• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ተመልሰናል!

October 29, 2019 07:42 am by Editor 4 Comments

የጎልጉል ርዕሰ አንቀጽ

በቅድሚያ ለጎልጉል ወዳጆችና አንባቢያን እንዲሁም ጠላቶች ለመጥፋታችን በርካታ አጥጋቢ ምክያቶች ቢኖሩንም በቅድሚያ ይቅርታ ለመጠየቅ እንወዳለን። መረጃ ከእኛ ለማግኘት ፈልጋችሁ ለበርካታ ወራት ሳታገኙ በመቅረታችሁ እናዝናለን። “የት ጠፋችሁ?” በማለት በተደጋጋሚ ስትጠይቁን ለነበራችሁ ቅኖች ምስጋናችን የላቀ ነው። የእናንተን መሰሉ ቅንነት ወደፊትም በብርታት እንድንቀጥል የሚያደርገን ነውና መልካምነታችሁ ወደፊትም አይለየን። በመጥፋታችን ደስ ብሏችሁ የነበረ የበለጠ ደስ ይበላችሁ እንደወጣን አልቀረንም፤ መጥተናል።

አገራችን ያለችበትን ወቅታዊ ሁኔታ ስንመለከተው በርካታ ተስፋ ሰጪ ተግባራት ሲደረጉ ብንመለከትም ያንን የሚያፈርስ እኩይ ተግባር ሲፈጸምም እናያለን። የተደፈውን ቀዳዳ መልሰው የሚቆፍሩ ክፉዎች የመኖራቸውን ያህል ላገራቸው ምንም ጩኸት ሳያሰሙ ተግተው የሚሠሩም እንዳሉ ይታወቃል። ቀን አልፎ ሌላ ቀን በተተካ ቁጥር “ዛሬስ ምን ክፉ ነገር ልናገር?” የሚል የተበላሸ አእምሮ ያላቸው በተለይ በሚዲያው ዘርፍ ያሉትን ያህል “ዛሬስ ስለአገሬ ምን ጥሩ ልሥራ?” ብለው በቀኝ ጎናቸው የሚነሱ ጥቂቶች አይደሉም። አፋቸውን በከፈቱ ቁጥር ክፋት ከመትፋት የማይቆጠቡ የመኖራቸውን ያህል ቢጽፉ፣ ቢናገሩም፣ ቢተቹም፣ መነሻቸው ቅንነት የሆኑ እጅግ ብዙዎች አሉ።

አገራችን ባሁኑ ጊዜ የምትፈልገው ህጸጿን እየነገረ ነጋ ጠባ የሚነዘንዛተን አይደለም። የሚታወቅ፣ የተመዘገበ፣ ታሪከም ሕዝብም የሚረዳው ዘርፈብዙ ችግሮች አሉባት። የአገራችን የወቅቱ ፍላጎት መሪዎችን ያለገደብ ቀንተሌት በመተቸት ህልውናዋን አደጋ ላይ የሚጥልባትን አይደለም።

በተለይ በሚዲያው መስክ የምንገኝ የአገራችንን የወደፊት ዕጣ ፈንታ በጣም ሊያሳስበን ይገባል። እኛ የምናገረው፣ የምንጽፈው፣ የምንተነትነው፣ ወዘተ የሰውን አስተሳሰብ ይነካል። ውጤቱም ለበጎ ወይም ለመጥፎ ይሆናል። ከድርጊት በፊት ሃሳብ ይቀድማል። በተደጋጋሚ ሲሰማ የቆየ ሃሳብ እውነት እየመሰለ መጥቶ ወደ ተግባር ይቀየራል፤ ይህም በቅጡ ካልተገራ አገር የሚያፈርስ ይሆናል። አገር ከፈረሰች በኋላ “ወይ አገሬ” ብሎ ማልቀሻ ቦታም አይኖርም።

በተለይ በአመራር ላይ ያለውን ኃይል ለማጥላላት በተያዘ አባዜ እና በዚያም በተከተለው ጭፍንነት ህወሓትን እስከመደገፍ እነ መለስን እስከማሞገስ የሚደርስ የሚዲያ ልፈፋ ዐቢይን ሳይሆን የሚጎዳው አገርን ሲቀጥልም ራስንና ቤተሰብን ነው።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዘመን ፍዳ ወህወሓት ፈጽሞ ያልታየና አገራችንን እንደ ወረርሽኝ እያጠቁ ያሉት ሁለት ነገሮች ናቸው፤ የሃሰት ወሬ እና ሕገወጥ የመሣሪያ ዝውውር ነው፤ የዚህ ፈብራኪ ማን እንደሆነም በውል ይታወቃል። ዓቅም ኖሮን ሁለቱንም በማስቆም አገራችንን ብንታደግ ደስ ባለን ነበር። ነገርግን አንድ ነገር ማድረግ እንችላለን ብለን እናምናለን፤ ለሕዝባችን በምንችለው ሁሉ ተዓማኒነት ያላቸውን መረጃ በማድረስ አገራችንን ከመጣባት መዓት ለመታደግ ውሳኔያችን በማድረግ ወደሥራ ተመልሰናል።

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ™” አቋም ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. gizachew abebe says

    October 29, 2019 09:20 am at 9:20 am

    ለመሆኑ አንድ የአገር መሪ ስልጣን በቃኝ፣ አገር መምራት አልቻልኩም የሚለው መቼ ነው!? አገርና ሕዝብስ ምን ሲሆኑ ነው!? የዐብይ አሕመድን ድክመት ማጋለጥ ለውጥን መቃዎም አይደለም… ለውጡን ሕያው ለማድረግ መስራ እንጅ!

    Reply
  2. bezuneh tessema says

    October 29, 2019 02:56 pm at 2:56 pm

    glad you back

    Reply
  3. Getachew Abera says

    October 29, 2019 07:19 pm at 7:19 pm

    እንኳን በሰላም ተመለሳችሁ!!
    ጊዜው : ከማንኛውም ጊዜ በላይ እንደናንተ አይነት ቅን አሳቢ: ለሀገር ህልውና እና ለህዝብ ሰላምና ልዕልና የሚጨነቅና የሚተጋ ዜጋ : ሃቀኛ: ቁምነገር ያዘለና መልካም አቅጣጫን የሚመራ ሃሳቦችን የሚያካፍል በእጅጉ የሚፈለግበት ነው::
    መልካም ሃሳባችሁና ዓላማችሁ ለሀገራችን የሚፈለገውን መልካም ግብ ይመታ ዘንድ ልባዊ ምኞቴን እየገለፅኩ: በርቱ! በያለንበት እንበርታ እላለሁ!

    አክባሪ ወንድማችሁ ጌታቸው አበራ

    Reply
  4. ሳምሶን says

    October 31, 2019 11:08 pm at 11:08 pm

    ጎልጉልን ማንበብ በመረጃ ጠቅሞኛል።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • EOC Bans Haile Gebrselassie Over Are­qie Comments Linked to Doping November 21, 2025 07:47 pm
  • በሥራ ማቆም አድማ ጥሪ ዘርፍ ባለሙያው ጃዋር ሌላ ጥሪ አቀረበ November 17, 2025 09:25 am
  • የ-አብሮነት ማኅበር የመረጠው ሕቡዕ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ይፋ ሆነ November 5, 2025 12:06 pm
  • “የኢሳያስ አፈወርቂ ውድቀት አይቀሬ ነው … “ፅምዶ” ራዕይ ዓልባ” ነው – ሼትል ትሮንቮል October 26, 2025 10:15 pm
  • አሜሪካ ስላልተቀበለችው ነው “የሽሽግር መንግሥት” ስብሰባው በአምስተርዳም ተካሄደው October 25, 2025 11:09 pm
  • በዓባይ ግድብ ምረቃ፡ የሕዝብ ደስታ፣ የቴድሮስ ካሳሁን ዝምታ September 14, 2025 04:27 am
  • ኢትዮጵያ የውኃ ኑክሊየር ማብላያዋን ልታስመርቅ ነው  August 29, 2025 11:46 pm
  • መከላከያ በፋኖ አመራሮች ላይ እርምጃ ወሰደ፤ ዘመነ በ“አንድ ማንኪያ ቅንነት” አንድ እንሁን አለ August 23, 2025 12:35 am
  • ፋኖን በፋይናንስና በሎጂስቲክስ የሚደግፉ የጎጃም ባለሃብቶች ከስደት ሊመለሱ ነው August 14, 2025 12:42 am
  • የበቀለ ገርባ የአሜሪካ ጥገኝነት ማመልከቻ ውድቅ ተደረገ August 13, 2025 12:16 pm
  • ሞዐ ተዋሕዶ “ነጻ አውጪ ግምባር” – ሞነግ August 13, 2025 12:58 am
  • የሃይማኖትና የመንግሥት ጥምረት በረከት ወይስ መርገም?  August 5, 2025 09:18 pm
  • የባከነ የስደት ሕይወት ከደባርቅ እስከ ኖርዌይ July 29, 2025 05:44 pm
  • “በዚህ ዓመት መጨረሻ ትግራይን እንቆጣጠራለን”፤ ቲፒኤፍ July 22, 2025 01:28 am
  • Rusted screws, metal spikes and plastic rubbish: the horrific sexual violence used against Tigray’s women July 4, 2025 01:48 am
  • በሞርሞን ቤ/ክ ዕርዳታ የኪዳነምህረት ኦርቶዶክስ ቤ/ክ ማምለኪያ ሥፍራ አገኘች July 2, 2025 01:28 pm
  • የበረከት ስምዖን “አየር ላይ ትዕይንት” አየር ላይ ተበተነ July 2, 2025 01:24 am
  • “ዐቢይ ይውረድ፣ እኛ እንውጣ፣ በተራችን እንግዛ” ስልቴዎች (ስብሃት፣ ልደቱ፤ ቴዎድሮስ) June 11, 2025 01:56 am
  • ኤሊያስ መሠረት የሚሠራው ለማነው? ለብጽልግና? ወይስ …? June 3, 2025 01:27 am
  • በግንቦት 20 – የሁለት መሪዎች ወግ May 28, 2025 02:01 am
  • በፈቃዳቸው የተመለመሉ ወጣቶች ሁርሶ ሥልጠና ጀመሩ May 22, 2025 09:11 am
  • ድብቁ ሤራ ሲጋለጥ – “ሦስትን ወደ አራት” May 21, 2025 01:01 am
  • ከትግራይ ሾልኮ የወጣው ምሥጢራዊው ሰነድ ምንድነው? May 20, 2025 09:18 am
  • በደቡብ ጎንደር በጸዳሉ ደሴ የተመሩት 72 ታጣቂዎች እጃቸውን ሰጡ May 19, 2025 02:24 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2025 · Goolgule