• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

አካፋን አካፋ እንላለን!!!

April 28, 2013 12:13 am by Editor Leave a Comment

የጎልጉል ማሳሰቢያ፡ ይህንን ጽሁፍ የላኩልን ሰላማዊት አሰፋ ይባላሉ፡፡ ስለጽሁፉ ይዘት እኛ ከምንናገር ይልቅ አንባቢዎች የራሳቸውን ግንዛቤ እንዲወስዱ ለንባብ አትመነዋል፡፡ ጸሐፊዋን በግል ለማግኘት የሚፈልጉ ሁሉ በቀጥታ በዚህ አድራሻ ለመጻፍ ይችላሉ (a_selamawit53@yahoo.com) ይህንን ጽሁፍ አስመልክቶ በጨዋነት የአጸፋ ምላሽ ለመስጠት የሚፈልጉ ሁሉ የሚልኩልንን ጽሁፍ እንደምናትም ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ!


ሀገራችን ኢትዮጵያ በጠባብ ዘረኞች መዳፍ ስር ከወደቀች እነሆ ከሁለት አስርት አመታት በላይ ተቆጠሩ። ህዝባችንም ቢሆን በዋነኛነት በዘር እንዲከፋፈል ተደርጎ እርስ በርሱ እንዳይተማመን ይልቁንም በጠላትነት እንዲተያይ ከመደረጉም ባሻገር በፖለቲካና በማህበራዊ ጉዳይ በገዛ ሀገሩ ባዕድ እንዲሆን ተደርጓል።በኢኮኖሚውም ቢሆን ኑሮው ዕለት፥ዕለት እያሽቆለቆለ በልቶ ማደርን እንደትልቅ ፀጋ ከሚቆጥርበት ዘመነ ፍዳ ላይ ይገኛል።

የፅሑፌ አላማ ሀገራችን ኢትዮጵያ የገባችበትን አዘቅት እና ህዝቦቿ የሚገኙበትን ሰቆቃ ለመዘርዘር ሳይሆን ከዚህ አስከፊ ሁኔታ ሀገራችንና ህዝቦቿ እንዳይወጡ የየበኩላቸውን አስተዋፅኦ ከሚያደርጉ ሰንኮፎች መካከል በአንዱ ዙሪያ ያለኝን አስተያየት ለማካፈል ነው።

የወያኔን ዕድሜ ከሚያራዝሙ በርካታ ምክንያቶች መካከል ጭንጋፍ /ምቱር/ ፖለቲከኞችና ፍሬ አልባ ድርጅቶቻቸው በዋናነት ይጠቀሳሉ።

እነዚህ ጭንጋፍ /ምቱር/ ፖለቲከኞች በሀገር ቤትም ከሀገር ቤት ውጪም በተለይ በአውሮፓና በዩ ኤስ አሜሪካ ይገኛሉ።የሀገር ቤቶቹ በአብዛኛው በምርጫ ሰሞን በወያኔ ተጠፍጥፈው የሚሰሩ አልያም ራሳቸው እንደ አሸን ፈልተው ከምርጫው ጋር አብረው የሚከስሙ ሲሆን ከዛ ውጪ ያሉትም ቢሆን የህዝብ አመኔታ የሌላቸውና መዋያ ባጡ አዛውንቶች የሚዘወሩ ፍሬ አልባ ሆነው እናገኛቸዋለን።ይህ ማለት ግን በሀገር ቤት ከወያኔ ጋር እየተላተመ ብሎም መስዋዕትነት እየከፈለ የሚታገል ድርጅት የለም ማለት አይደለም።

በሌላ በኩል በህዝባችን ቁስል ላይ ጥዝጣዜን እየጨመሩ ከሚገኙት መካከል ውጪ ሀገር የሚኖሩ ነፍስ-አልባ ተንቀሳቃሽ ሬሳዎች ሲሆኑ እኒህ የጨነገፉ ፖለቲከኞች ”ኢትዮጵያን ነፃ እናወጣለን” እያሉ ፍሬ-አልባ ድርጅቶችን በማቋቋም በህዝብ ስም የሚነግዱ፣በነፃነት ስም እየማሉ ነፃ ያልወጡ፣በስደተኛ ወንድሞቻቸው ስቃይ የግል ጥቅማቸውን የሚያሳድዱ፣የሚሰርቁ፣የሚዋሹ፣ስደተኛ ሴት እህቶቻችንን የሴሰኝነታቸው ማራገፊያ የሚያደርጉ ሲሆን ”ሰው መሳይ በሸንጎ” እንደሚባለው ወድቆ በተነሳው ባንድራችን በየአደባባዩ ሲምሉ፣ስለሀገር አንድነት እና ስለህዝቦቿ ፍትህ ማጣት ሲያወሩ ኤሎሄ ከማለት አልፈን ብዕር እንድናነሳ አስገድዶናል።

ለዛሬ መነሻዬን የአውሮፓ እምብርት ከሆነችው ጀርመን አድርጌአለሁ። (በዚህ አጋጣሚ ውድ አንባብያን ሆይ! በስራ ምክንያት ዩ ኤስ አሜሪካ በየጊዜው የምሄድ በመሆኑ በአሜሪካም ያየሁትንና በቂ ማስረጃ ያገኘሁበትን በቀጣይ እትም አቀርበዋለሁ)። (ሙሉው ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
Copyright © 2026 · Goolgule