• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ተመልሰናል!

October 29, 2019 07:42 am by Editor 4 Comments

የጎልጉል ርዕሰ አንቀጽ

በቅድሚያ ለጎልጉል ወዳጆችና አንባቢያን እንዲሁም ጠላቶች ለመጥፋታችን በርካታ አጥጋቢ ምክያቶች ቢኖሩንም በቅድሚያ ይቅርታ ለመጠየቅ እንወዳለን። መረጃ ከእኛ ለማግኘት ፈልጋችሁ ለበርካታ ወራት ሳታገኙ በመቅረታችሁ እናዝናለን። “የት ጠፋችሁ?” በማለት በተደጋጋሚ ስትጠይቁን ለነበራችሁ ቅኖች ምስጋናችን የላቀ ነው። የእናንተን መሰሉ ቅንነት ወደፊትም በብርታት እንድንቀጥል የሚያደርገን ነውና መልካምነታችሁ ወደፊትም አይለየን። በመጥፋታችን ደስ ብሏችሁ የነበረ የበለጠ ደስ ይበላችሁ እንደወጣን አልቀረንም፤ መጥተናል።

አገራችን ያለችበትን ወቅታዊ ሁኔታ ስንመለከተው በርካታ ተስፋ ሰጪ ተግባራት ሲደረጉ ብንመለከትም ያንን የሚያፈርስ እኩይ ተግባር ሲፈጸምም እናያለን። የተደፈውን ቀዳዳ መልሰው የሚቆፍሩ ክፉዎች የመኖራቸውን ያህል ላገራቸው ምንም ጩኸት ሳያሰሙ ተግተው የሚሠሩም እንዳሉ ይታወቃል። ቀን አልፎ ሌላ ቀን በተተካ ቁጥር “ዛሬስ ምን ክፉ ነገር ልናገር?” የሚል የተበላሸ አእምሮ ያላቸው በተለይ በሚዲያው ዘርፍ ያሉትን ያህል “ዛሬስ ስለአገሬ ምን ጥሩ ልሥራ?” ብለው በቀኝ ጎናቸው የሚነሱ ጥቂቶች አይደሉም። አፋቸውን በከፈቱ ቁጥር ክፋት ከመትፋት የማይቆጠቡ የመኖራቸውን ያህል ቢጽፉ፣ ቢናገሩም፣ ቢተቹም፣ መነሻቸው ቅንነት የሆኑ እጅግ ብዙዎች አሉ።

አገራችን ባሁኑ ጊዜ የምትፈልገው ህጸጿን እየነገረ ነጋ ጠባ የሚነዘንዛተን አይደለም። የሚታወቅ፣ የተመዘገበ፣ ታሪከም ሕዝብም የሚረዳው ዘርፈብዙ ችግሮች አሉባት። የአገራችን የወቅቱ ፍላጎት መሪዎችን ያለገደብ ቀንተሌት በመተቸት ህልውናዋን አደጋ ላይ የሚጥልባትን አይደለም።

በተለይ በሚዲያው መስክ የምንገኝ የአገራችንን የወደፊት ዕጣ ፈንታ በጣም ሊያሳስበን ይገባል። እኛ የምናገረው፣ የምንጽፈው፣ የምንተነትነው፣ ወዘተ የሰውን አስተሳሰብ ይነካል። ውጤቱም ለበጎ ወይም ለመጥፎ ይሆናል። ከድርጊት በፊት ሃሳብ ይቀድማል። በተደጋጋሚ ሲሰማ የቆየ ሃሳብ እውነት እየመሰለ መጥቶ ወደ ተግባር ይቀየራል፤ ይህም በቅጡ ካልተገራ አገር የሚያፈርስ ይሆናል። አገር ከፈረሰች በኋላ “ወይ አገሬ” ብሎ ማልቀሻ ቦታም አይኖርም።

በተለይ በአመራር ላይ ያለውን ኃይል ለማጥላላት በተያዘ አባዜ እና በዚያም በተከተለው ጭፍንነት ህወሓትን እስከመደገፍ እነ መለስን እስከማሞገስ የሚደርስ የሚዲያ ልፈፋ ዐቢይን ሳይሆን የሚጎዳው አገርን ሲቀጥልም ራስንና ቤተሰብን ነው።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዘመን ፍዳ ወህወሓት ፈጽሞ ያልታየና አገራችንን እንደ ወረርሽኝ እያጠቁ ያሉት ሁለት ነገሮች ናቸው፤ የሃሰት ወሬ እና ሕገወጥ የመሣሪያ ዝውውር ነው፤ የዚህ ፈብራኪ ማን እንደሆነም በውል ይታወቃል። ዓቅም ኖሮን ሁለቱንም በማስቆም አገራችንን ብንታደግ ደስ ባለን ነበር። ነገርግን አንድ ነገር ማድረግ እንችላለን ብለን እናምናለን፤ ለሕዝባችን በምንችለው ሁሉ ተዓማኒነት ያላቸውን መረጃ በማድረስ አገራችንን ከመጣባት መዓት ለመታደግ ውሳኔያችን በማድረግ ወደሥራ ተመልሰናል።

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ™” አቋም ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. gizachew abebe says

    October 29, 2019 09:20 am at 9:20 am

    ለመሆኑ አንድ የአገር መሪ ስልጣን በቃኝ፣ አገር መምራት አልቻልኩም የሚለው መቼ ነው!? አገርና ሕዝብስ ምን ሲሆኑ ነው!? የዐብይ አሕመድን ድክመት ማጋለጥ ለውጥን መቃዎም አይደለም… ለውጡን ሕያው ለማድረግ መስራ እንጅ!

    Reply
  2. bezuneh tessema says

    October 29, 2019 02:56 pm at 2:56 pm

    glad you back

    Reply
  3. Getachew Abera says

    October 29, 2019 07:19 pm at 7:19 pm

    እንኳን በሰላም ተመለሳችሁ!!
    ጊዜው : ከማንኛውም ጊዜ በላይ እንደናንተ አይነት ቅን አሳቢ: ለሀገር ህልውና እና ለህዝብ ሰላምና ልዕልና የሚጨነቅና የሚተጋ ዜጋ : ሃቀኛ: ቁምነገር ያዘለና መልካም አቅጣጫን የሚመራ ሃሳቦችን የሚያካፍል በእጅጉ የሚፈለግበት ነው::
    መልካም ሃሳባችሁና ዓላማችሁ ለሀገራችን የሚፈለገውን መልካም ግብ ይመታ ዘንድ ልባዊ ምኞቴን እየገለፅኩ: በርቱ! በያለንበት እንበርታ እላለሁ!

    አክባሪ ወንድማችሁ ጌታቸው አበራ

    Reply
  4. ሳምሶን says

    October 31, 2019 11:08 pm at 11:08 pm

    ጎልጉልን ማንበብ በመረጃ ጠቅሞኛል።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የገዳ ሥርዓት እና የኦሮሞ ገዢ መደብ June 20, 2022 11:34 pm
  • “የወልቃይትን ጉዳይ ለድርድር የማናቀርበው ቀይ መስመራችን ነው” ርዕሰ መስተዳድር ይልቃል June 12, 2022 07:09 pm
  • የሰሜን ምዕራብ ዕዝና የአማራ ልዩ ኃይል ተከዜ ክፍለ ጦር ዕውቅናና ሽልማት ተሰጣቸው June 12, 2022 06:21 pm
  • ሀገር በቀል ባህላዊ የግጭት አፈታቶችን በተገቢው በመጠቀም ዘላቂ እርቅና ሰላምን ማምጣት ይቻላል June 12, 2022 05:40 pm
  • የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን በገረጂና በቀበና ያስገነባቸውን የመኖሪያ አፓርትመንቶች አስመረቀ June 12, 2022 05:35 pm
  • በኦነግ ሸኔ ፈርሶ የነበረውና ወታደራዊ ጠቀሜታ ያለው ድልድይ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ June 10, 2022 09:13 am
  • ጃዋር በዳውድ ኢብሣ ቀይ መስመር ተሰመረለት June 8, 2022 12:59 pm
  • ወልቃይት: ቢመረንም ለመዋጥና ራሳችንን ለመመልከት እንሞክር June 8, 2022 11:53 am
  • እብድ ይሻለዋል እንጂ አይድንም፤ ሐጂ ጃዋር አሁን ለምን ብቅ አለ? June 8, 2022 05:59 am
  • ሕዝብ ድምፅ የነፈጋቸው “ፓርቲዎች” የሽግግር መንግሥት ይቋቋም አሉ June 7, 2022 01:11 am
  • “አድጌ እንደናንተ መሆን እፈልጋለሁ” June 5, 2022 06:58 pm
  • በሳምንት ለ100 ያህል ሕሙማን አገልግሎት የሚሰጥ የኩላሊት ዕጥበት ማዕከል ሥራ ጀመረ May 30, 2022 02:20 am
  • የጥቁር አንበሳ ዕጩ መኮንኖች (ካዴቶች) ተመረቁ May 29, 2022 04:01 pm
  • “ኢትዮጵያን መንካት አይቻልም!!” በሚል ቁጭት ነው እየሠራን ያለነው May 29, 2022 01:04 pm
  • “ከሞፈርና ቀንበር ወደ ትራክተር” በሚል መርህ ለአማራ ገበሬዎች የግብርና ሜካናይዜሽን ተሰጠ May 29, 2022 02:02 am
  • ኢትዮ 360 “የወያኔ፣ የጁንታ ሚዲያ ነው” – ባለከዘራው ጄኔራል May 27, 2022 02:51 am
  • “እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ የሚያጣሉን ፖለቲከኞች ናቸው” የአማራ ወዳጃቸውን አደራ ቤት የመለሱ የቅማንት ተወላጅ May 27, 2022 01:40 am
  • ትግራይን አገር እናደርጋለን፤ “በውይይት እና በጦርነት” ሁሉንም ጉዳይ እንቋጫለን – የወንበዴው መሪ ደብረጽዮን May 26, 2022 09:18 am
  • “ሁለቱ የምዕራብ ዕዝ ተዋጊ ዶክተሮች” May 26, 2022 08:19 am
  • ወደ ትህነግ ሊተላለፍ የነበረ አምስት ሚሊዮን ብር ከ20 ተጠርጣሪዎች ጋር ተያዘ May 25, 2022 01:57 am
  • የጦርነቱ ስትራቴጂያዊ እውነታዎች May 19, 2022 09:37 am
  • በጦርነቱ የተጎዱ አካባቢዎችን ለማቋቋም የሚውል የ15 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ድጋፍ የዓለም ባንክ May 16, 2022 10:22 am
  • በአዲስ አበባ 1 ሺህ 98 የብሬን እና 2 ሺህ 162 የክላሽ ጥይት ተያዘ May 16, 2022 10:10 am
  • በአዲስ አበባ ከተማ በግለሰብ መኖሪያ ቤት ከ5 ሺህ በላይ የአሜሪካ ዶላርና የተለያዩ አገራት ገንዘቦች ተያዙ May 16, 2022 09:53 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2022 · Goolgule