጻርም ነው ጽሑፏን መጻፌ፡፡
ወ/ሮ ሚሊ ሃይማኖትሽን ከመለወጥሽ በፊት ሕይዎትሽ ዓለማዊ (ኃጢአት የበዛበት) እንደነበር ነግረሽናል፡፡ ታዲያ ከዚህ ሕይዎት ለመውጣት ያንን ጥሩ ያልሆነ ሕይዎትሽን ለመቀየር መቀየር የነበረብሽ ራስሽን እንጂ ሃይማኖትሽን እኮ አልነበረም መቀየር የነበረብሽ፡፡ ምክንያቱም የነበርሽባት ሃይማኖት ዓለማዊነትን አትሰብክምና ኃጢአተኞች ሁኑ ብላ አትሰብክም አታስተምርምና፡፡
ወ/ሮ ሚሊ ያንች ምትርኢት (ፊልም) ምንም እንኳን ያየሁት ባይሆንም ካወራቹህት እንደተረዳሁት ከሆነ ሊኖረው ከሚችለው ማኅበራዊ ፋይዳ አንጻር ስመዝነው በጣም ጠቃሚና ጥሩ ነው ማለት እችላለሁ፡፡ ለሕዝባችን ማኅበራዊና መንፈሳዊ ጤና ተጨንቀሽ ይሄንን ምትርኢት በማቅረብሽም ስለ እውነት በጣም አደንቅሻለሁ፡፡ ይሄ ድካምሽ ከንቱ ሆኖ ሊቀር ከመቻሉ አንጻር ካለኝ ሥጋት አኳያም እጅግ አዝኘልሻለሁ፡፡ በሃይማኖት ውስጥ ሆነሽ ይሄንን ግሩም ሥራ ሠርተሽ ቢሆን ኖሮ ከጌታ ዘንድ ምን ያህል ዋጋ ባሰጠሸ ነበር፡፡ ምን ማለቴ መሰለሽ በወጋቹህ ወቅት ምትርኢትሽን ከመሥራትሽ በፊት ጥናት እንዳደረግሽ ነግረሽናል፡፡ ከጥናትሽ እስከአሁንም ልብ ያላልሽውን አንድ ቁም ነገር እንዳገኘሽ አምናለሁ፡፡ ጥናት ስታደርጊ ልሳን ተገለጸልን ብለው በየ አዳራሹ ምንነቱን የማያውቁትን የሚያዥጎደጉዱትን የዛር መንፈስ ቋንቋ እንደ ፓስተሮቹ ሁሉ በየጠንቋዩ በየቃልቻው ቤት በቃልቾቹ ወይም በጠንቋዮቹ አንደበት ሲባል ሲዥጎደጎድ ሰማሽ አይደል? እንዴትና ለምንስ ሊሆን እንደቻለ የምታውቂው ነገር አለ እኅት ወ/ሮ ሚሊ? የሚሠራባቸው መንፈስ አንድ ስለሆነ ነው ሌላ አይደለም፡፡
በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ሐዋርያት ልሳናት(ቋንቋዎች) ተገልጸውላቸው ነበር፡፡ የሐዋ. ሥራ 2፤4-13 እነዚያ ለሐዋርያቱ የተገለጹላቸው ልሳናት ወይም ቋንቋዎች ታዲያ ከተለያዩ ሀገራት መተው በዚያ ተሰብስበው የነበሩ የተለያዩ ሀገራት ሰዎች ቋንቋዎች በመሆናቸው በዚያ የነበሩ የተለያዩ ሀገራት ሰዎች ሐዋርያት ቋንቋዎቻቸውን በመናገራቸው “እነዚህ ዕብራዊያን ሲሆኑ እንዴት በየቋንቋችን ሊናገሩን ቻሉ?” በማለት ተደነቁ እንጂ ልሳን ተገለጸልን ብለው ምንነቱ የማይታወቅ የቃላት እሩምታ እንደሚያዥጎደጉዱት ፓስተሮች ማንም የማያዳምጠውንና የማያውቀውን አይደለም የተናገሩት፡፡ ታዲያ እኅቴ አዳራሽ ውስጥ በአገልጋዮችሽ አንደበት ስትሰሚው የነበረውን የክፉ መንፈስ ቋንቋ ጠንቋይ ቤትም መስማትሽ ምንም የጫረብሽ ጥያቄ አልነበረም?
ይሄውልሽ እኅቴ ወ/ሮ ሚሊ የዋህ አትሁኝ ሃይማኖት አንዲት ናት ከዚህች አንዲት ሃይማኖት ውጪ እንድንበት እንጓዝበት እንኖርበት ዘንድ የተሰጠ ሌላ ሃይማኖት የለም፡፡ ይሄንን ያልኩት እኔ አይደለሁም የእግዚአብሔር ቃል እንጂ፡፡ “አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት” ኤፌ. 4፤5 ይህች አንዲት ሃይማኖት ከአዳም ጀምሮ ነበረች እስከ ዓለም ፍጻሜም ትኖራለች፡፡ ክርስትናና ይሁዲነት (ሐዲስ ኪዳንና ብሉይ ኪዳን) ወይም ሐዲስና ኦሪት በአንዲቷ ሃይማኖት ውስጥ ያሉ ኪዳናት ናቸው እንጂ ሃይማኖቶች አይደሉም፡፡
የኢየሱስን ስም ስለጠሩ እውነት እንዳይመስልሽ የትኛውን ኢየሱስ እንደሚጠሩ አላወቅሽም፡፡ አውሬውን ጨምሮ ብዙ ሐሰተኞች ኢየሱሶች አሉና፡፡ ይህ እንደሚሆን እራሱ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ኢየሱስ አስቀድሞ ተናግሯል፡፡ የዘመኑ ፍጻሜ ሲቃረብ ብዙዎች ሐሰተኞች መምህራን በየ እልፍኙ የሚሰብኩላቸው ሐሰተኞች ኢየሱሶች ሐሰተኞች ክርስቶሶች ይመጡ ዘንድ እንዳላቸውና ከእነሱም እንድንጠበቅ አስጠንቅቆናል፡፡ ማቴ. 24፤1-28
ቅዱስ ጳውሎስም “ የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሯቹህን ዋኖቻቹህን አስቡ የኑሯቸውንም ፍሬ እየተመለከታቹህ በእምነት ምሰሏቸው ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ እስከ ዘለዓለምም ያው ነው ልዩ ልዩ ዓይነት በሆነ በእንግዳ ትምህርት አትወሰዱ፡፡ ልባቹህ በጸጋ ቢጸና መልካም ነው እንጂ በመብል አይደለም በዚህ የሚሠሩባት አልተጠቀሙምና ” ዕብ. 13፤7-9 እናም እኅቴ የትንቢት መፈጸሚያ አትሁኝ አዲስ ኢየሱስ የለም ካለም ሐሰተኛው አውሬው ነውና ልብ አድርጊ፡፡ እኅቴ ወ/ሮ ሚሊ ዛሬ የክርስቲያን ሃይማኖት ነኝ የሚሉት ብቻ 33000 ደርሰዋል፡፡ እያንዳንዳቸው ስለ ኢየሱስ ማንነት የሚናገሩት አንዱ ከሌላው የተራራቀ የተለያየ ነው፡፡ አንደኛው ኢየሱስ እንደኛ ሰው ነው በመልካም አገልግሎቱ ተሾመ ሲለው ሌላኛው አማላጅ ነው፣ ሌላው ሚካኤል ነው ሲለው ሌላኛው አንድ ገጽ ነው፣ አንዱ ሁለት ባሕሪ ነው ሲለው ሌላኛው በመንፈስ እንጂ በአካል አልተነሣም ሲል እንዲህ እንዲህ እያሉ ሐሰተኞችን ኢየሱሶች ክርስቶሶች ይሰብካሉ፡፡ ቃሉ እንዳለው ከነዚህ ውስጥ አንዱ ብቻ ከሆነ ትክክሉ 32999ኙ ሐሰተኞችና የጥፋት የሞት መንገዶች ናቸው ማለት ነው፡፡
የእግዚአብሔር ቃል ስለ እነዚህ ሐሰተኞች ሲናገረን “ ነገር ግን ወንድሞች ሆይ እናንተ የተማራቹህትን ትምህርት የሚቃወሙትን መለያየትንና መሰናከያን የሚያደርጉትን ሰዎች እንዳትመለከቱ እለምናቹሀለሁ፡፡ ከእነሱ ዘንድ ፈቀቅ በሉ እንደነዚህ ያሉት ለገዛ ሆዳቸው እንጂ ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ አይገዙምና በመልካምና በሚያቆላምጥ ንግግርም ተንኮል የሌለባቸውን ሰዎች ያታልላሉ” ሮሜ 16፤15-23 “እንደነዚህ ያሉ ሰዎች የክርስቶስን ሐዋርያት እንዲመስሉ ራሳቸውን እየለወጡ ውሸተኞች ሐዋርያትና ተንኮለኞች ሠራተኞች ናቸውና፡፡ ይህም ድንቅ አይደለም ሰይጣን ራሱ የብርሃንን መልአክ እንዲመስል ራሱን ይለውጣልና እንግዲህ አገልጋዮቹ ደግሞ የጽድቅ አገልጋዮች እንዲመስሉ ራሳቸውን ቢለውጡ ታላቅ ነገር አይደለም፡፡ ፍጻሜያቸውም እንደ ሥራቸው ይሆናል፡፡ 2ኛ ቆሮ. 11፤13 እያለ ስለማንነታቸው ቁልጭ አድርጎ በግልጽ ጽፎባቸዋል፡፡
እኅቴ ወ/ሮ ሚሊ እባክሽን ንቂ አትታለይ “ መንፈስ ግን በግልጥ በኋለኞቹ ዘመናት አንዳንዶች የሚያስቱ መናፍስትንና በውሸተኞች ግብዝነት የተሰጠውን የአጋንንት ትምህርት እያዳመጡ ሃይማኖትን ይክዳሉ” ብሏል 1ኛ ጢሞ. 4፤1-2 በእርግጥ አንች ቃሉ እንዳለው አስመሳዮች በመልካምና በሚያቆላምጥ ንግግር ሲደልሉሽ እውነት መስሎሽ ይሆናል መናፍቅ የሆንሽው፡፡ ያለው እውነታ ግን ይሄው ነው፡፡ ሃይማኖት ዛሬ በኔና በአንቺ ዘመን የመጣ የተፈጠረ እንዳልሆነ ብታስተውይ ብቻ፤ ምንም ዓይነት መጽሐፍ ቅዱሳዊ ዕውቀት ባይኖርሽ እንኳን ለመንቃት ላለመታለል በቻልሽና ዛሬ በኛ ዘመን በየቀኑ ማንም ቀባዣሪ ሐሰተኛ በድፍረት ለራሱ እንደሚመቸው አድርጎ አጣሞ እየተረጎመ የምንትስ ቤተክርስቲያን እያለ በየ አዳራሹ እየለጠፈ የሚለፈልፈው ሁሉ አዳዲስ በመሆናቸው ብቻ ከላይ እንደጠቀስኩልሽ የእግዚአብሔር ቃል ሁሉ በኋለኛው ዘመን ይመጣሉ ተጠንቀቁ እያል የገለጻቸው የአውሬው አገልጋዮች ሐሰተኞች መምህራንና ሐሰተኞች ነቢያት መሆናቸውን ማወቅ መረዳት በቻልሽ ነበር፡፡
“እግዚአብሔር እንዲህ ይላል በመንገድ ላይ ቁሙ ተመልከቱም የቀደመችውንም መንገድ ወዴት እንደሆነች ዕወቁ መልካሚቱ መንገድ ወዴት እንደሆነች ዕወቁ በእርሷም ላይ ሂዱ ለነፍሳቹህም ዕረፍትን ታገኛላቹህ እነሱ ግን አንሄድባትም አሉ” ኤር. 6፤16 “የመጀመሪያዋን እምነት እስከመጨረሻው አጽንተን ብንጠብቅ የክርስቶስ ተካፋዮች ሆነናልና” ዕብ. 3፤14 ይላል ቃሉ እኅቴ ወ/ሮ ሚሊ እውነት መዳን ከፈለግሽ ወደ መጀመሪያዪቱ ወደ ቀዳሚዋ ወደ ጥንታዊቷ ክርስቶስም በደሙ ወደ ዋጃት ወደ እውነተኛዋ ሃይማኖት ነይ፡፡ የኢየሱስ ምስክር ያለንና የመዳን ተስፋ የተሰጠን እኛ የቅድስት ብጽዕት ድንግል ማርያም ልጆች ነን “ ዘንዶውም በሴቲቱ ላይ ተቆጥቶ የእግዚአብሔርን ትእዛዛት የሚጠብቁትን የኢየሱስም ምስክር ያላቸውን ከዘሯ የቀሩትን ሊዋጋ ሔደ በባሕርም አሸዋ ላይ ቆመ” ራዕ. ዮሐ. 12፤17
እኅቴ መዳን ከፈለግሽ ብቸኛው የመዳኛ መንገድ ይሄው ነው የዮሐ. ወንጌል 19፤26-27 ላይ እንደተገለጸልን የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀሉ በመከራ ላይ ሆኖ እየቃተተ በሚወደው ሐዋርያ በዮሐንስ ወንጌላዊ አማካኝነት የተሰጠችንን እናትነቷንና ልጆቿ ተደርገን የመቆጠር የአምላክ ስጦታ ወደሽ አምነሽ አክብረሽ ተቀብለሽ ከዘሯ ተቆጠሪ ከዚህ ውጪ መዳን የምትችይበት መንገድ የለም፡፡
እኅቴ ሚሊ ምንም እንኳ ስለ ክርስቶስ ፍቅር መቀኘቱ አስፈላጊ ቢሆንም እንዲህ ፍቅሩ ካለሽ ልታደርጊው የሚገባሽን ነግሮሻል “ እኔን መከተል የሚወድ ቢኖር ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሰክሞ ይከተለኝ ” ማቴ. 16፤24 ለዚህም ነው ሐዋርያት “ወደ እግዚአብሔር መንግሥት በብዙ መከራ እንገባ ዘንድ ያስፈልገናል” ያሉት የሐዋ. ሥራ 14፤22 ስለዚህም በምቾትና በድሎት በመሽሞንሞን በመቀማጠል አይደለም ራስሽን ጣዪ መስቀሉን (መከራውን መራብ መጠማቱን በድካም በእንግልት ስለ ስሙ ስለ ክብሩ ስለ ፍቅሩ መሰቃየቱን ወዘተ.) በመሸከም በመፈጸም ነው የክርስቶስ የሚኮነው እሺ? መንፈሳዊነት ማለትም ይሄ ነው እንጂ የሥጋን ምኞትና ምቾት መጠበቅ መከተል አይደለም ዓለማዊነት ማለት እሱ ነው፡፡ አንቺ የምታመልኪበት ድርጅት ይሄንን የክርስቶስ ቃል በመቃወም ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጪ በሆነ መንገድ ስለ ክርስቶስ ስለ ፍቅሩ ስለ ክብሩ መከራ መቀበልን አይቀበሉም፡፡
ሐዋርያው ያዕቆብ ስለ እነዚህ ሲናገር “ ወንድሞች ሆይ እምነት አለኝ የሚል ሥራ ግን የሌለው ሰው ቢኖር ምን ይጠቅመዋል? እምነቱስ ሊያድነው ይችላልን?….ከነፍስ የተለየ ሥጋ የሞተ እንደሆነ እንዲሁ ደግሞ ከሥራ የተለየ እምነት የሞተ ነው ” ያዕ. 2፤ ብሎሻልና ልብ በይ ሃይማኖት እንዲህ ፌዝ አይደለምና ተጠንቀቂ፡፡ ጾምን በመጥላት ብቻ መናፍቅ የሆነ ሰው አውቃለሁ፡፡ መናፍቅ በመሆን ጾም ጸሎት ስግደትና የተለያዩ መንፈሳዊ ተግባራትን ማድረግ ሳያስፈል ባቋራጭ መጽደቅ የሚቻል ስለ ሚመስላቸው፡፡ “ሙሽራው ከእነሱ የሚወሰድብት ወራት ይመጣል በዚያ ጊዜም ይጾማሉ” ማቴ. 9፤15 “ይህ ዓይነት ክፉ መንፈስ ግን ከጸሎትና ከጾም በስተቀር አይወጣም” ማቴ. 17፤14-21
“በጠበበው ደጅ ግቡ ወደ ጥፋት የሚወስደው ደጁ ሰፊ መንገዱም ትልቅ ነውና ወደ እሱም የሚገቡ ብዙዎች ናቸው፡፡ ወደ ሕይዎት የሚወስደው ደጁ የጠበበ መንገዱም የቀጠነ ነውና የሚያገኙትም ጥቂቶች ናቸው” ማቴ. 7፤13-14 እርግጠኛ ነኝ እንደብዙዎቹ የአንቺ እምነት ተከታዮች ሁሉ የሥጋ ፈቃድሽን የሥጋ ምኞትሽን ለመጠበቅ ማለትም ላለመጾም ላለመጸለይ ላለመስገድ በስሙ መከራ ላለመቀበልና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ባልሆነ መንገድ አንድ ጊዜ በጸጋው ድኛለሁ አያስፈልግም እያሉ እራሳቸውን በማታለል ከእነኝህ ግዴታ ከሆኑ መንፈሳዊ ሥራዎች ለመራቅ ብለሽ ላለ መፈጸም ላለመገዛት ብለሽ ካልሆነና በየዋህነት መስሎሽ ተታለሽ ከሆነ መናፍቅ የሆንሽው እውነቱን ተረድተሸ ለመመለስ እስካሁን የነገርኩሽ ቃል በጣም ከበቂ በላይ ነው፡፡ ነገር ግን ለእግዚአብሔር በጾም በጸሎት በስግደት ላለመገዛት፣ ጌታን በእነዚህ ላለማክበር፣ ጾም ጸሎት ስግደትን በመጥላት ሆድሽን ወደሽ ሳትጾሚ ለመኖር፣ ላለመጸለይ፣ ላለመስገድ፣ ስለ ፍቅሩ ስለ ስሙ ስለ ክብሩ ወደሽና ፈቅደሽ ፈልገሽ የተለያዩ መከራዎችን መቀበልን (መስቀሉን መሸከምን) ሥጋን የማድከም መንፈሳዊ ሕይዎትን ጠልተሽ የሥጋ ፈቃድሽን የሥጋ ምኞትሽን የሥጋ ምቾትሽን ለመጠበቅና ዓለማዊ ለመሆን፣ ጹሚ ጸልዪ ስገጂ የተለያዩ መንፈሳዊ ተግባራትን እያደረግሽ ስለ ክርስቶስ መከራ ተቀበዪ የሚልሽ ሳይኖር “አንድ ጊዜ በጸጋው ድኛለሁ” እያልሽ እራስሽን በማጃጃል እንደፈለግሽ ሆነሽ ልጓም እንደሌለው ፈረስ እየፋነንሽ ለመኖር ከሆነ የሄድሽው እኔ አይደለሁም እሱ ራሱ ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ወርዶ ቢነግርሽ እንደማትሰሚው እርግጠና ነኝ ፈልገሽ የሄድሽው እሱን አይደለምና፡፡
እኅቴ እንዲያው ሌላው ሁሉ ይቅር እነዚህ ሃይማኖት ነን ባይ ድርጅቶች እኮ በሚገባ እንምታውቂው ሁሉ ግብረሰዶምን ተቀብለው ሥርዓት እየፈጸሙ ወንድን ከወንድ ሴትን ከሴት የሚያጋቡ እርኩሶች ናቸው፡፡ የሃይማኖት መሪዎቻቸውም ይሄንን ጸያፍ እርኩሰት የሚፈጸሙ መሆናቸውን በግልጽ በአደባባይ ይናገራሉ፡፡ ሀገር ውስጥ ያሉት የእነዚህ እርኩሶች ቅርንጫፎች መሆናቸውንና ያቋቋሟቸው ወይም የመሠረቷቸውም እነዚሁ እንደሆኑ ታውቂያለሽ፡፡ ስም መጥቀስ ሳያስፈልገኝ ከዐሥር ዓመታት በፊት አንድ የእናንተ የእምነት ድርጅት መሪ “ግብረ ሰዶማዊ የሆነ ሰው የእኛ አባል መሆን ይችላል” ብለው መግለጫ ሰጥተው ከሀገራችን ባሕልና ሕግ የሚጻረር አቋም በመሆኑ ውዝግብ ተነሥቶ እንደነበር አስታውሳለሁ፡፡ እንግዲህ ይሄንን ሁሉ ጉድ እያየሽ እንዴት ሃይማኖት ነው እድንበታለሁ ብለሽ ልትኖሪበት ቻልሽ? ይሄ ሁሉ ጉድ የሚሠራባቸው መንፈስ የዲያብሎስ መንፈስ እንደሆነ አያመለክትሽም? እንዳታስተውዪ ያደረገሽ የክፉ መንፈስ አዚም ነውና ክርስቶስ ይስበርልሽ፡፡
አብሶ ደግሞ ሰው ኢትዮጵያዊ ሆኖ መናፍቅ ሲሆን እጅግ የሚገርም ነገር ነው እኛ እኮ ልጆቹ ሕዝቡ እንደሆንን በቃሉ በአንደበቱ የመሰከረልን ክቡር ሕዝብ ነን “የእስራኤል ልጆች ሆይ እናንተ ለኔ እንደ ኢትዮጵያ ልጆች አይደላቹህምን ይላል እግዚአብሔር” ትን. አሞ.9፤7 ከእግዚአብሔር ልጅነት ነው የኮበለልሽው ተመለሽ ተመለሽ ተመለሽ “በፊቱ ኢትዮጵያ ይሰግዳሉ ጠላቶቹም አፈርን ይልሳሉ” መዝ.71፤9 ተብሎ እግዚአብሔርን አምላኪነታችን የተጻፈልን የተመሰከረልን ሕዝብ ነን፡፡ እኛ ኢትዮጵያዊያን በሁለቱም ኪዳናት አስቀድሞም በሕገ ልቡና እግዚአብሔርን ያመለክን በዓለም ብቸኛ ሕዝብ እንደሆንን ታውቂ ይሆን? ታዲያ እኛ ነን ለሌላው መመስከር ያለብን ወይስ ሌላው ለእኛ? ማንም ከእግዚአብሔር ጋራ ምንም ዓይነት ትውውቅ ያልነበረው አረማዊ ሁሉ ያውም ለእኛ ምንም የማለት ሞራላዊም ሆነ መንፈሳዊ ብቃት አለው ብለሽ ታምኛለሽ? ሲጀመር የእነዚህ ሰዎች ዓላማ ሰውን ሃይማኖተኛ ማድረግ አይደለም፡፡
ታሪክን ታውቂ እንደሆን ሃይማኖትን ሽፋን አድርገው ገብተው ለቅኝ ግዛት መሰለልና ዜጎች ለሀገራቸው ያላቸውን ፍቅር በማሳጣት፣ ማንነታቸውን በማስካድ ለቅኝ ግዛት ማመቻቸት ነበር፡፡ አንጋፋው የኬንያ መሪ ጆሞ ኬንያታ ያሉትን አልሰማሽም “ ሃይማኖትን እንስበክላቹህ ብለው መጽሐፍ ቅዱስ ይዘው ገቡና ሰበኩን ስትጸልዩም አንገታቹህን ደፍታቹህ ዐይናቹህን ጨፍኑ አሉን እኛም እንደዚያው አደረግን ዐይናችንን ገልጠን ቀና ስንል ግን መሬታችንን ሁለ ነገራችንን ወስደውት በእጃችንም ላይ ካቴና ገብቶ የእነሱ ባሪያ ሆነን እራሳችንን አገኘነው” ብለው ነበር፡፡
ዛሬም ቢሆን ቅኝ ግዛት መልኩን ቀየረ እንጅ አልቀረምና እናንተ ላይ ሲንጸባረቅ እንደምናየው ሁሉ ዓላማቸውና ተግባራቸው ይሄው ነው፡፡ ከእነሱ ጋራ ስትተባበሪ ለሀገርሽ ለታሪክሽ ለሕዝብሽና ለማንነትሽ ጠላት እየሆንሽ እንደሆነ ተረጂ፡፡ ከእነዚህ ወገኖች ጋራ ኖረሽ ዐይተሽ እንደተረዳሽው ያላቸው አቋምና ስሜታቸው ሁሉ ፀረ ኢትዮጵያ ነው፡፡ የሀገር ፍቅር ስሜት የሚባል ነገር ጨርሶ የላቸውም፡፡ እንዲህ ሆናቹህ ለመቀረጻቹህ የእነዚያ ባዕዳን ሰባኪዎቻቹህ ሚና ሙሉ ድርሻ አለው፡፡ ለባሕላችን ለማንነታችን ለቅርሶቻችን ለእሴቶቻችን ሁሉ ዴንታ የላቹህም ብቻ ሳይሆን ለማጥፋትም ታጥቃቹህ ትሠራላቹህ፡፡ እንደዜጋ እንደ ኢትዮጵያዊ የራሳቹህ እንደሆነ አይሰማቹህም፡፡ ይሄ ባንዳነት ነው ከዚህ የከፋ ባንዳነት የለም፡፡ እናም ከሁለቱም በኩል በሃይማኖቱም በፖለቲካውም ፋይዳና ትክክለኝነት መሠረት የሌላቹህ የጥፋትና የክህደት ማዕከላት ናቹህ፡፡ ለአንድ ዜጋ ከዚህ በላይ ሞት አለው ብየ አላስብም፡፡
እኅቴ ወ/ሮ ሚሊ ኢትዮጵያዊነትሽን ማንነትሽን ስርሽን የምትወጅው የምታከብሪውና የምትኮሪበትም ከሆነ ውጪ ከእነሱ ተለዪ ራቂ ወደማንነትሽ ተመለሺ፡፡ በምንም መመዘኛ ባንዳነት ክህደት፣ ውርደት፣ ሞት እንጅ ኩራት ክብር አይደለምና፡፡ በእውነት እንዲህ በመሆንሽ ልታፍሪ ይገባል እራስሽን ነው ያዋረድሽው፡፡ ለራስሽ ያለሽን ዝቅተኛ ግምት ነው ያሳየሽው፡፡ ይሄ ሁሉ ጉድ እያለ ማስተዋል ተስኖሽ በዚህ ውስጥ መቆየትሽ መቀጠልሽም ያለሽን ደካማ የብስለትና የማስተዋል የንቃት ደረጃና ብቃት ያሳያል፡፡ ያንችን ብቻ ሳይሆን እዚያ ካምፕ ውስጥ ያሉ ወገኖቻችንንም ሁሉ ነው፡፡ በዚህ ያላፈርሽ በሌላ በምንም ነገር ልታፍሪ አትችይም፡፡ ከላይ እንደጠቀስኩልሽ (ትን. አሞጽ 9፤7) ኢትዮጵያዊነት ማለት የእግዚአብሔር ልጅነት ማለት ነው፡፡ ወደ እግዚአብሔር ልጅነትሽ ተመለሽ፡፡ ኢትዮጵያዊነትሽን ጠብቀሽ የእግዚአብሔር ልጅ እንደሆንሽ ጸንቶ የመኖር እናት አባቶቻችን የጣሉብሽን አደራ መጠበቅ መወጣት ይኖርብሻል፡፡ ተመለሺ ተመለሺ ተመለሺ፡፡
እኅቴ ይህቺ ሃይማኖት ብቸኛዋ የእውነት መንገድ እንደመሆኗ መጠን ሰይጣን እጅግ ይፈታተናታል፡፡ ከዚህ የተነሣ ምናልባት አንዳንድ ደስ የማያሰኝ ነገር ብታዪ ቢያጋጥምሽ ወደ እግዚአብሔር እያመለከቱ ያንን ጠንክሮ መዋጋት ነው እንጅ መጥፋቱ መውጣቱ መፍትሔ አይደለም፡፡ እባክሽን እኅቴ ይሄ የሞትና የሕይዎት የጽድቅና የኩነኔ ጉዳይ ነውና እንደቀላል እንደዋዛ እንደ ቀልድ አትይው፡፡ ከዚህ በላይ ሊያሳስብሽ የሚገባ ነገር ሊኖር አይገባም፡፡ ከሕይዎት በላይ ምን ሊያሳስብ የሚገባ ነገር ሊኖር ይችላል?

ለማንኛውም እኅቴ እውነቱ ይሄው ነው ከእነዚህ ሰዎች ጋራ እንደመኖርሽ የታዘብሽው ብዙ ሌሎች ነገሮች ይኖራሉ ብየ አምናለሁ፡፡ እስኪ ልብ ብለሽ ተመልከቻቸው ጤነኞች ናቸው? የሥነ ልቡና ችግር ያለባቸው ንኮች አይደሉም? የቅድስት ድንግል ማርያም ልጅ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ልቡናሽን ያብራልሽ እውነትን ይግለጥልሽ ከሞት ከጨለማ ከአውሬው እጅ ይታደግሽ፡፡ አሜን! አሜን! አሜን!
amsalugkidan@gmail.com
እዉነትህ ነዉ ወዳጀ እዉነት በሆድ ይዘዉ ለገንዘብ ሲሉ ሀሰትን ከሚሰብኩ አዉሬዎች የቅድስት ድንግል ማሪያም ልጅ መደሀኒት አለም ይጠብቀን አሜን!!!
ትምክህት 101… ደሞ ሀይማኖት መስበክ ጀመራችሁልኝ… kikiki
Tkkl blehal bzu sewoch emnetachewn yemikeyrut lebr new
Betam rikashi kalatin bemetekemih mamenetih tawukol
Seali amesalu, TSEHUFEHEN anebebkut. ye mejemeriyaw 5 anqtseoch(paragrpahs) betam arif neberu. enem bante esmamalehugn. ye lelawun sew haymanot meneqef ene becha tekekele negn, be leleoch beyahmanot west yalu sewoch behatiyat new yeminorut be hatiyat new malet alemebsel new. Haymanot science aydelem. ye emenet guday new ke lib gar becha yemigenagn. leleawun mefred ayegebam. lezih new i agree only in the first 5 pargraphs yalkeh. keza behuala yetsafekew gin, ante yewekeskat setyo yaderegechewen new antem ayderkew. tadiya yanet ena yesua liyunet mindenew. esua orthodox haymanoten ankuasheshech, ante degmo ke orthodx wechi yaluten hulu ankuasheshek. RESPECT!
Well said… thanks bro. It is a must read .. those of you who are wasting your time through the bad spirit spread by wealth seeker pastors, take your time to read and return to the truth. God bless all.
very impressive!! God bless
e/r yimarik !besimet sayhon beslet maletim bewinet lay yetemeserete neger bintsif tiru new lemanignawim bible anbib lemetechet sayhon lemedan.
Nothing spritual in your post. Though, you qoute from the Bible not in its full context. You used Bible verses only for your hatred politics. You are hatred filled politician not the disciple of Jesus who preached love in word and did. The way to salivation is not religion but Jesus who proclaimed Himself so. ኢየሱስም፦ እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም
ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።
Jhon 14: 6
በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት
እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር
አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ
ወዶአልና። Jhon 3:16
You are only accuser which is Devils’ behavior according to the Bible. You are hattred filled that is typical to Satan. Your objective is purely politics as I can see. Protestant christians are protesters against those are contrary to Gods’ Word. We love our country and our fellow brothers regaedless of their differences in religion, race etc. Don’t you know in Ethiopia, there are protestants who are beaten even killed for holding Truth and siding public in the former regime. Come out of darkness and be man of peace. Don’t accuse people for their religious prefferences.
God is Love!
You do not understand @ Misgana, those all proverbs (quotations) are not mine, the proverbs are God’s word. So you are not blaming me, you are blaming God. Please read again and again until you got understand please? I am not the one who said them false prophet, gluttons, devils, disciples of devil, dead faith etc.
Do you believe in bible? If you say yes, so how you reject the word “one Jesus, one Faith, one Baptism” Eph.4:5 and the other quotations I quoted in the article? Please, read attentively forget your early thinking and wrong understanding about the Lord Jesus and Faith (Religion) .
Yes indeed God is love, but you haven’t the real God. Because what you believe about God and his identity is wrong. I never hate any one, but I hate their bad works and habits as the Lord Jesus Christ expect me to do. So I condemn the Heresies acts (preaching homosexuality and others) and I avoid them as I should be as a Christian. The word of God ordered me to do so. Is that hatred? You do not understand this is not about ethical case this is about religion, this is about Jesus Christ not about something another. You are protesting the one Lord (Jesus) …. Ok? you have no unity even among your selves (protestant) about many things not only about Jesus, you create new new Jesus every day. This is ridiculous. Do not try denying the truth, do not make yourself the accomplishment of prophecy, do not cheat yourself, wake up brother?
“I am the way, the truth, and the life. No one comes to the Father except through Me.” Yes that is undeniable. I never said there is another way of salvation. What I have been wrote is about the Way, the Faith, the Religion that makes us to find the real Jesus Christ OK? And now I need to quote this Lord Jesus word “He who receives you (his holy disciples) receives Me, and He who receives Me receives Him who sent Me. He who receives a prophet in the name of a prophet shall receive a prophet’s reward. And He who receives a righteous man in the name of a righteous man shall receive a righteous man reward. And who ever gives one of those little ones only a cup of cold water in the name of a disciple, assuredly , I say to you, He shall by no means lose his reward” Matt. 10:40-42 this means He who do not receives them (his holy disciples) do not receives Him. Haven’t you heard that Lord’s word before? I doubt it, you have nothing in your hands.
“ remember those who rule over you, who have spoken the word of God to you, whose faith follow, considering the out com of their conduct. Jesus Christ is the same yesterday, today, and forever. Don’t be carried about with various and strange doctrines. For it is good that heart be established by grace, not with foods which have not profited those who have been occupied with them.” Heb. 13:7 you are protesting that word of God.
one Jesus Christ!
Amsalu
“(ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው)” መቀየር የሚያስፈልገው ራስን ወይስ ሃይማኖትን? በማለት ላቀረብከው ሃሳብ ነው ምላሽ የሰጠሁህ
የሠዓሊነት ማዕረጉ ከስነመለኮት ትንተና ጋር ያለው ግንኙነት አልታይ ቢለኝም ማስታወቂያ ካልሆነ ማለቴ ነው ለማስተካከል የተፈለገውን ሃሳብ በሌላ ጠብአጫሪ ቃላቶች ማስተካከል መፈለግ አስገራሚ አድርጎብኛል..ለምሳሌ “…ሆን ተብሎ ለማጥቃት የሚሰነዘሩ እኩይና አጥቂ ቃላቶች ናቸው እንጂ፡፡ እነዚህ ሰዎች ማንንም ማጥቃት ሳያስፈልጋቸው ፕሮቴስታንት (ተቃዋሚ) ሆንኩ በማለት ያላቸውን ለውጥ መግለጥ የሚችሉበት ዕድል ነበር፡፡ በጣም የሚገርመኝ ነገር ቢኖር የብዙኃን መገናኛዎቹ ለእነዚህ ሰዎች እንዴት ይሄንን ጥቃት ለመፈጸሚያ መገልገያ መጠቀሚያ ለመሆን እንደሚፈቅዱና ጥቃቱን እንደሚያስተናግዱ ነው፡፡…” መገናኛ ብዙሃን ማለት የትኛውን ሃሳብ ብቻ ማስተናገድ አለባቸው…ፕሮቴስታንት የሚለውን ስያሜ እራሳቸው የሚጠሩበት ነው ወይስ አንተን መሰሎች የሚጠሩበት ነው?ማወቅ ከፈለክ ግን ወንጌላዊያን ክርስቲያኖች ብለው ነው ራሳቸውን የሚጠሩበት፡፡
መቼም አቃቤ እምነት ለመሆን ስለምትጥር .መቼም ምኞትህ ጥሩ ቢሆንም .ያለ በቂ መፍጻሃፍ ቅዱሳዊ አውድና ሹመት ያው እንደገለጽከው በሰዓሊነት..መጽሓፍ ቅዱስ ስዕል አይደለም.. በቂ ጥናት የሚፈልግ ሲሆን ይህ የመደዴ ዘመን አይደለም እና አንዳንድ ጉዳዮች ላስታውስህ፡፡
….ይሄንን ያልኩት እኔ አይደለሁም የእግዚአብሔር ቃል እንጂ፡፡ “አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት” ኤፌ. 4፤5 ይህች አንዲት ሃይማኖት ከአዳም ጀምሮ ነበረች እስከ ዓለም ፍጻሜም ትኖራለች፡፡ ክርስትናና ይሁዲነት (ሐዲስ ኪዳንና ብሉይ ኪዳን) ወይም ሐዲስና ኦሪት በአንዲቷ ሃይማኖት ውስጥ ያሉ ኪዳናት ናቸው እንጂ ሃይማኖቶች አይደሉም፡፡
ይህንን ያልኩት እኔ አይደለሁም… ማን ነው ታዲያ…አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት…የኤፌሶን ጸሓፊ አንዲት ነበረች አንዲት ትናራለች ነው ያለው? ይህ መጽሓፍ ቅዱስን ሳይማሩ ለማስተማር የሚሞክሩ ደፋሮች አተረጓገጎም ነው፡፡ ባንተ አተረጓገጎም ይህን ጽሁፍ በተጻፈበት ጊዜ የነበረችው ካቶሊክ ቤተክርስቲያን ስለነበረች የሮም ማለቴ ነው እኔ ባለቤቱ ነኝ ትለው ነበርና ያቺ አንዱዋ እኔ የምላት ነች ለማለት ትጠቀምበት ነበር ግን ሊሆነ አይችልም፡፡ አሁን አንደ.ይሁንና ..አንዲት እምነት ያለው አንድነትን ለመጠበቅ ትጉ ኑሮአችሁና ትምህርታችሁ ይመሳሰል ለማለት እንጂ ያኛው ልክና ያህኛው ልክ አይደለም ለማለት የተቀመጠ አይደለም፡፡ በተጨማሪ ደግሞ ሓዋሪያው ጳውሎስ ክርስትናና ይሁዲነት አንድ ናቸው አይልም፡፡ ክርስትናና ይሁዲነት ፈጽሞ ሊታረቁ የማይችሉ እውነታዎች ናቸው ኢየሡስ አምላክ ነው እና ኢየሡስ አታላይ ነው ብሎ በማመን ያህል ያለ ልዩነት ነው ያለው የሰቀሉትም ለዚህ ነው፡፡ ብሉይና አዲስ ኪዳንም የአካልና የጥላ መካከል ያለ ልዩነት ስለሆነ አንድም አይደሉም፡፡ በአሮጌና በአዲስ መካከል ያሉ ልዩነቶች ናቸው፡፡ ኦሪት ያረጀና ወደሱም ሲዞሩ ኦሪት የሚያደርግ ሲሆን ወደ አዲስ ኪዳን ሲዞር ግን መንፈስና ጌታን ወደሆነው ወደ ክርስቶስ የሚታይበት የተባረከ መገለጥና ብርሃን የሚበራበት ማእከል መመልከት ነው፡፡
ሰዓሊውና ፈሪሳዊው ወንድሜ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አሁን አንተ ልትሙዋገትላት እንደምትፈልገው አይነት ቤተክርስቲያን አይደለችም፡፡ እንዳንተ አይነት ሳይማሩ ለማስተማር ፓለቲካውን ከእግዚአብሔር ቃል ቀላቅለው..ፓለቲካ መልካም አስተዳደርን ለማምጣት ቢነካኩት ምንም አይደለም ሰውን ለማጥቃት ለመዝረፍ ለመሳደብና ለመግደል ሰይጣናዊ ስራን ለመስራት ምሽግ የሚያደርጉበት አይደለም፡፡ ነገር ግን እውነትን በፍቅር ለመግለጽ እድሜውም ብቃትም እውቀትም ስላላት ከኦርቶዶክስ ቤተእምነት ውጪ ያለን ወንጌላዊያን ክርስቲያኖች ብንሆንም ደግሞ በአክብሮት የምንሰማት ስለሆነች ባንተ ያልተገራ ንግግር ቤተክርስቲያኑዋን አንመዝንም፡፡ እጅግ የተከበሩ እውነትን የሚያውቁ ያወቁትን የሚኖሩ የበዙባት ቤተክርስቲያን ነች፡፡ ያ ማለት ግን ክርስቶስን ሳያውቁ በውስጥዋ የሚኖሩ የሉም ማለት አይቻልም አንተ ወንድማችን በከፍተኛ ወኔ ባገኘከው እድል ያሻህን ለማለት መፈለግህን ስለምታሳየን ኢየሱስ እንዳልገባህ ቃላቶችህ ምስክር ናቸው፡፡
……ከእነዚህ ወገኖች ጋራ ኖረሽ ዐይተሽ እንደተረዳሽው ያላቸው አቋምና ስሜታቸው ሁሉ ፀረ ኢትዮጵያ ነው፡፡ የሀገር ፍቅር ስሜት የሚባል ነገር ጨርሶ የላቸውም፡፡”
ደፋሩ ፈሪሳዊው ወንድማችን የራሱን ስሜት እንኩዋን በቅጡ የማያውቀው ቢያንስ 16 ሚሊዮን የሚሆንን ቁጥር ያለው ህዝብ ሲጨረግድ ያው ያለፍርሃትና ያለሃፍረት በመሆኑ እገረምበታለሁ፡፡ የምድር ባለቤት እግዚአብሔር እስከሆነ ድረስ የማንም ስሜት የማንንም ስሜት ሊለካ ስለማይችል አሜሪካ ቁጭ ብሎ ኢትዮጵያዊ ማነው የሚል ትንታኔ ለመስጠት የበለጠ ኢትዮጵያዊ እኔነኝ ለማለት ማሰብ ያስገርማል ፡፡ ሓዋሪያት ስራ 17፤26 እያንዳንዱ የሚኖርበትን ዳርቻና የሚኖርቡትን ልክ ወሰነላቸው ስለሚል አንተ ከዳርቻው ውጪ ስለሆንክ ኢትዮጵያዊ ነኝ ልትል አትችልም ኢትዮጵያዊ ሆነህ ከእግዚአብሔር የተሰጠህን ትእዛዝ ለመፈጸም ተልከህ ካልሆነ..ያረከውን አርገህ ፈርጥጠህ ተከባብሮና ተቀባብሎ የሚኖርን ህዝብ ለመሸንሸን ማንነት ይጎድልሃል፡፡ ሰዓሊው ..በንግግር ደረጃ እራስን ከሾመው ሰአሊው መናገር ቢያስፈልግ ኢትዮጵያዊ አለመሆንህን ልነግር እችል ነበር ቢያንስ አሁን እኔ የምኖረው ኢትዮጵያ ውስጥ ስሆን ደስታዋን መከራዋን ስቃዩዋን አብሬ የእለት ከእለት ትንፋሹዋን የምምጋት ደግሞም ሓገር ማለት መሬቱ ሳይሆን ሃገር ማለት እኔ ነበርኩ! ቢያስፈልግ ኢትዮጵያዊነት መመዘኛ ነጽብ እኔ መሆኔን እገልጽልሃለሁ፡፡
ለማንኛውም መዘላበድህን ትተህ ቁጭ ብለህ አንዱን ያዘው ዘመኑ የፐሮፌሺናሊዝም ዘመን ነው፡፡
ይታደግሽ፡፡ አሜን! አሜን! አሜን!…
አሜን እግዚብሔር ማለትና አሜን ይሁን ማለት ነው፡፡ ሰው እራሱ ተነግሮ እርሱው ንግግሩ ይሁን የሚል ከሆነ ድግምት ወይም አስማት ነው ፡፡ አሜን የሚለው ቃል ስራ ላይ የሚውለው እንደእግዚአብሔር ቃል ስንናገርና …ቀጥሎም ጥያቄአችንን በራሱ በተሰጠን መመሪያ መሰረት ይሁንልን ብለን ስንጠይቅ ነው፡፡ በስሜ የምትጠይቁትን እኔ አደርገዋለሁ ሲል ጌታችን ኢየሡስ ክርስቶስ ስለተናገረ.. በኢየሠሱስ ክርስቶስ ስም ይሁንልን ማለት ነው፡፡ሸ ስለዚህ እባክህ ቁጭ ብለህ ሓገር ያቆሙ ዘመን ያሻገሩ የተከበሩና ያስከበሩ አባቶች ስላሉ ከነርሱ ተማር፡፡
አበበ ነኝ ኢትዮጵያ
አቶ አበበ በጣም ትገርማለህ እኔን ያለሞያህ በማታውቀው ነገር ዘባረክ እያልክ አንተ ብሰህ መገኘትህ ገርሞኛል፡፡ ነው ወይስ አንተ የሥነ-መለኮት ሊቅ ነህ? አዎ እንዳትለኝና ጉድ እንዳታሰኘኝ፡፡ ነገሩ ደፋሮች አይደላቹህ ትላለህ እኮ አታፍርም፡፡ ሲጀመር እኔ የሥነ-መለኮት ሊቅ ነኝ አላልኩም ቃሉ “በእናንተ ስላለ ተስፋ ምክንያት ለሚጠይቋቹህ ሁሉ መልስ ለመስጠት ዘወትር የተዘጋጃቹህ ሁኑ” 1ኛ ጴጥ. 3፤15 ይላልና ቃሉ አማኝ ሆኘ በሃይማኖት ውስጥ ስኖር ስለ አምላኬ ላውቀው የሚገባኝንና ያወኩትን ነው ለመመስከር የሞከርኩት፡፡ ይሄንን ለማድረግ የሥነ መለኮት ሊቅ መባል የግድ አይጠበቅብኝም ክርስቲያን መሆኔ በቂ ነው እሽ? በክርስቲያንነቴ ግዴታ አለብኝ፡፡
“ጳውሎስ አንድነትን ለመጠበቅ ትጉ ኑሯቹህ ትምህርታቹህ ይመሳሰል ለማለት እንጅ ይሄኛው ልክ ነው ያኛው ልክ አይደለም ለማለት አይደለም” ነበር ያልከው? የምትለው የጨነቀህ ትመስላለህ፤ እውነት አስጨንቅሀለች፤ እንዳታምን ማመን አትፈልግም ዝም እንዳትል ደግሞ የሕሊናህ ጩኸት እረፍት ነሳህ እሱን ያስታገስክ መስሎህ ምን ይሉኛል ብለህ ሳትጨነቅ ጨርሶ የማይመስልን ነገር ቀበጣጥረህ አረፍከው፡፡ ይገርማል በቃ ይህችን ታክል ናት እውቀትህ? አዎ በእርግጥ ስለማታውቅማ ነው የሳትከው ስለዚህ ለዚህ ፍየል ወዲያ ቅዝምዝም ወዲህ ለሆነው ምላሽህ መደነቅ የለብኝም፡፡ ነገር ግን እንዲህ ግልጽ ሆኖ የተጻፈን ነገር መረዳት ባለመቻልህ እጅግ መደነቄን ሳልነግርህ አላልፍም፡፡ ለነገሩ መረዳት ባለመቻልህ ላይሆን ይችላል ነገር ግን ቃሉ እንዳለው ሆድህን ወደህ እውነትን በሆድ ለውጠሀትም ሊሆን ይችላል፡፡
ጥሩ “የመጀመሪያዋን እምነት እስከ መጨረሻው አጽንተን ብንጠብቅ የክርስቶስ ተካፋዮች ሆነናልና” ዕብ. 3፤14 ይሄስ ምን ማለት ነው? ከመጀመሪያዋ በስተቀር በኋለኛው ዘመን የሚመጡት በሐሳዊያኑ ሆዳቸው አምላካቸው ክብራቸው በነውራቸው በሆኑት የተመሠረቱት ድርጅቶች ትክክል ናቸው ማለት ነው አይደል? አየ አንተ! እስኪ ጆሮህክ ክፍት አድርግና አዳምጥ? ይሄውልህ ሲጀመር እነዚህ ከ33,000 በላይ የሆኑ የክርስትና ሃይማኖት ነን የሚሉ ድርጅቶች የተለያየ የሚለያዩበት አስተምህሮ ባይኖራቸው ኖሮ ባልተለያዩም ነበር፡፡ ነገር ግን የሚያለያያቸው ነገር ስላለ ተለያዩ ቁጥራቸውም እዚህ ሊደርስ ቻለ፡፡ አቶ አበበ አንተ ስታስበው ሁሉም ስለኢየሱስ ክርስቶስ የሚያወሩት የሚያምኑት የተለያየ ሆኖ እያለ እንዴት ሁሉም ልክ ሊሆኑ ይችላሉ? ቃሉን ተወው አሌ ብለኸዋልና ነገር ግን እንዲያው በአመክንዮ (በሎጂክ) ዐይን ስታየው ሁሉም የሚያወሩት የተለያየ ሆኖ እያለ እንዴት ሁሉም ልክ ሊሆኑ ይችላሉ? ዐየህ ምን ያህል እንደደነቆርክ? ይሄ ጥያቄ እኮ ገና አፉን የፈታ ሕፃን ሳይቀር በቀላሉ ሊመልሰው የሚችለው ጥያቄ ነው፡፡ ችግርህ ገብቶኛል ሳታውቀው ቀርተህም ላይሆን ይችላል ከላይ እንዳልኩት ሆድህን መውደድህ ነው እንዳታስተውል ወይም ለምታውቀው ነገር ግን ለማትኖረው እውነት እንዳትገዛ ያደረገህ፡፡
ለማንኛውም ቃሉ በጣም ግልጽ ነው “አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት” ኤፌ.4፤5 ይሄ ማለት አንዱ ብቻ ነው ልክ ሌላኛው አይደለም ማለት አይደለም ስትል ጌታም አንድ አይደለም ብዙ ነው ጥምቀትም አንዲት አይደለችም ብዙ ናት ማለትህ እንደሆነ ገብቶሀል? ጌታንም ሐዋርያው ጳውሎስንም ውሸታም እያልክ እንደሆነስ ገብቶሀል? “በዚያ ጊዜ ማንም እነሆ ክርስቶስ እዚያ አለ ወይም እዚህ አለ ቢላቹህ አትመኑ ሐሰተኞች ክርስቶሶችና ሐሰተኞች ነቢያት ሐሰተኞች መምህራን ይነሣሉና ቢቻላቸውስ የተመረጡትን እንኳ እስኪያስቱ ድረስ ታላላቅ ምልክትና ድንቅ ያሳያሉ፡፡ እነሆ አስቀድሜ ነገርኳቹህ” ማቴ. 24፤23-25 ይሄ የጌታ ቃልና ጽሑፉ ላይ የጠቀስኳቸው ቅዱስ ጳውሎስ የአጋንንትን ስብከት እያዳመጡ ሃይማኖትን ይክዳሉ እያለ የተናገራቸው ቅዱስ ያዕቆብ ሥራ የተለረው እምነት የሞተ ነው እያለ የገለጸው እነኝህ ሁሉ ውሸት ናቸው ማለት ነዋ! እውነት ከሆኑ ደግሞ ከአንዱ በስተቀር 33,999 ኙ ሃይማኖት ነኝ ባይ አወናባጅ የአውሬው ድርጅት ሁሉ ሐሰተኛና የጥፋት መሆናቸው ግድ ነው፡፡ እነዚህ ከጊዜ በኋላ የተፈጠሩትና አሁንም በየቀኑ የየሚፈጠሩት አዳዲሶቹም ካልሆኑ ሌላ ማን ሊሆን ይችላል? ምስጋና ለእሱ ይሁንና ቃሎቹስ ውሸት አይደሉም እውነት ናቸው የአምላክ ቃል ናቸውና ይሄው በእናንተ ላይ ተፈጽሞም እያየን ነው፡፡ ጌታ እነሆ አስቀድሜ ነገርኳቹህ ያለባቹህ፣ ቅዱስ ጳውሎስ እያለቀስኩ እላቹሀለሁ ከእነሱ እራቁ ያለባቹህ እናንተ ናቹህ፡፡ ወዮ ለእናንተ ከእውነት ይልቅ ሆዳቹህ ለበለጠባቹህ ዲያብሎስን ለምታገለግሉና ለምታመልኩም፤ ጌታ በፊቱ እሳት እየነደደ ለመፍረድ ሲመጣ በፍርሐትና በመንቀጥቀጥ በማይጠቅም ለቅሶና ዋይታ በግራው ለፍርድ ትቆማላቹህና፡፡ ከግብር አባታቹህ ከዲያብሎስና ከሠራዊቱም ጋራ ወደ ዘለዓለም እሳት ትጣላላቹህ፡፡ በእርግጥ አንተም እንደ የጥፋት መልእክተኛነትህ ቃሉን እውነት ነው እንድትል አይጠበቅብህም፡፡
“ይህ ጥቅስ በተጻፈበት ወቅት የነበረችው የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ስለነበረች ካቶሊኮች ለእኛ የተነገረ ነው ይሉ ነበር” ነው ያልከው? እንዲያው ግን አታፍርም? አእላፋት በሚያዩት በሚያነቡት መካነ ድር ላይ ዝም ብለህ ጨርሶ የማታውቀውን ነገር በግምት ትቀባጥራለህ? ካቶሊኮችም ከቤተክርስቲያን በመነጠል ካቶሊክነትን ከማወጃቸው በፊት ቤተክርስቲያን አንድ እያለች የሐዋርያት አለቃ የሆነው ጌታም የመንግሥተ ሰማያትን መክፈቻ ቁልፍ የሰጠው ጴጥሮስ መንበሩ ከእኛ ነውና እኛ የበላይ ነን ይሉ ነበር እንጅ ይሄንን አንተ ያልከውን እንደማይሉ መቶ በመቶ እርግጠኛ ነኝ ምክንያቱም ቤተክርስቲያን በገጠማት አጋንንታዊ ፈተና ምዕራቦቹ አዲስ አስተምህሮ በማብጣታቸው በምሥራቅና በምዕራብ ተከፍላ የተለዩት የወጡት ምዕራባዊያኑ ካቶሊክ (የሁሉም) ነባሩ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ (ነባር፣ ቀጥተኛ) ተብሎ ስም የወጣላቸው 451ዓ.ም. በኬልቄዶኑ ጉባኤ ነው እሽ? እስከዚያ ዘመን ድረስ የዚህ የዚህ የሚባል ቅጽል ስም አልነበረም፡፡ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ብቸኛዋ ትክክለኛ ሃይማኖት ናት ብየ ስል ይሄ ስሟ ኤርሚያስ በ6፤16 ላይ ጳውሎስ በኤፌ. 4፤5 ላይና ዕብ. 3፤14 ላይ ስለ እሷ በተናገሩበት ዘመን ነበረ እያልኩ አይደለም፡፡ አታስተውልም እንጂ እዛው ላይ ገልጨዋለሁ በዚህች ሃይማኖት ውስጥ ሁለቱም ኪዳናት ጊዜያቸውን ጠብቀው ተፈጽመዋል ብያለሁ፡፡ ስለዚህ ይህች ሃይማኖት አሁን የተሰጣት ክርስቲያናዊ ሥያሜ በብሉይ ዘመንና በሐዲስም እስከ አምስተኛው መቶ ክ/ዘመን ድረስ አልነበረም ማለት ነው፡፡ ነግር ግን በየ ኪዳናቱ ዘመን በወቅቱ ያለውን ኪዳን በሚያመለክት መልኩ ስሞች ነበሯት፡፡ እነዚያም ስሞች ሁለቴ ተቀያይረዋል፡፡ ሥሟ ይቀያየር እንጅ እሷ ግን ያችው እሷ ናት አልተለወጠችም፡፡ ይህች ትክክለኛ ሃይማኖት ያለችው በአምስቱ የምሥራቅ አብያተ ክርስቲያናት (oriental Churches) ሀገራት ነው፡፡ እነሱም በኢትዮጵያ፣ በግብጽ፣ በሶሪያ፣ በአርመንና በሕንድ፡፡ በዚህ በዘመኑ ፍጻሜ ግን ከአውሬው ውጊያ ብርታት የተነሣ በአንዳንዶቹ አስተምህሯቸውን የሚለውጥ ችግር እየተፈጠረባቸው ነው፡፡
“ጳውሎስ አይሁድነትና ክርስትና አንድ ናቸው አላለም” ነበር ያልከው? እንጭጭ የሆነን ሰው ማስረዳት እንዴት አስቸጋሪ ነው ባካቹህ? እሽ ጳውሎስ የት ቦታ ላይ ነው አንድ አይደሉም ሁለቱ የማይጣጣሙ የሚቃረኑ ናቸው ያለው? ወንድሜ በኦሪት ውስጥ ሐዲስ እንደነበረች ያለ ኦሪት ሐዲስ እንደማትኖር አታውቅም? ሐዲስ ጊዜዋ ሲደርስ ለመወለድ በእናቷ በኦሪት ማሕጸን ነበረች፡፡ ኦሪትና ነቢያት ስለ መሲሑ ስለ ክርስቶስ ትንቢት መናገራቸውን፣ ሱባኤ መቁጠራቸውን፣ በተስፋ መጠበቃቸውን አታውቅም? ይሁዲነት(ኦሪት) የማን ነው? ማንስ ነው የመሠረተው? ነቢያቱ የማን ናቸው? ሕግጋቱስ የማን ናቸው? የእግዚአብሔር አይደሉምን? ሲባል ሰምተሀል፤ በእርግጥ ሙሴ በመሥፍንነቱ ለአሥተዳደር እንዲያመቸው የደነገጋቸው ሕጎች አዎ ተሽረዋል፡፡ የኃጢአት ማሥተስረያው የበግና የእርግብ ወሥዋዕትም ተሸሮ በአማናዊው በግ በኢየሱስ ክርስቶስ ተተክተዋል፡፡ አሮጌው እርሾ ማለት እነኝህ የተሻሩት ናቸው እንጅ ኦሪትና ነቢያት አይደሉም ምክንያቱም በዚያ ዘመን ለነቢያቱ ለዘለዓለም ለዘለዓለም እያለ የገባቸው ቃልኪዳኖች እንዳለው ሁሉ የዘለዓለምና የማይሻሩ ናቸውና፤ እግዚአብሔር ቃሉን የሚያጥፍ ወይም ውሸታም አይደለምና፡፡ ስለ ኦሪትና ነቢያትማ ክርስቶስ እንዳረጋገጠው “እኔ ሕግንና ነቢያትን ለመሻር አልመጣሁም ልፈጽም እንጅ ለመሻር አልመጣሁም፡፡ እውነት አላቹሀለሁ ሰማይና ምድር እስኪያልፍ ድረስ ከሕግ አንዲት የውጣ ወይም አንዲት ነጥብ ከቶ አታልፍም ሁሉ እስኪያልፍ ድረስ” ማቴ. 5፤17- 18 “ነገር ግን ከሕግ አንዲት ነጥብ ከምትወድቅ ሰማይና ምድር ቢያልፍ ያቀላል” ሉቃ. 16፤17 ነው ያለላቸው፡፡
አንተ ግን ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው ከአጋንንት በተማርከው ትምህርት “ክርስትናና ይሁዲነት ፈጽሞ ሊታረቁ የማይችሉ እውነታዎች ናቸው” ስትል ዘባረክ፡፡ “ኢየሱስ አምላክ ነው ማለትና ኢየሱስ አታላይ ነው ብሎ የማመን ያህል ልዩነት ነው ያለው የሰቀሉትም ለዚህ ነው” አልክ ለመሆኑ ይሁዲነት ወይም ኦሪት የት ቦታ ላይ ነው ኢየሱስ አምላክ አይደለም አታላይ ነው ያሉት? ይልቁንም አምላክ መሲህ እንደሚወለድና እንደሆነ የአመጻ ልጆች ግን አምላክ መሲሕ አይደለም ብለው እንደሚሰቅሉት በሞቱም አርነት እንደሚያወጣን እንደሚቤዠን ተናገሩ ተነበዩ እንጅ፡፡ ኢሳ.7፤14 ኢሳ. 53፤1-12 ኢሳ. 9፤6 መዝ. 21(22) 12-18 መዝ. 47(48)፤5 መዝ. 34(35)፤ 1-28 ወዘተ. ያንተ ችግር አታውቅም የሚገርመው ያለምንም ሐፍረት ዝም ብለህ በግምት ትዘባርቃለህ፡፡ የቀያፋና የሐና ጉባኤ ማለት ይሁዲነት ወይም ኦሪት ማለት አይደለም እሽ? ስለ አንተ እኔ አፈርኩልህ፡፡ ወይ አልገባኝም አላውቅም ብሎ መጠየቅ አንድ ነገር ነው፡፡ ዐውቃለሁ ብሎ ግን ጨርሶ የማያውቁትን ነገር መዘባረቅ ነውር ነው ያዋርዳልም፡፡
አቶ አበበ ፕሮቴስታንት(ተቃዋሚ) የሚለውን ስም አንተ ነህ ወይ የሰጠኸን ነው ያልከኝ? በጣም የሚገርም ነው፡፡ ባይሆን ስማችን ማንነታችንን ግብራችንን ሥራችንን እያሳበቀብን ስለሆነ ቀይረነዋል በለኝ እንጅ በመላው ዓለም መጠሪያ ስማቹህ እንደሆነ ጭራሽ እኔ ልንገርህ? ይሄ የታወቀ ነገር አይደለም እንዴ? አቶ አበበ እባክህን የምታስተባብለውን ነገር እንኳን ለይተህ ዕወቅ? ያለብህ የክህደት አባዜ ሁሉም የሚያውቀውን ነገር ለመካድ ለማስተባበል ሲያስደፍርህ በግልጽ ትታያለህ፡፡ እባክህ ሰው ምን ይለኛል በል?
አቶ አበበ አሜሪካ ተሁኖ ኢትዮጵያዊ ነኝ ማለት ስለ ኢትዮጵያ መቆጨት መቆርቆር በፍቅሯ መቃጠል እንዴት ሆኖ ነው የማይቻለው? ወያኔ ነህ እንዴ? በተሰደዱ ወገኖቻችን ላይ ከባድ ጥላቻ ይታይብሀል፡፡ እንዴት ነው የምታስበው? በስንቱስ ጥሬ ሆነህ ትዘልቀዋለህ? አሜሪካ እንደምኖር እንዴት እርግጠኛ ሆነህ ለማውራት እንደደፈርክ ገርሞኛል፡፡ ይሄን ግምትህን እውነት እያስመሰልክ ማውራትህን አትተውም? ለማንኛውም እኔ የምኖረው እዚሁ ሀገሬ ኢትዮጵያ ውስጥ ነው፡፡ ለምንም ነገር ብትፈልጉኝ አለሁ፡፡
አዎ ለኢትዮጵያ ሃይማኖት፣ ባሕል፣ ታሪክ፣ ማንነት፣ መለያ ለእሴቶቻችን ሁሉ ፍቅር ተቆርቋሪነት የላቹህም ብያለሁ፡፡ የማናውቅ መሰለህ እንዴ ከኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የምትነጥቋቸውን በጎች ምንም ነገር ለማስተማር ከመሞከራቹህ በፊት የመጀመሪያ እርምጃቹህ የነበራቹህባትን ሃይማኖት፣ የነበራቹህን ማንነት በሙሉ እንዲህ እያላቹህ እርገሙ እያላቹህ ማስረገም አይደለም እንዴ? ባንዳ ብየ ስል ዝም ብየ ከምንም ተነሥቸ ወይም በጥላቻ ይመስልሀል? ነው ወይስ ይሄንን አያውቁም ብለህ ነው? አንተን ሲያስክዱህ እንዴት አደርገው ነው ያስካዱህ? ከመናፍቃን ወላጆች ተወልደህ መናፍቅነትን ከእነሱ ወርሰህ ከሆነ ይሄ እጣ አያጋጥምህም፡፡ ከአንዲቷ ሃይማኖት ወጥተህ ተነጥለህ ጠፍተህ ተጠልፈህ ከሆነ ግን የተቀላቀልካቸው ይሄ አይቀርልህም፡፡ 16 ሚልዮን (አእላፋት) ሆነናል ነው ያለከኝ? ይሄ ሁሉ በግ ተበልቷል? ለቅድስት ቤተክርስቲያን ከዚህ የከበደ ኃዘን አለ? ወዮ ይሄንን ያህል መንጋ ላስበሉት እረኞች! ምንም እንኳን አባት ያልተከለው ተክል መነቀሉ የማይቀር ቢሆንም ክርስቶስ ከሐሰት ከጥፋት ወደ እውነት፣ ከሞት ወደ ሕይዎት፣ ከጨለማ ወደ ብርሃን እንዲመልሳቹህ መጸለይ ግን ግዴታየ ነውና እጸልያለሁ፡፡
አምሳሉ