• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ህወሃት አረጋግቶ አገገመ

December 1, 2012 12:55 am by Editor Leave a Comment

ኢህአዴግ “አረጋግቶ አገገመ” ከተባለው አዲሱ “ምደባ” መካከል የንግድ ሚኒስትር  ተብለው በተሰየሙት ላይ ብቸኛው የፓርላማ ተወካይ አቶ ግርማ ሰይፉ ጠንካራ መከራከሪያ በማቅረብ ተቃወሙ። አቶ ግርማ የሚሾሙ ብቻ ሳይሆን የሚነሱ ባለስልጣናት ከሃላፊነታቸው የተነሱበት ምክንያትም ለህዝብ መቅረብ እንዳለበት አሳሰቡ። አቶ ሃይለማርያም ተቃውሞውን “መክረንና ገምግመን ያደረግነው ነው” ሲሉ ተከላከሉ። አቶ ግርማ ብሩ (አሁን አምባሳደር) ሲመሩት የነበረውን ሚኒስቴር መ/ቤት “ስያሜና ምልክት መለየት የማይችል” በማለት አንቋሸሹት።

ጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ አገሪቱን በመሩበት ሶስት ወራት ካቢኒያቸውን በደንብ መገምገማቸውን በግምት በመግለጽ ተቃውሞ ያቀረቡት አቶ ግርማ ሰይፉ በምደባው በተወሰነ ደረጃ እንደሚስማሙ ተናግረዋል። የንግድ ሚኒስትሩ አቶ ከበደ ጫኔን ምደባ የተቃወሙት በማስረጃ ነው። የዓለም ባንክ ለንግድ ምዝገባ የማያመቹ አገሮችን ዝርዝር ጥናት ይፋ ሲያደርግ ኢትዮጵያ ከ185 አገሮች የ165ኛ ደረጃ ማግኘቷን፣ ለዚህም የዳረጉት ቀደም ሲል በተጠባባቂ ሚኒስትርነት ለረዥም ጊዜ ያገለገሉት አቶ ከበደ ጫኔ በመሆናቸው አዲሱ ሹመት እንደማይገባቸው አቶ ግርማ በተቃውሞ ተናግረዋል። በተጨማሪም ህዝብ የማወቅ መብት ስላለው ከፍተኛ ባለሥልጣናት ከሃላፊነታቸው ሲነሱ ምክንያቱ ይፋ ሊሆን እንደሚገባው ማሳሰቢያ አቅርበዋል።

አቶ ግርማ ብቻ የተቃውሞ አስተያየት ያቀረቡበት ምደባ በስፋት ሃሳብ ሲሰጥበት ለነበረው የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ወንበር መልስ በመስጠት ተጠናቋል። ምደባውን ህወሃት ሲያሸንፍ የተመደቡት ሚኒስትር አቶ መለስ በህይወት እያሉ ይተኳቸዋል የተባሉት ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም ናቸው። የግራ ዘመሙን የፖለቲካ ጎዳና እምብዛም የማያውቁት ዶ/ር ቴዎድሮስ “ልምድ ያላቸው ታጋይ አይደሉም” በሚል ህወሃትን በከፍተኛ አመራርነት ስለመወከላቸው ጥያቄ የሚያቀርቡባቸው ነበሩ።

ለሼኽ መሐመድ ሁሴን አላሙዲን እጅግ ቅርብ  የሆኑት አዲሱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር ድር /ኔትዎርክ/ አካል ናቸው። በምደባው በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነት ማዕረግ የፋይናንስና የኢኮኖሚ ዘርፍ አስተባባሪ ሆነው የተመደቡት ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤልም በተመሳሳይ የአቶ መለስ ቅርብ ሰው ናቸው። ጎልጉል ዶ/ር ደብረጽዮን ወደ ከፍተኛው ስልጣን ርካብ እንደሚሻገሩ ጠቅላይ ሚኒስትር እንደሚሆኑ ዘግቦ ነበር።

ክፍት በነበሩና በአዲሶቹ ሶስት አደረጃጀቶች መሰረት የተካሄደውን የባለሥልጣናት ምደባ አስመልክቶ አቶ ሃይለማርያም “ጠ/ሚኒስትሩ በቀጥታ ከሚከታተላቸውና ከሚመራቸው የመከላከያ፣ የደህንነት፣ የዲፕሎማሲ፣ የማክሮና ሜጋ ፕሮጀክቶች በተጨማሪ ያሉትን የማህበራዊ፣ የመልካም አስተዳደር፣ የኢኮኖሚና የፋይናንስ ዘርፎችን የመከታተል ስራ እንዲሰሩ ክላስተሮች ተቋቁመዋል” ብለዋል። አይይዘውም  አደረጃጀቱ ስራዎችን በየደረጃው ለመምራት የሚያስችል እንደሆነ አመልክተዋል።

የኢህአዴግ ፓርላማ በዛሬው ዕለት የቀረቡለትን ምደባዎች ሲያጸድቅ ጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ያቀረቡት የከፍተኛ ባለሥልጣናት ምደባ ከአቶ ደመቀ መኮንን በተጨማሪ ሁለት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮችን አካትቷል። ምደባው ከትግራይ ሁለት፣ አንድ ከኦሮሚያ፣ አንድ ከጉራጌ ብሄረሰብ የተካተቱበት መሆኑ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለተመዳቢዎቹ ሲያስታውቁ ገልጸዋል።

ምደባው በደፈናው ሁሉም የኢህአዴግ አባል ድርጅቶች የተካተቱበት ቢመስልም ጎልጉልን ጨምሮ በተለያዩ ሚዲያዎች አስቀድሞ እንደተነገረው ከአቶ መለስ ዜናዊ ህልፈት በኋላ ተግባራዊ ተደርጓል ለተባለው የቡድን አመራር ማረጋገጫ ተደርጎ ተወስዷል። በጸደቀው ምደባ መሰረት ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር፣ አቶ ሙክታር ከድር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር፣ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር የነበሩት ዶ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም  የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፣ ዶ/ር ከሰተብርሃን አድማሱ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር፣ አቶ ከበደ ጫኔ የንግድ ሚኒስትር እንዲሆኑ  ተደርጓል።

በዚሁ ምደባ መሰረት ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የፋይናንስና የኢኮኖሚ ዘርፍ አስተባባሪ ሆነው ቢመደቡም ከደህንነት ጋር የተቆራኘውን የመገናኛና የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትርነታቸውን አልተነጠቁም። የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ሃላፊነታቸውን ስለመቀጠላቸው በይፋ ያልተገለጸው አቶ ሙክታር ከድር በምክትል ጠ/ሚኒስትርነት ማዕረግ የመልካም አስተዳደር ማሻሻያ ዘርፍ አስተባባሪና የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትር ሆነዋል። አቶ ሙክታር ከኦሮሚያ ምክትል ፕሬዚዳንትነታቸው ተነስተው ለሁለት ዓመት ኢህአዴግ ጽህፈት ቤት ያለ ስራ እንዲቀመጡ ተደርጎ የነበረው በመልካም አስተዳደር ችግርና አቅም ማነስ እንደነበር በማስታወስ አስተያየት የሰጡ “ምደባው ኦህዴድ የምክትል ጠ/ሚኒስትርነት ቦታ አገኘ በሚል የፖለቲካ ጨዋታ ለመጫወትና የውጪ ጉዳይ ሚኒስትርነቱን ቦታ በመጠየቁ ለማስተዛዘኛ ነው” ብለዋል። በሌላ በኩልም አቶ ሙክታር ለባለሃብቱ አላሙዲ ቅርበት ያላቸውና በዚሁ ቅርበታቸው ሳቢያ ኦሮሚያ ክልል ባለሃብቱ ግብር እንዲከፍሉና የወሰዱትን ቦታ እንዲያለሙ ለማስገደድ ሲንቀሳቀስ አቶ ሙክታር በመቃወማቸው በኦህዴድ ስራ አስፈጻሚ በጉድለት መገምገማቸውን ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ ይናገራሉ።

ደመቀ መኮንን እና ሃይለማርያም ደሳለኝ

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የትምህርት ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ጨምሮ ሶስት  ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮች የሚደገፉት አቶ ሃይለማርያም፣ አቶ መለስን ተክተው መስራት በጀመሩ ማግስት “የምንሰራውና የምንመራው በቡድን ነው” ባሉት መሰረት በሶስት ም/ጠቅላይ ሚኒስትሮች መታጀባቸው ይፋ ሆኗል። ጎልጉል ብዙም ትኩረት ያልተሰጣቸውን ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ጠ/ሚኒስትር ለማድረግ ታስቦ በአሜሪካን  ተጽዕኖና በቅድመ ማግባባቱ ላይ የኦህዴድን ድጋፍ ሊያገኙ ባለመቻላቸው አቶ ሃይለማርያም በነበሩበት እንዲቀጥሉ መደረጉ መዘገቡ ይታወሳል።

በአዲሱ ምደባ የዶ/ር ቴዎድሮስን ቦታ በመረከብ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር የሆኑት ምክትላቸው ዶ/ር ከሰተብርሃን አድማሱ ናቸው። የአምስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ምደባ ይፋ በሆነበትና በዛሬው ዕለት አቶ ሃይለማርያም እንደ ወትሮው ሁሉ ንግግራቸውን የጀመሩት የአቶ መለስን ስም በማስቀደም ነበር። በዚሁ ንግግራቸው “ቀደም ሲል የተያዘው የአመራር መተካካት ከታቀደው በፊት ተግባራዊ ይደረጋል” ሲሉ ተደምጠዋል።

አቶ ግርማ ሰይፉ ላቀረቡት ተቃውሞ መልስ የሰጡት አቶ ሃይለማርያም ቀደም ሲል አቶ ግርማ ብሩ ይመሩት የነበረውን የንግድ ሚኒስቴር “የንግድ ምልክትና የንግድ ስያሜ እንኳን መለየት የማይችል እጅግ ኋላ ቀር” ሲሉ ነው ያንኳሰሱት። የዓለም ባንክ ሪፖርት ይፋ ባይደረግም አቶ ከበደ ጫኔ ችግር እንዳለ በማወቅ አዲስ አዋጅ በማዘጋጀትና ዘመናዊ አሰራር በመዘርጋት ተቋሙን በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ለመለወጥ እየሰሩ ያሉ ሚኒስትር መሆናቸውን በመግለጽ አቶ ሃይለማርያም ተከራክረውላቸዋል። አዳዲሶቹ የፌደራል ስራ አስፈጻሚዎች ቃለመሃላ ፈጽመዋል። ኦህዴድ ያገኘዋል የተባለውን የውጪ ጉዳይ ሚኒስትርነት መቀመጫ ማጣቱን ተከትሎ አስተያየት ለማሰባሰብ ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም። ምደባው እንደተለመደው በአንድ ድምጸ ታቅቦ ነው የጸደቀው። በዕለቱ ምክንያቱ ባይታወቅም አፈ ጉባኤ አባዱላ ገመዳ አልተገኙም።

ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (https://www.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
  • የጃኖ ስጦታና የዶሮ ፖለቲካ በጎንደር March 10, 2026 09:24 am
Copyright © 2026 · Goolgule