• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አካፋን አካፋ እንላለን!!!

April 28, 2013 12:13 am by Editor Leave a Comment

የጎልጉል ማሳሰቢያ፡ ይህንን ጽሁፍ የላኩልን ሰላማዊት አሰፋ ይባላሉ፡፡ ስለጽሁፉ ይዘት እኛ ከምንናገር ይልቅ አንባቢዎች የራሳቸውን ግንዛቤ እንዲወስዱ ለንባብ አትመነዋል፡፡ ጸሐፊዋን በግል ለማግኘት የሚፈልጉ ሁሉ በቀጥታ በዚህ አድራሻ ለመጻፍ ይችላሉ (a_selamawit53@yahoo.com) ይህንን ጽሁፍ አስመልክቶ በጨዋነት የአጸፋ ምላሽ ለመስጠት የሚፈልጉ ሁሉ የሚልኩልንን ጽሁፍ እንደምናትም ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ!


ሀገራችን ኢትዮጵያ በጠባብ ዘረኞች መዳፍ ስር ከወደቀች እነሆ ከሁለት አስርት አመታት በላይ ተቆጠሩ። ህዝባችንም ቢሆን በዋነኛነት በዘር እንዲከፋፈል ተደርጎ እርስ በርሱ እንዳይተማመን ይልቁንም በጠላትነት እንዲተያይ ከመደረጉም ባሻገር በፖለቲካና በማህበራዊ ጉዳይ በገዛ ሀገሩ ባዕድ እንዲሆን ተደርጓል።በኢኮኖሚውም ቢሆን ኑሮው ዕለት፥ዕለት እያሽቆለቆለ በልቶ ማደርን እንደትልቅ ፀጋ ከሚቆጥርበት ዘመነ ፍዳ ላይ ይገኛል።

የፅሑፌ አላማ ሀገራችን ኢትዮጵያ የገባችበትን አዘቅት እና ህዝቦቿ የሚገኙበትን ሰቆቃ ለመዘርዘር ሳይሆን ከዚህ አስከፊ ሁኔታ ሀገራችንና ህዝቦቿ እንዳይወጡ የየበኩላቸውን አስተዋፅኦ ከሚያደርጉ ሰንኮፎች መካከል በአንዱ ዙሪያ ያለኝን አስተያየት ለማካፈል ነው።

የወያኔን ዕድሜ ከሚያራዝሙ በርካታ ምክንያቶች መካከል ጭንጋፍ /ምቱር/ ፖለቲከኞችና ፍሬ አልባ ድርጅቶቻቸው በዋናነት ይጠቀሳሉ።

እነዚህ ጭንጋፍ /ምቱር/ ፖለቲከኞች በሀገር ቤትም ከሀገር ቤት ውጪም በተለይ በአውሮፓና በዩ ኤስ አሜሪካ ይገኛሉ።የሀገር ቤቶቹ በአብዛኛው በምርጫ ሰሞን በወያኔ ተጠፍጥፈው የሚሰሩ አልያም ራሳቸው እንደ አሸን ፈልተው ከምርጫው ጋር አብረው የሚከስሙ ሲሆን ከዛ ውጪ ያሉትም ቢሆን የህዝብ አመኔታ የሌላቸውና መዋያ ባጡ አዛውንቶች የሚዘወሩ ፍሬ አልባ ሆነው እናገኛቸዋለን።ይህ ማለት ግን በሀገር ቤት ከወያኔ ጋር እየተላተመ ብሎም መስዋዕትነት እየከፈለ የሚታገል ድርጅት የለም ማለት አይደለም።

በሌላ በኩል በህዝባችን ቁስል ላይ ጥዝጣዜን እየጨመሩ ከሚገኙት መካከል ውጪ ሀገር የሚኖሩ ነፍስ-አልባ ተንቀሳቃሽ ሬሳዎች ሲሆኑ እኒህ የጨነገፉ ፖለቲከኞች ”ኢትዮጵያን ነፃ እናወጣለን” እያሉ ፍሬ-አልባ ድርጅቶችን በማቋቋም በህዝብ ስም የሚነግዱ፣በነፃነት ስም እየማሉ ነፃ ያልወጡ፣በስደተኛ ወንድሞቻቸው ስቃይ የግል ጥቅማቸውን የሚያሳድዱ፣የሚሰርቁ፣የሚዋሹ፣ስደተኛ ሴት እህቶቻችንን የሴሰኝነታቸው ማራገፊያ የሚያደርጉ ሲሆን ”ሰው መሳይ በሸንጎ” እንደሚባለው ወድቆ በተነሳው ባንድራችን በየአደባባዩ ሲምሉ፣ስለሀገር አንድነት እና ስለህዝቦቿ ፍትህ ማጣት ሲያወሩ ኤሎሄ ከማለት አልፈን ብዕር እንድናነሳ አስገድዶናል።

ለዛሬ መነሻዬን የአውሮፓ እምብርት ከሆነችው ጀርመን አድርጌአለሁ። (በዚህ አጋጣሚ ውድ አንባብያን ሆይ! በስራ ምክንያት ዩ ኤስ አሜሪካ በየጊዜው የምሄድ በመሆኑ በአሜሪካም ያየሁትንና በቂ ማስረጃ ያገኘሁበትን በቀጣይ እትም አቀርበዋለሁ)። (ሙሉው ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule