• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ተመልሰናል!

October 29, 2019 07:42 am by Editor 4 Comments

የጎልጉል ርዕሰ አንቀጽ

በቅድሚያ ለጎልጉል ወዳጆችና አንባቢያን እንዲሁም ጠላቶች ለመጥፋታችን በርካታ አጥጋቢ ምክያቶች ቢኖሩንም በቅድሚያ ይቅርታ ለመጠየቅ እንወዳለን። መረጃ ከእኛ ለማግኘት ፈልጋችሁ ለበርካታ ወራት ሳታገኙ በመቅረታችሁ እናዝናለን። “የት ጠፋችሁ?” በማለት በተደጋጋሚ ስትጠይቁን ለነበራችሁ ቅኖች ምስጋናችን የላቀ ነው። የእናንተን መሰሉ ቅንነት ወደፊትም በብርታት እንድንቀጥል የሚያደርገን ነውና መልካምነታችሁ ወደፊትም አይለየን። በመጥፋታችን ደስ ብሏችሁ የነበረ የበለጠ ደስ ይበላችሁ እንደወጣን አልቀረንም፤ መጥተናል።

አገራችን ያለችበትን ወቅታዊ ሁኔታ ስንመለከተው በርካታ ተስፋ ሰጪ ተግባራት ሲደረጉ ብንመለከትም ያንን የሚያፈርስ እኩይ ተግባር ሲፈጸምም እናያለን። የተደፈውን ቀዳዳ መልሰው የሚቆፍሩ ክፉዎች የመኖራቸውን ያህል ላገራቸው ምንም ጩኸት ሳያሰሙ ተግተው የሚሠሩም እንዳሉ ይታወቃል። ቀን አልፎ ሌላ ቀን በተተካ ቁጥር “ዛሬስ ምን ክፉ ነገር ልናገር?” የሚል የተበላሸ አእምሮ ያላቸው በተለይ በሚዲያው ዘርፍ ያሉትን ያህል “ዛሬስ ስለአገሬ ምን ጥሩ ልሥራ?” ብለው በቀኝ ጎናቸው የሚነሱ ጥቂቶች አይደሉም። አፋቸውን በከፈቱ ቁጥር ክፋት ከመትፋት የማይቆጠቡ የመኖራቸውን ያህል ቢጽፉ፣ ቢናገሩም፣ ቢተቹም፣ መነሻቸው ቅንነት የሆኑ እጅግ ብዙዎች አሉ።

አገራችን ባሁኑ ጊዜ የምትፈልገው ህጸጿን እየነገረ ነጋ ጠባ የሚነዘንዛተን አይደለም። የሚታወቅ፣ የተመዘገበ፣ ታሪከም ሕዝብም የሚረዳው ዘርፈብዙ ችግሮች አሉባት። የአገራችን የወቅቱ ፍላጎት መሪዎችን ያለገደብ ቀንተሌት በመተቸት ህልውናዋን አደጋ ላይ የሚጥልባትን አይደለም።

በተለይ በሚዲያው መስክ የምንገኝ የአገራችንን የወደፊት ዕጣ ፈንታ በጣም ሊያሳስበን ይገባል። እኛ የምናገረው፣ የምንጽፈው፣ የምንተነትነው፣ ወዘተ የሰውን አስተሳሰብ ይነካል። ውጤቱም ለበጎ ወይም ለመጥፎ ይሆናል። ከድርጊት በፊት ሃሳብ ይቀድማል። በተደጋጋሚ ሲሰማ የቆየ ሃሳብ እውነት እየመሰለ መጥቶ ወደ ተግባር ይቀየራል፤ ይህም በቅጡ ካልተገራ አገር የሚያፈርስ ይሆናል። አገር ከፈረሰች በኋላ “ወይ አገሬ” ብሎ ማልቀሻ ቦታም አይኖርም።

በተለይ በአመራር ላይ ያለውን ኃይል ለማጥላላት በተያዘ አባዜ እና በዚያም በተከተለው ጭፍንነት ህወሓትን እስከመደገፍ እነ መለስን እስከማሞገስ የሚደርስ የሚዲያ ልፈፋ ዐቢይን ሳይሆን የሚጎዳው አገርን ሲቀጥልም ራስንና ቤተሰብን ነው።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዘመን ፍዳ ወህወሓት ፈጽሞ ያልታየና አገራችንን እንደ ወረርሽኝ እያጠቁ ያሉት ሁለት ነገሮች ናቸው፤ የሃሰት ወሬ እና ሕገወጥ የመሣሪያ ዝውውር ነው፤ የዚህ ፈብራኪ ማን እንደሆነም በውል ይታወቃል። ዓቅም ኖሮን ሁለቱንም በማስቆም አገራችንን ብንታደግ ደስ ባለን ነበር። ነገርግን አንድ ነገር ማድረግ እንችላለን ብለን እናምናለን፤ ለሕዝባችን በምንችለው ሁሉ ተዓማኒነት ያላቸውን መረጃ በማድረስ አገራችንን ከመጣባት መዓት ለመታደግ ውሳኔያችን በማድረግ ወደሥራ ተመልሰናል።

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ™” አቋም ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. gizachew abebe says

    October 29, 2019 09:20 am at 9:20 am

    ለመሆኑ አንድ የአገር መሪ ስልጣን በቃኝ፣ አገር መምራት አልቻልኩም የሚለው መቼ ነው!? አገርና ሕዝብስ ምን ሲሆኑ ነው!? የዐብይ አሕመድን ድክመት ማጋለጥ ለውጥን መቃዎም አይደለም… ለውጡን ሕያው ለማድረግ መስራ እንጅ!

    Reply
  2. bezuneh tessema says

    October 29, 2019 02:56 pm at 2:56 pm

    glad you back

    Reply
  3. Getachew Abera says

    October 29, 2019 07:19 pm at 7:19 pm

    እንኳን በሰላም ተመለሳችሁ!!
    ጊዜው : ከማንኛውም ጊዜ በላይ እንደናንተ አይነት ቅን አሳቢ: ለሀገር ህልውና እና ለህዝብ ሰላምና ልዕልና የሚጨነቅና የሚተጋ ዜጋ : ሃቀኛ: ቁምነገር ያዘለና መልካም አቅጣጫን የሚመራ ሃሳቦችን የሚያካፍል በእጅጉ የሚፈለግበት ነው::
    መልካም ሃሳባችሁና ዓላማችሁ ለሀገራችን የሚፈለገውን መልካም ግብ ይመታ ዘንድ ልባዊ ምኞቴን እየገለፅኩ: በርቱ! በያለንበት እንበርታ እላለሁ!

    አክባሪ ወንድማችሁ ጌታቸው አበራ

    Reply
  4. ሳምሶን says

    October 31, 2019 11:08 pm at 11:08 pm

    ጎልጉልን ማንበብ በመረጃ ጠቅሞኛል።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
  • “አዲሷ” ኢህአፓ፤ ከንፈሯን ቀለም የተቀባች አሳማ February 25, 2026 11:24 am
  • የተንጋደደው የገዱ መልስ February 6, 2026 03:05 pm
  • ሻዕቢያ “አክሱም ገብቶ ወጣቶች በጅምላ ሲረሽን ጸብ ተፋፍሟል …” February 4, 2026 01:15 pm
  • አደራ ጠባቂው የኢሉአባቦር ሕዝብ February 4, 2026 12:14 pm
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን January 28, 2026 09:56 am
  • በአሜሪካ ጥምር ዜግነት እንዲቀር ጥያቄ ቀረበ January 27, 2026 03:05 pm
  • “ከህወሓት፣ ከሻዕቢያ፣ ከግብፅ ሰዎች ጋር ሆኖ እንዴት የአማራን ጥያቄ ማስመለስ ይቻላል?” ኮሎኔል ፈንታው January 25, 2026 04:23 am
  • የኢትዮጵያ አየር ኃይል: ለአፍሪካ ሀገራት የመጀመሪያዎቹን የአየር ኃይል አብራሪዎች ያሰለጠነ ተቋም January 25, 2026 03:50 am
  • የአማረ ሪፖርተር እያደረሰ ያለው የብሔራዊ ደኅንነት አደጋ January 22, 2026 01:56 am
  • የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የማርያምን ማዕረግ ዝቅ አደረገች December 12, 2025 09:27 pm
  • ኢህአፓ: ከነጭ ሽብር ወደ “አዲስ አበባ ትናገር” የጎዳና ሽብር? December 12, 2025 09:11 pm
  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule