• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ተመልሰናል!

October 29, 2019 07:42 am by Editor 4 Comments

የጎልጉል ርዕሰ አንቀጽ

በቅድሚያ ለጎልጉል ወዳጆችና አንባቢያን እንዲሁም ጠላቶች ለመጥፋታችን በርካታ አጥጋቢ ምክያቶች ቢኖሩንም በቅድሚያ ይቅርታ ለመጠየቅ እንወዳለን። መረጃ ከእኛ ለማግኘት ፈልጋችሁ ለበርካታ ወራት ሳታገኙ በመቅረታችሁ እናዝናለን። “የት ጠፋችሁ?” በማለት በተደጋጋሚ ስትጠይቁን ለነበራችሁ ቅኖች ምስጋናችን የላቀ ነው። የእናንተን መሰሉ ቅንነት ወደፊትም በብርታት እንድንቀጥል የሚያደርገን ነውና መልካምነታችሁ ወደፊትም አይለየን። በመጥፋታችን ደስ ብሏችሁ የነበረ የበለጠ ደስ ይበላችሁ እንደወጣን አልቀረንም፤ መጥተናል።

አገራችን ያለችበትን ወቅታዊ ሁኔታ ስንመለከተው በርካታ ተስፋ ሰጪ ተግባራት ሲደረጉ ብንመለከትም ያንን የሚያፈርስ እኩይ ተግባር ሲፈጸምም እናያለን። የተደፈውን ቀዳዳ መልሰው የሚቆፍሩ ክፉዎች የመኖራቸውን ያህል ላገራቸው ምንም ጩኸት ሳያሰሙ ተግተው የሚሠሩም እንዳሉ ይታወቃል። ቀን አልፎ ሌላ ቀን በተተካ ቁጥር “ዛሬስ ምን ክፉ ነገር ልናገር?” የሚል የተበላሸ አእምሮ ያላቸው በተለይ በሚዲያው ዘርፍ ያሉትን ያህል “ዛሬስ ስለአገሬ ምን ጥሩ ልሥራ?” ብለው በቀኝ ጎናቸው የሚነሱ ጥቂቶች አይደሉም። አፋቸውን በከፈቱ ቁጥር ክፋት ከመትፋት የማይቆጠቡ የመኖራቸውን ያህል ቢጽፉ፣ ቢናገሩም፣ ቢተቹም፣ መነሻቸው ቅንነት የሆኑ እጅግ ብዙዎች አሉ።

አገራችን ባሁኑ ጊዜ የምትፈልገው ህጸጿን እየነገረ ነጋ ጠባ የሚነዘንዛተን አይደለም። የሚታወቅ፣ የተመዘገበ፣ ታሪከም ሕዝብም የሚረዳው ዘርፈብዙ ችግሮች አሉባት። የአገራችን የወቅቱ ፍላጎት መሪዎችን ያለገደብ ቀንተሌት በመተቸት ህልውናዋን አደጋ ላይ የሚጥልባትን አይደለም።

በተለይ በሚዲያው መስክ የምንገኝ የአገራችንን የወደፊት ዕጣ ፈንታ በጣም ሊያሳስበን ይገባል። እኛ የምናገረው፣ የምንጽፈው፣ የምንተነትነው፣ ወዘተ የሰውን አስተሳሰብ ይነካል። ውጤቱም ለበጎ ወይም ለመጥፎ ይሆናል። ከድርጊት በፊት ሃሳብ ይቀድማል። በተደጋጋሚ ሲሰማ የቆየ ሃሳብ እውነት እየመሰለ መጥቶ ወደ ተግባር ይቀየራል፤ ይህም በቅጡ ካልተገራ አገር የሚያፈርስ ይሆናል። አገር ከፈረሰች በኋላ “ወይ አገሬ” ብሎ ማልቀሻ ቦታም አይኖርም።

በተለይ በአመራር ላይ ያለውን ኃይል ለማጥላላት በተያዘ አባዜ እና በዚያም በተከተለው ጭፍንነት ህወሓትን እስከመደገፍ እነ መለስን እስከማሞገስ የሚደርስ የሚዲያ ልፈፋ ዐቢይን ሳይሆን የሚጎዳው አገርን ሲቀጥልም ራስንና ቤተሰብን ነው።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዘመን ፍዳ ወህወሓት ፈጽሞ ያልታየና አገራችንን እንደ ወረርሽኝ እያጠቁ ያሉት ሁለት ነገሮች ናቸው፤ የሃሰት ወሬ እና ሕገወጥ የመሣሪያ ዝውውር ነው፤ የዚህ ፈብራኪ ማን እንደሆነም በውል ይታወቃል። ዓቅም ኖሮን ሁለቱንም በማስቆም አገራችንን ብንታደግ ደስ ባለን ነበር። ነገርግን አንድ ነገር ማድረግ እንችላለን ብለን እናምናለን፤ ለሕዝባችን በምንችለው ሁሉ ተዓማኒነት ያላቸውን መረጃ በማድረስ አገራችንን ከመጣባት መዓት ለመታደግ ውሳኔያችን በማድረግ ወደሥራ ተመልሰናል።

ጎልጉል፤ የድረገጽ ጋዜጣ


ይህ ርዕሰ አንቀጽ የ“ጎልጉል: የድረገጽ ጋዜጣ™” አቋም ነው።

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Editorial Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. gizachew abebe says

    October 29, 2019 09:20 am at 9:20 am

    ለመሆኑ አንድ የአገር መሪ ስልጣን በቃኝ፣ አገር መምራት አልቻልኩም የሚለው መቼ ነው!? አገርና ሕዝብስ ምን ሲሆኑ ነው!? የዐብይ አሕመድን ድክመት ማጋለጥ ለውጥን መቃዎም አይደለም… ለውጡን ሕያው ለማድረግ መስራ እንጅ!

    Reply
  2. bezuneh tessema says

    October 29, 2019 02:56 pm at 2:56 pm

    glad you back

    Reply
  3. Getachew Abera says

    October 29, 2019 07:19 pm at 7:19 pm

    እንኳን በሰላም ተመለሳችሁ!!
    ጊዜው : ከማንኛውም ጊዜ በላይ እንደናንተ አይነት ቅን አሳቢ: ለሀገር ህልውና እና ለህዝብ ሰላምና ልዕልና የሚጨነቅና የሚተጋ ዜጋ : ሃቀኛ: ቁምነገር ያዘለና መልካም አቅጣጫን የሚመራ ሃሳቦችን የሚያካፍል በእጅጉ የሚፈለግበት ነው::
    መልካም ሃሳባችሁና ዓላማችሁ ለሀገራችን የሚፈለገውን መልካም ግብ ይመታ ዘንድ ልባዊ ምኞቴን እየገለፅኩ: በርቱ! በያለንበት እንበርታ እላለሁ!

    አክባሪ ወንድማችሁ ጌታቸው አበራ

    Reply
  4. ሳምሶን says

    October 31, 2019 11:08 pm at 11:08 pm

    ጎልጉልን ማንበብ በመረጃ ጠቅሞኛል።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ሦስት ትውልድ የበላ የሐሰት ትርክት! March 23, 2023 11:59 am
  • “ሽብርተኝነቱን ማንሳቱ በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ለማቋቋም ይረዳል” – ዶ/ር ጌዲዮን March 22, 2023 05:05 pm
  • አስነዋሪ ተግባር ሲፈጸምባቸው የነበሩ የምሽት ክለቦች ተዘጉ March 22, 2023 12:57 pm
  • ህወሓትን ከሽብርተኝነት እንዲሰረዝ የወሰናችሁ ሁሉ ተጠያቂዎች ናችሁ – ኢዜማ March 22, 2023 12:06 pm
  • የኡጋንዳ ፓርላማ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን በእስር የሚያስቀጣ ወንጀል የሚያደርግ ረቂቅ ሕግ አጸደቀ March 22, 2023 12:44 am
  • በጌታቸው ምርጫ ማግስት በትግራይ ሕዝባዊ ዐመፅ ተጀመረ March 21, 2023 11:01 pm
  • በትግራይ ሥልጣንና ንጉሥ ፈጣሪነት ከአድዋ ወደ ራያ ተሻገረ March 19, 2023 03:45 am
  • ኤርሚያስ ከጌታቸው ረዳ ጋር ምሥጢራዊ የስልክ ግንኙነት ነበረው March 19, 2023 02:44 am
  • እየተገባደደ ያለው የምስራቅ አፍሪቃ የትራንስፖርት ኮሪደርና ለውጥ የናፈቃት ኤርትራ March 15, 2023 04:44 pm
  • በባዶ እግር በሮም አበበን ለመድገም March 15, 2023 01:40 pm
  • አሜሪካ ሁለገብ ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ ናት – አንቶኒ ብሊንከን March 15, 2023 08:52 am
  • ጠቅላላ ጉባኤን ያስተጓጎሉ ላይ ክስ እንዲመሰረት ምርጫ ቦርድ ጠየቀ March 15, 2023 08:48 am
  • በኦሮሚያ የተሽከርካሪ ፍጥነት መገደቢያ ገጠማ ያለ አግባብ ለአንድ ግለሰብ ተሰጥቷል ተባለ March 15, 2023 01:43 am
  • ምርጫ ለተወዳደሩና እውቅና ላላቸው ፓርቲዎችመንግሥት 106 ሚሊዮን ብር መደበ March 15, 2023 12:52 am
  • አረመኔና Transgender “ደፋር ሴቶች” ተብለው በተሸለሙበት መዓዛም ተሸለመች  March 10, 2023 10:45 pm
  • ዓድዋ 127 በዓድዋ ከተማ March 2, 2023 09:56 am
  • በምኒሊክ አደባባይ የአድዋ ድል በዓል አከባበር ላይ ምን ተፈጠረ? March 2, 2023 09:43 am
  • አውቶቡሶቹ ከዓለም ባንክ በተገኘ ብር ነው የተገዙት February 24, 2023 10:44 am
  • በአውቶቡሶቹ ግዢ ቢያንስ 1 ቢሊዮን ብር ተሰርቋል፤ ዶ/ር ዐቢይ አስቸኳይ ማብራሪያ ጠይቀዋል February 24, 2023 08:39 am
  • የውርደት ፖለቲካና ፕሮፓጋንዳ! February 24, 2023 08:19 am
  • “አማርኛን የአፍሪካ ኅብረት የሥራ ቋንቋ በማድረግ የኢትዮጵያ ብቻ ሣይኾን የአፍሪካም ማድረግ ይገባል” ራህማቶ ኪታ February 21, 2023 10:09 am
  • አማርኛ የአፍሪካ ኅብረት ቋንቋ እንዲሆን የቀረበ ጥሪ February 21, 2023 10:01 am
  • በገፊና ጎታች ሤራ ከመፈንቅለ ሲኖዶስ እስከ መፈንቅለ መንግሥት February 17, 2023 06:39 pm
  • ኦነግ ሸኔ አሸባሪነቱ ሳይነሳለት በሽመልስ የሰላምና የእርቅ ጥሪ “በክብር” ቀረበለት February 17, 2023 12:35 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule