• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

‘አጃኢብ’ ያሰኘው የአዜብ መስፍን ወሬ

September 22, 2017 10:29 am by Editor 2 Comments

“አከ’ሲ” አለ ያገሬ ሰው፣ ከሰሞኑ ‘አጃኢብ’ ያሰኘውን የአዜብ መስፍን ወሬ ሲሰማ። አዜብ ልምድ ያላት ውሸታም እንጂ  ልምድ ያላት ኮሜዲያን አትመስልም ነበር። ከሚሚ ስብሃቱ ጋር በያዝነው ሳምንት የተወኑት ድራማ ግን ጦሽ አርጎ ያስቃል። መቼም ጥርስ እንጂ ልብ አይስቅ። ፈንድሻም’ኮ ልቧ እየተቃጠለ ነው ፊትዋ ሚፈካው።

ሴትየዋ አይኗን ሳይሆን ቅንድቧን በጨው አጥባ “ምንም የለኝም ግን ይወረስ” ነው የምትለው። መለስ የባንክ ደብተር ይቅርና መንጃ ፈቃድ እንኳ የለውም ስትል የቀለደችበት ወቅት ሩቅ አይደለም። እርግጥ ነው አዜብ በራስዋ ስም እንኳን ሕንጻ፣ ሲም ካርድም ሊኖራት አይችልም። ጥሩ ጋዜጠኛ አልገጠማትም እንጂ፣ ቢገጥማት፣ “እመኑኝ ልጃገረድ ነኝ!” ብላ እያለቀሰችም ቢሆን ለማሳመን ትሞክር ነበር። ልጆቼን እየተበደርኩ ነው የማስተምረው ብላ በተናገረች ሰሞን ኤ.ቢ.ሲ ኢንተርናሽናል የተባለው የማድሪድ ጋዜጣ ወ/ሮ አዜብ መስፍን በአንድ ቀን የግል ግብይት ብቻ 1.5 ሚሊዮን ዶላር እንዳወጣች ዘግቦ ነበር።

የወዲ ስብሃቱ ልጅ አላማ ‘የሙስናዋን ንግስት’ ነጻ ለማውጣት መሞከር ባይሆን ኖሮ፣ በነካ እጅዋ ሰሞኑን በወደቀ ሂሳብ እየተቸበቸቡ ስላሉ የአዲስ አበባ ሕንጻዎች ጉዳይ ታነሳ ነበር።

የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ጠቅልሎ  የያዘው ኤፈርት አናት ላይ ቁጭ ብላ “ምንም የለኝም” የሚል ነጠላ ቀልድ የለቀቀችው አዜብ 30 ሚሊዮን ብር  ከኪስዋ መዝዛ  ለመቀሌ ስፖርት ክለብ መለገስዋን እንኳ ረስታዋለች። ግብር የማይከፍልና የኦዲት ቁጥጥር የማይነካው ደጀና የተባለው የማፍያ ኩባንያ ከኤፈርት ጋር ተጣምሮ የሃገሪቱን ኢኮኖሚ እኩሌታ ይዟል። ካፒታሉ አፍሪካ አንደኛ  የሆነው የዚህ ጥምር ዋና ሥራ አስፈጻሚ (CEO) ነኝ ብላናለች አዜብ። ሰማይ አይታረስ፣ ንጉስ አይከሰስ፣ ደሞዝ አይነገር … ደሞዝ አይጠየቅ! በዛሚ!

“ዛሚ ኤፍ.ኤም” ተብሎ በሚጠራው የነሚሚ ስብሀቱ ራዲዮ ጣቢያ ከዚህ ቀደም የሞራል ቀውስ ውስጥ ገብተው የሚዋኙ ትናንሾችን እያቀረበ፣ በደረቀ ፕሮፓጋንዳ  ብቻ ብዙ መጓዝ ባለመቻሉ፣ የፕሮግራም ለውጥ ያደረገ ይመስላል። እንደ አዜብ መስፍን አይነቱን ጥያቄና መልስ እያስጠና ተከታታይ ድራማ ማቅረብ ጀምረዋል። የመጀመርያው ሾው  በቴዲ አፍሮ  ተጀመረ ። ገድለው ሃውልት መስራት ለነሱ አዲስ ነገር አይደለምና ጸሃይ የሞቀውን “እርምጃው ፍትሃዊ አይደለም” እንቶፈንቶ ደጋገመችው። የቴዲ አፍሮን የአልበም ምረቃ ያገደውን ስውር እጅ  አደባብሳ አለፈችው። ስለማታውቀው  ፍትህ እና መብት መለፈፍዋ ግን ብዙዎችን ሳያስደምም አልቀረም።

አዜብ በተከታዩ ክፍል ብቅ ብላ፣ “የምተዳደረው በዶሞዝ ነው። መለስም፣ እኔም፣ ልጆቼም ሃፍት የላቸውም” አለችን።

“ውልና ማስረጃ የሌለው ሃፍት ካላኝ ቦታውን ያሳዩኝ እና ለኢትዮጵያ ህዝብ ልመልሰው” የሚለው ሕጻን ልጅን እንኳ የማያሳምን አባባልዋ ትንሽ ያስቃል። ሕዝብ በደቦ ወጥቶ የአዜብና ዘመዶችዋን ያልተመዘገበ ንብረት እንዲያፈላልግላት መጠየቅዋ ነው ወይንስ የእሷም ህንጻዎች እንደ ኮንዶሚኒየሙ “ጠፍተዋል” ብለው ነገሯት? ከሠበታ የወሰደችው 1200 ሄክታር መሬት የቀብርዋ ስፍራ መሆኑ ነው። ይህ ደግሞ በነሱ ቋንቋ ሙስና አይባልም። ሙስናም ቢሆን ለከባባድ ሚዛን የህወሃት አባላት የአገልግሎት ስጦታ ነው። አቶ አያሌው መንገሻ፣ የቀድሞው የደህንነት መ/ቤት ሹም ህብር ሬዲዮ ላይ ቀርበው በሰጡት ቃለ ምልልስ “በሕወሃት ሙስና ወንጀል አይደለም” ብለውናል።

ኮሜዲያን ወደ ውጭ ሲሰደዱ፣ ፖለቲከኞቹ  ቦታቸውን ይዘዋል ልበል? ከሰሞኑ የህወሃት ካድሬዎች እንደጉድ መቀለድ ጀምረዋል። አዜብ እና ከሚሚ ተደራጅተው የሰሩት ይህ  እየሳቁ-ማንባት ተውኔት ግን ከኮሜዲ መስመር ወጣ ይላል።

ቃለ-ምልልሱ የተጠና ላለማስመሰል እንኳ አለመሞከራቸው፣ ለአድማጭ ያላቸውን ንቀት ያሳያል። “መኖርያ ቤት ሰርተሻል?” የሚለው የመጀመርያ ጥያቄ ሲቀርብላት ነበር፣ አዜብ “ከሌላው ጋር አብሬ ልመልሰው” ስትል ተከታዩን ጥያቄም እንደምታውቀው ያስፎገረችው። መዋሸት አንድ ነገር ነው። ውሸት ለማስመሰል መቻል ደግሞ ማወቅን ይጠይቃል። ይህንን እንኳን ማድረግ አልቻሉም። የዛሚዋ ካድሬ ሚሚ ስብሃቱ አዜብን ለማንጻት ብዙ የታከከች ይመስላል – ለዛሬ ባይሳካም።

አዜብ እውቀት ነጻ ትሁን እንጂ፣ በጣም ደፋር ናት። የእንግሊዝን መንግስትንም ሆነ የአውሮፓ ህብረትን ብትጠይቁ ምንም የሌለኝ  ድሃ መሆኔን ይነግሯችኋል ትለናለች። አዜብ ሃብታም ግን የምትሆነው ህወሃት ወይንም ኤፈርት ሲለቅቃት ብቻ ነው። “ድርጅቴ ሲለቅቀኝ በግሌ ከጉልት ንግድ በመጀመር ሃብታም ሆናለሁ” ስትል አስቃናለች።

ይህንን ያድርግልሽ ብለናል!

ክንፉ አሰፋ

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. በለው ! says

    September 26, 2017 09:46 pm at 9:46 pm

    ——– ታጋይቷ አልሰሙም ? “ኀይለመለስ ከአማራ ክልል በስተቀር ሁሉም ክልሎች ወርቅ በሰፌድ ይነጠራል ” በወይልቃይት አማራነትዎ አንድ ሰፌድ አልሰፉም ? ወይስ ሰፌድ መግዣ የለዎትም? አለዚያም ጥሩ ጎረቤት የለዎትም ? ምን አልባት የመለስ ወንድም ጢቢኛ ሲሸጥ፡ እህቱ ጠላ ስትሸጥ ፡እርስዎ ጉልት ቸርቻሪ መሆን ያማረዎት ፓርቲዬ አለቅም አለኝ ትወና ህወሃት ሥራ አይንቅም ድልድይ ማፍረስ፡ ባንክ መዝረፍም፡ የዕርዳታየለዎትም፡፡፡፡ሙስናም የተካነበት ፍጥረቱ አደለም እንዴ? ዋሸሁ?
    ______ “የምተዳደረው በዶሞዝ ነው። መለስም፣ እኔም፣ ልጆቼም (ሃፍት )የላቸውም አለችን። ኤ.ቢ.ሲ ኢንተርናሽናል የተባለው የማድሪድ ጋዜጣ ወ/ሮ አዜብ መስፍን በአንድ ቀን የግል ግብይት ብቻ 1.5 ሚሊዮን ዶላር እንዳወጣች ዘግቦ ነበር።”

    ” አዜብ እውቀት ነጻ ትሁን እንጂ፣ በጣም ደፋር ናት። የእንግሊዝን መንግስትንም ሆነ የአውሮፓ ህብረትን ብትጠይቁ ምንም የሌለኝ ድሃ መሆኔን ይነግሯችኋል ትለናለች። አዜብ ሃብታም ግን የምትሆነው ህወሃት ወይንም ኤፈርት ሲለቅቃት ብቻ ነው። “ድርጅቴ ሲለቅቀኝ በግሌ ከጉልት ንግድ በመጀመር ሃብታም ሆናለሁ”… ይህንን ያድርግልሽ ብለናል!

    _____ “የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ጠቅልሎ የያዘው ኤፈርት አናት ላይ ቁጭ ብላ “ምንም የለኝም” የሚል ነጠላ ቀልድ የለቀቀችው አዜብ 30 ሚሊዮን ብር ከኪስዋ መዝዛ ለመቀሌ ስፖርት ክለብ መለገስዋን እንኳ ረስታዋለች። ግብር የማይከፍልና የኦዲት ቁጥጥር የማይነካው ደጀና የተባለው የማፍያ ኩባንያ ከኤፈርት ጋር ተጣምሮ የሃገሪቱን ኢኮኖሚ እኩሌታ ይዟል። ካፒታሉ አፍሪካ አንደኛ የሆነው የዚህ ጥምር CEO ነኝ ብላናለች አዜብ። ውልና ማስረጃ የሌለው ሃፍት ካላኝ ቦታውን ያሳዩኝ እና ለኢትዮጵያ ህዝብ ልመልሰው” ስትል አስቃናለች።” ሕዝብ የወርቆቹ ሲሆን ቦርቃቃው ብሔር ብሔረሰብ ግን ለጭፈራ እንጂ ለሀፍት ውርስ እንኳ ቦታ የለውም ማንነቱን የጣለ ሀፍት ይጠይቃልን? ወ /ሮ አዜብ ቤት አለዎት?ከአስረኛ እና ጎላ ከጥሊያን ወረራ ግዜ በሹምባሽነት የተሸለሙት ሲወርድ ሲዋረድ የመጣው ሀፍት በገዢውና አውራው ፓርቲ ተራራውን ላንቀጠቀጡ በውልና ማስረጃ አፀደቀላቸው!?
    *************!
    “ቀዳማዊት እመቤት አትበሉኝ ” ! ያ …ማለት የአቶ እከሌ ሚስት ለማለት ነው ። ታጋይ አዜብ መስፍን( ጎላ ) በሉኝ ሲሉ ለዚህ ኮራጅ ትውልድ ማረሚያ ሰጡ ምንስ ቢሆን ወልቃይት ተከዜን ሳይሻገሩ ለአማርኛ አይቀርብምን!?
    “ተመዝግቦ በነፃ የታደላችሁ ሀብትና መሬት ስንት ነው ? ብሎ የሚጠይቅ የለም፡ ይህ ሕዝባቸው ማንነቱን ያወቀው እና የተፈጠረው በሕወሓት መልካም ፈቃድ ነው ። ” ከውጭ ይዘነው የመጣነውን ገንዘብ ሌላ ሀገር ኢንቨስት ከማድረግ ለአማራና ኦሮሞ ትንሽ ትንሽ በጭቀንላቸዋል ። ለመሆኑ የኢፈርትን ገንዘብ የሚጠይቀው ምን ሰው ? ማለቴ ሰው ስል የተማረ ማለቴ ነው”ዶክተር ስብሃት ነጋ
    ** የሚደግፋቸው ፹ከመቶ ገበሬ ስላልተማረ ሰው አደለም !። ማንነትህን በፍቃደኝነት ለቀህ ሀገርህን በክልል ለውጠው የበይ ተመልካች ፡ቤተ ሙከራ፡ ሆነህ ለጭፈራ ተጠራርቶ ተገፋትሮ የሚመጣ፡ የልዩ ጥቅማጥቅም ምርኮኛ ሕዝብ፡ የእርዳታ ንፍሮ እየነፋ በተውሶ ልብስና የፀሐይ መነፅር ተወጥሮ የአዞ ዕንባ :ልሃጭና ንፍጡን ባዶ ሳጥን ላይ ሲያዝረከርክ ቤተመንግሥት ቁጭ ብለው አድርባይ ! እያሉ ተሳልቀዋል አሁን ቢኮምኩ ብርቅ ነው ? ጠቅላዩ ባለቤታቸው የብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦችን ቀልድና ተረት ጨርሰው የቻይና ተረትና አባባል ፓርላማ መኮመክ ሲጀምሩ ጠቀለሏቸው።ህወሓት ኢህአዴግና ኢፈርት በመለስ ዜናዊ ቤተሰብ ጭንቅላት ብቻ እየተመራ ሌላው ሎሌ መሃይም ነው ማለት አደለምን ?ለመሆኑ የመንገድ ላይ ነዋሪ ልጆች እና ባለቤታቸውን ተማምነው ሀፍት ንብረታቸውን ገጠር ተነጥቀው ቤተመንግሥት መንገድ ዳር የወደቁትን ብሔር ብሔረሰቦች እንደምን አደረጓቸው ? እነሱ ሀፍት አካብተው መለስ ቤተሰብ ላይ የተነሱትን ሥም አጥፊ፡ የሙሰኞች ቡድን እንዳለ አያወቁ እስከ ዛሬ ለኢትዮጵያ ሕዝባቸው ለምን አላጋለጡም ? አስገደ እና ገብረመድህን የተባሉትን ዛር ቀስቃሽ አስጓሪ ይላክባቸው !!።
    ዘይገርም…

    Reply
  2. balcha says

    October 2, 2017 03:58 pm at 3:58 pm

    Azeb and aba sebhat nega are clue less but clue givers. Lie is there moto and arrogance is there identity. They are all lucky because they are in Ethiopia, if they were some where else, it could have been a different story.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule