• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“አይማረኝ አልምራችሁም” ቦኮ ሃራም ለደቡብ አፍሪካ መንግሥት

April 17, 2015 08:08 am by Editor Leave a Comment

ደቡብ አፍሪካ በተቀሰቀሰው ዓመጽና ግድያ ቦኮ ሃራም የአጸፋ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠነቀቀ፡፡ የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ግጭቱንና ግድያውን እንዲያስቆም ገደብ ሰጠ፡፡ “አይማረኝ አልምራችሁም” አዘል መልዕክት ማስተላለፉ ተገልጾዋል፡፡

የደቡብ አፍሪካው ፕሬዚዳንት ያዕቆብ ዙማ ልጅ የውጭ አገር ዜጎች ከደቡብ አፍሪካ መባረር አለባቸው በማለት ከተናገረ በኋላ የተነሳው ዓመጽና አሰቃቂ ግድያ በርካታዎችን ያስደነገጠና ያስቆጣ ሆኗል፡፡ ከኤድዋርድ ዙማ በተጨማሪ የዙሉው ንጉሥ ተመሳሳይ ንግግር በማድረጋቸው አፍሪካውያን በአፍሪካውያን ላይ ለማመን የሚከብድ ጥቃቶችን ሲፈጽሙ ታይተዋል፡፡

ይህ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ለተለያዩ የውጭ አገር ዜጎች ዘግናኝ ሞት ምክንያት የሆነው ቀውስ በቶሎ እንዲቆም የተለያዩ ጥረቶች እየተደረጉ እንደሆነ የተለያዩ የዜና መዋዕሎች ዘግበዋል፡፡

እስካሁን በእርግጠኝነት ባይታወቅም ከተገደሉት መካከል ናይጄሪያውያን መገኘታቸው ያስቆጣው ቦኮ ሃራም ደቡብ አፍሪካ ደም መፋሰሱን፣ ግድያውንና ዘረፋውን ካላስቆመች የአጸፋ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል፡፡ በተሰጠው ገደብ የደቡብ አፍሪካ መንግሥት በውጭ አገር ዜጎች ላይ እየተከሰተ ያለውን ለማስቆም እምቢ የሚል ከሆነ ቦኮ ሃራም ደቡብ አፍሪካን በቦምብ እንደሚያናውጣት አስጠንቅቋል፡፡ በዚህ በዩትዩብ ተሰራጨ በተባለ አጭር የቪዲዮ መልዕክት መሠረት ቦኮ ሃራም በአጸፋው በናይጄሪያ፣ በቻድ፣ በኒጀር እና በአካባቢው አገራት የሚገኙ ደቡብ አፍሪካውያንን በሞት እንደሚቀጣ ማስታወቁ ተገልጾዋል፡፡

የቦኮ ሃራም መልዕክት እርግጠኛ መሆኑ አልታወቀም ያለው አንድ የናይጄሪያ ጋዜጣ ቦኮ ሃራም ጥቃቱን ከላይ በተጠቀሱት አገራት በሚገኙ የደቡብ አፍሪካ ኤምባሲዎችም ጭምር ላይ እንደሚያደርስ ማስታወቁን ዘግቧል፡፡

የስሙ ትርጓሜ “የምዕራባውያን ትምህርት ሃራም (እርኩስ) ነው” የሆነው ቦኮ ሃራም እኤአ ከ2009 ጀምሮ በናይጄሪያና አጎራባች አገራት እስከ 13ሺህ የሚጠጉ ሰዎችን መግደሉ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ እስላማዊ መንግሥት ለመመሥረት በርካታ ዜጎችን ያፈናቀለው ቦኮ ሃራም በዚህን ወቅት “ጥሩ ሰው” መስሎ ለመታየት መሞከሩ ያስቆጣቸው ናይጄሪያውያን በማኅበራዊ ገጾች አጸፋውን መልሰዋል፡፡ አንዱ አስተያየት ሰጪ “ቦኮ ሃራም አፉን ቢዘጋ ይሻለዋል፤ እነሱ ራሳቸው የሚያደርጉት (ዘግናኝ ተግባር) በደቡብ አፍሪካ ከሚደረገው የተሻለ ነው ብለው ያስባሉ፤ ማፈሪያዎች” ብሏል፡፡

የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚ/ር መ/ቤት ቦኮ ሃራምን አሸባሪ ድርጅት በማለት የፈረጀው ሲሆን የናይጄሪያ መንግሥት እስካሁን ከቦኮ ሃራም ጋር ጦርነት እያካሄደ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የሲኖዶሱ ውዝግብ አካሄድና መጪው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔ February 6, 2023 02:03 am
  • የእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ ተራዘመ፤ ተጠባቂው ዕርቅ ፍንጭ እያሳየ ነው February 3, 2023 05:17 pm
  • የብላቴ: የውጊያ ማርሽ ቀያሪ ሠራዊት መፍለቂያ ማዕከል February 3, 2023 10:06 am
  • በኢትዮጵያ 27 በመቶ የሚሆነው የአእምሮ በሽተኛ ነው ተባለ February 3, 2023 09:47 am
  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule