• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አካፋን አካፋ እንላለን!!!

April 28, 2013 12:13 am by Editor Leave a Comment

የጎልጉል ማሳሰቢያ፡ ይህንን ጽሁፍ የላኩልን ሰላማዊት አሰፋ ይባላሉ፡፡ ስለጽሁፉ ይዘት እኛ ከምንናገር ይልቅ አንባቢዎች የራሳቸውን ግንዛቤ እንዲወስዱ ለንባብ አትመነዋል፡፡ ጸሐፊዋን በግል ለማግኘት የሚፈልጉ ሁሉ በቀጥታ በዚህ አድራሻ ለመጻፍ ይችላሉ (a_selamawit53@yahoo.com) ይህንን ጽሁፍ አስመልክቶ በጨዋነት የአጸፋ ምላሽ ለመስጠት የሚፈልጉ ሁሉ የሚልኩልንን ጽሁፍ እንደምናትም ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ!


ሀገራችን ኢትዮጵያ በጠባብ ዘረኞች መዳፍ ስር ከወደቀች እነሆ ከሁለት አስርት አመታት በላይ ተቆጠሩ። ህዝባችንም ቢሆን በዋነኛነት በዘር እንዲከፋፈል ተደርጎ እርስ በርሱ እንዳይተማመን ይልቁንም በጠላትነት እንዲተያይ ከመደረጉም ባሻገር በፖለቲካና በማህበራዊ ጉዳይ በገዛ ሀገሩ ባዕድ እንዲሆን ተደርጓል።በኢኮኖሚውም ቢሆን ኑሮው ዕለት፥ዕለት እያሽቆለቆለ በልቶ ማደርን እንደትልቅ ፀጋ ከሚቆጥርበት ዘመነ ፍዳ ላይ ይገኛል።

የፅሑፌ አላማ ሀገራችን ኢትዮጵያ የገባችበትን አዘቅት እና ህዝቦቿ የሚገኙበትን ሰቆቃ ለመዘርዘር ሳይሆን ከዚህ አስከፊ ሁኔታ ሀገራችንና ህዝቦቿ እንዳይወጡ የየበኩላቸውን አስተዋፅኦ ከሚያደርጉ ሰንኮፎች መካከል በአንዱ ዙሪያ ያለኝን አስተያየት ለማካፈል ነው።

የወያኔን ዕድሜ ከሚያራዝሙ በርካታ ምክንያቶች መካከል ጭንጋፍ /ምቱር/ ፖለቲከኞችና ፍሬ አልባ ድርጅቶቻቸው በዋናነት ይጠቀሳሉ።

እነዚህ ጭንጋፍ /ምቱር/ ፖለቲከኞች በሀገር ቤትም ከሀገር ቤት ውጪም በተለይ በአውሮፓና በዩ ኤስ አሜሪካ ይገኛሉ።የሀገር ቤቶቹ በአብዛኛው በምርጫ ሰሞን በወያኔ ተጠፍጥፈው የሚሰሩ አልያም ራሳቸው እንደ አሸን ፈልተው ከምርጫው ጋር አብረው የሚከስሙ ሲሆን ከዛ ውጪ ያሉትም ቢሆን የህዝብ አመኔታ የሌላቸውና መዋያ ባጡ አዛውንቶች የሚዘወሩ ፍሬ አልባ ሆነው እናገኛቸዋለን።ይህ ማለት ግን በሀገር ቤት ከወያኔ ጋር እየተላተመ ብሎም መስዋዕትነት እየከፈለ የሚታገል ድርጅት የለም ማለት አይደለም።

በሌላ በኩል በህዝባችን ቁስል ላይ ጥዝጣዜን እየጨመሩ ከሚገኙት መካከል ውጪ ሀገር የሚኖሩ ነፍስ-አልባ ተንቀሳቃሽ ሬሳዎች ሲሆኑ እኒህ የጨነገፉ ፖለቲከኞች ”ኢትዮጵያን ነፃ እናወጣለን” እያሉ ፍሬ-አልባ ድርጅቶችን በማቋቋም በህዝብ ስም የሚነግዱ፣በነፃነት ስም እየማሉ ነፃ ያልወጡ፣በስደተኛ ወንድሞቻቸው ስቃይ የግል ጥቅማቸውን የሚያሳድዱ፣የሚሰርቁ፣የሚዋሹ፣ስደተኛ ሴት እህቶቻችንን የሴሰኝነታቸው ማራገፊያ የሚያደርጉ ሲሆን ”ሰው መሳይ በሸንጎ” እንደሚባለው ወድቆ በተነሳው ባንድራችን በየአደባባዩ ሲምሉ፣ስለሀገር አንድነት እና ስለህዝቦቿ ፍትህ ማጣት ሲያወሩ ኤሎሄ ከማለት አልፈን ብዕር እንድናነሳ አስገድዶናል።

ለዛሬ መነሻዬን የአውሮፓ እምብርት ከሆነችው ጀርመን አድርጌአለሁ። (በዚህ አጋጣሚ ውድ አንባብያን ሆይ! በስራ ምክንያት ዩ ኤስ አሜሪካ በየጊዜው የምሄድ በመሆኑ በአሜሪካም ያየሁትንና በቂ ማስረጃ ያገኘሁበትን በቀጣይ እትም አቀርበዋለሁ)። (ሙሉው ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የአየለ ጫሚሶ ቅንጅት ፈረሰ January 18, 2021 02:31 pm
  • ህወሓት ተሠረዘ!!! January 18, 2021 01:32 pm
  • ዓሲምባ፣ ሣልሳዊ ወያኔና ባይቶና ከመፍረሳቸው በፊት ማብራሪያ እንዲሰጡ ተነገራቸው January 18, 2021 01:00 pm
  • ቤተሰቦች አስከሬን መውሰድ እንደሚችሉ ተነገረ January 14, 2021 06:48 pm
  • ስብሃት፤ “ከሞትን ቆይተናል፤ … አሁን የቀብር ሥነ-ስርዓታችን” እየተፈጸመ ነው January 14, 2021 01:37 pm
  • “ተመልሰን እንነሳለን” ያሉት ህወሓቶች ተመልሰው ወደማይነሱበት ተሸኙ January 13, 2021 01:12 pm
  • አፋር ነፃ አውጪ (ኡጉጉሙን) ለመጠቀም የታቀደው የህወሃት ሤራ ከሽፏል January 13, 2021 01:10 pm
  • ህወሃትን ወደ ጅቡቲ ለማሻገር ሲሰሩ የነበሩ የአፋር ታጣቂዎች በሰላም ወደ ክልሉ ገቡ January 13, 2021 06:47 am
  • በታህሳስ ወር ብቻ ከ344 ሚሊየን ብር በላይ የኮንትሮባንድ ዕቃ ተያዘ January 13, 2021 06:10 am
  • የብልፅግና ፓርቲ ቀጣይ ፈተና ምን ሊሆን ይችላል? January 13, 2021 04:10 am
  • ለትምህርት እንዲሆነን January 11, 2021 01:20 pm
  • “ከተቀበሩበት የጃርት ጉድጓድ ነው ያወጣናቸው” መቶ አለቃ ስዩም ቱርቦ January 11, 2021 12:11 pm
  • የተደመሰሱና በቁጥጥር ሥር የዋሉ የወንበዴው አባላት ይፋ ሆነ January 7, 2021 01:16 pm
  • ዐቢይና መኮንኖቹ በመቀሌ፤ “ድሉ የመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው” December 13, 2020 02:36 pm
  • ወንበዴው ህወሓት ከ1.4 ትሪሊዮን ብር በላይ ዘርፎ በውጭ አገራት ባንኮች አስቀምጧል December 8, 2020 01:05 am
  • ማይካድራ – የትህነግ የዘር ማጥፋት ጥግ ቋሚ ምስክር December 8, 2020 12:57 am
  • የወልቃይት ጠገዴ እናቶች ሰቆቃ ሲታወስ December 8, 2020 12:50 am
  • የደብረጽዮን ዋሻ December 7, 2020 11:30 pm
  • ባለ ከዘራው ኮሎኔል December 7, 2020 05:15 pm
  • ሰላማዊ ሕይወት በማይጨው December 7, 2020 04:12 pm
  • ተጠርጣሪ የፌዴራልና የአዲስ አበባ ፖሊሶች የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው December 7, 2020 11:46 am
  • ከ3 ሺህ በላይ ተተኳሽ ጥይቶች በወልዲያ ጉምሩክ ሊያሳልፉ የሞከሩ 4 ግለሰቦች ተያዙ! December 7, 2020 11:18 am
  • ወንበዴዎቹ ይጠቀሙባቸው የነበሩ ተሽከርካሪዎችና የግል ሰነዶቻቸው ተያዙ December 7, 2020 10:50 am
  • ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ በሶማሌ ክልል ተመሠረተ December 7, 2020 10:31 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2021 · Goolgule