• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አካፋን አካፋ እንላለን!!!

April 28, 2013 12:13 am by Editor Leave a Comment

የጎልጉል ማሳሰቢያ፡ ይህንን ጽሁፍ የላኩልን ሰላማዊት አሰፋ ይባላሉ፡፡ ስለጽሁፉ ይዘት እኛ ከምንናገር ይልቅ አንባቢዎች የራሳቸውን ግንዛቤ እንዲወስዱ ለንባብ አትመነዋል፡፡ ጸሐፊዋን በግል ለማግኘት የሚፈልጉ ሁሉ በቀጥታ በዚህ አድራሻ ለመጻፍ ይችላሉ (a_selamawit53@yahoo.com) ይህንን ጽሁፍ አስመልክቶ በጨዋነት የአጸፋ ምላሽ ለመስጠት የሚፈልጉ ሁሉ የሚልኩልንን ጽሁፍ እንደምናትም ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ!


ሀገራችን ኢትዮጵያ በጠባብ ዘረኞች መዳፍ ስር ከወደቀች እነሆ ከሁለት አስርት አመታት በላይ ተቆጠሩ። ህዝባችንም ቢሆን በዋነኛነት በዘር እንዲከፋፈል ተደርጎ እርስ በርሱ እንዳይተማመን ይልቁንም በጠላትነት እንዲተያይ ከመደረጉም ባሻገር በፖለቲካና በማህበራዊ ጉዳይ በገዛ ሀገሩ ባዕድ እንዲሆን ተደርጓል።በኢኮኖሚውም ቢሆን ኑሮው ዕለት፥ዕለት እያሽቆለቆለ በልቶ ማደርን እንደትልቅ ፀጋ ከሚቆጥርበት ዘመነ ፍዳ ላይ ይገኛል።

የፅሑፌ አላማ ሀገራችን ኢትዮጵያ የገባችበትን አዘቅት እና ህዝቦቿ የሚገኙበትን ሰቆቃ ለመዘርዘር ሳይሆን ከዚህ አስከፊ ሁኔታ ሀገራችንና ህዝቦቿ እንዳይወጡ የየበኩላቸውን አስተዋፅኦ ከሚያደርጉ ሰንኮፎች መካከል በአንዱ ዙሪያ ያለኝን አስተያየት ለማካፈል ነው።

የወያኔን ዕድሜ ከሚያራዝሙ በርካታ ምክንያቶች መካከል ጭንጋፍ /ምቱር/ ፖለቲከኞችና ፍሬ አልባ ድርጅቶቻቸው በዋናነት ይጠቀሳሉ።

እነዚህ ጭንጋፍ /ምቱር/ ፖለቲከኞች በሀገር ቤትም ከሀገር ቤት ውጪም በተለይ በአውሮፓና በዩ ኤስ አሜሪካ ይገኛሉ።የሀገር ቤቶቹ በአብዛኛው በምርጫ ሰሞን በወያኔ ተጠፍጥፈው የሚሰሩ አልያም ራሳቸው እንደ አሸን ፈልተው ከምርጫው ጋር አብረው የሚከስሙ ሲሆን ከዛ ውጪ ያሉትም ቢሆን የህዝብ አመኔታ የሌላቸውና መዋያ ባጡ አዛውንቶች የሚዘወሩ ፍሬ አልባ ሆነው እናገኛቸዋለን።ይህ ማለት ግን በሀገር ቤት ከወያኔ ጋር እየተላተመ ብሎም መስዋዕትነት እየከፈለ የሚታገል ድርጅት የለም ማለት አይደለም።

በሌላ በኩል በህዝባችን ቁስል ላይ ጥዝጣዜን እየጨመሩ ከሚገኙት መካከል ውጪ ሀገር የሚኖሩ ነፍስ-አልባ ተንቀሳቃሽ ሬሳዎች ሲሆኑ እኒህ የጨነገፉ ፖለቲከኞች ”ኢትዮጵያን ነፃ እናወጣለን” እያሉ ፍሬ-አልባ ድርጅቶችን በማቋቋም በህዝብ ስም የሚነግዱ፣በነፃነት ስም እየማሉ ነፃ ያልወጡ፣በስደተኛ ወንድሞቻቸው ስቃይ የግል ጥቅማቸውን የሚያሳድዱ፣የሚሰርቁ፣የሚዋሹ፣ስደተኛ ሴት እህቶቻችንን የሴሰኝነታቸው ማራገፊያ የሚያደርጉ ሲሆን ”ሰው መሳይ በሸንጎ” እንደሚባለው ወድቆ በተነሳው ባንድራችን በየአደባባዩ ሲምሉ፣ስለሀገር አንድነት እና ስለህዝቦቿ ፍትህ ማጣት ሲያወሩ ኤሎሄ ከማለት አልፈን ብዕር እንድናነሳ አስገድዶናል።

ለዛሬ መነሻዬን የአውሮፓ እምብርት ከሆነችው ጀርመን አድርጌአለሁ። (በዚህ አጋጣሚ ውድ አንባብያን ሆይ! በስራ ምክንያት ዩ ኤስ አሜሪካ በየጊዜው የምሄድ በመሆኑ በአሜሪካም ያየሁትንና በቂ ማስረጃ ያገኘሁበትን በቀጣይ እትም አቀርበዋለሁ)። (ሙሉው ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule