• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዓረና ትግራይ ፓርቲ አዲስ ፕሬዚዳንት መረጠ

September 10, 2013 04:46 am by Editor Leave a Comment

ከጳጉሜን 2 እስከ 3 ቀን 2005 ዓ.ም. ሦስተኛ ጉባዔውን በመቐለ ከተማ ያካሄደው ዓረና ትግራይ ለዲሞክራሲና ለሉዓላዊነት (ዓረና ትግራይ) ፓርቲ በቀድሞው የትግራይ ፕሬዚዳንት አቶ ገብሩ አስራት ምትክ፣ የፓርቲውን የቀድሞ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ብርሃኑ በርሄን ፕሬዚዳንት አድርጎ መረጠ፡፡

የሕወሓት መሥራች አቶ አስገደ ገብረ ሥላሴ በፈቃዳቸው ከፓርቲው አመራር መልቀቃቸው ታውቋል፡፡

በአቶ ገብሩ አስራት የቀረበው የፓርቲው የሦስት ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት የተገመገመ ሲሆን፣ በክልልም ሆነ በአገር አቀፍ ደረጃ የአገሪቱ የፖለቲካ ሁኔታ የማያሠራ ቢሆንም በዚሁ ሳይደናቀፍ ዓላማውን እያሳካ መሆኑ ተገልጿል፡፡ በክልሉ ውስጥ በበርካታ ከተሞች በሕገወጥ መንገድ ቤቶች መፍረሳቸውን የተመለከተው ፓርቲው፣ ሕዝቡ በመልካም አስተዳደርና በፖለቲካ ነፃነት ችግር ውስጥ እንደሚገኝ መገምገሙን አስታውቋል፡፡

የፓርቲውን ፕሮግራምና ሕገ ደንብ የገመገሙ ጉባዔተኞች፣ ከተወሰኑ ማሻሻያዎች በስተቀር ከፍተኛ ለውጥ ያላደረጉ መሆኑን ለሪፖርተር የገለጹት የፓርቲው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አምዶም ገብረ ሥላሴ ናቸው፡፡ ውይይት ከተደረገባቸው ጉዳዮች መካከል የአገሪቱ የፖለቲካ ምኅዳርና በተለይ በክልሉ ውስጥ በአባላቱ ላይ እየደረሰ የሚገኘው አፈና ይገኙበታል ብለዋል፡፡ አፈናው ከፍተኛ መሆኑ የተገመገመ ቢሆንም፣ በቀጣይ ፓርቲው አባል የሆነበት መድረክ ወደ ሙሉ ውህደት የሚያመራ በመሆኑ፣ አፈናውን ተቋቁሞ ለውጥ ለማምጣት መወሰኑን አክለው ገልጸዋል፡፡

በዚሁ ሦስተኛው የፓርቲው ጉባዔ የሕግ ባለሙያውና የቀድሞ የሕወሓት አባልና ታጋይ አቶ ብርሃኑ ኃይሉ ፕሬዚዳንት ሆነው ሲመረጡ፣ አቶ ጎይቶም ፀጋይ ለምክትል ፕሬዚዳንትነት ተመርጠዋል፡፡

በማኅበራዊ ድረገጾች በተለይ የሕወሓትና የትግራይ ክልላዊ መንግሥት የፍትሕና የመልካም አስተዳደር ጉድለቶች ናቸው የሚላቸውን በመተቸት የሚታወቀው ወጣት አብርሃ ደስታ፣ ጉባዔውን ከአቶ ገብሩ አስራትና ከወ/ሮ አረጋሽ አዳነ ጋር በመሆን መምራቱንና በመጨረሻም የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ ሆኖ መመረጡ ተገልጿል፡፡

በ2000 ዓ.ም. በትግራይ ክልል የመጀመሪያ ተቃዋሚ ፓርቲ ሆኖ የተመሠረተው ዓረና ትግራይ ፓርቲ ከዚህ በፊት 90 የነበረውን የጠቅላላ ጉባዔ አባላት ቁጥር ወደ 130 ከፍ እንዲል ማድረጉ ታውቋል፡፡ በተጨማሪም የሥራ አስፈጻሚ አባላትን ቁጥር ከዘጠኝ ወደ አሥራ አንድ ከፍ ያደረገ ሲሆን፣ የማዕከላዊ ኮሚቴ ቁጥር ከ21 ወደ 25 ማሳደጉም ተወስቷል፡፡ ከእነዚህ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት መካከል 15 የሚሆኑት አዳዲስ ተመራጮች መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ (ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • “አስደንጋጭ”! 1 ሚሊዮን ከሚጠጋ ተፈታኝ ተማሪ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገባው 30 ሺህ (3.3%) ብቻ ነው  January 27, 2023 09:11 am
  • የማይዘነጋዉ የኢትዮጵያዊያኖች የጀግንነት ተጋድሎ ታሪክ፡- ኮሎኔል ባጫ ሁንዴ (ታጠቅ) January 27, 2023 06:12 am
  • ጎርጎራ – የመጻዒው ዘመን ሙሽራ! የዉበት ፈርጥ! January 17, 2023 04:18 pm
  • ሁለተኛው መስቀል አደባባይ January 17, 2023 04:13 pm
  • በአቡዳቢ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን January 17, 2023 04:08 pm
  • በንፋስ ስልክ ላፍቶ ስምንት የመሬት ሌቦች ተያዙ January 16, 2023 11:36 am
  • ሺሻ ሲያስጨሱ በተገኙ ሆቴሎችና የምሽት ጭፈራ ቤቶች ላይ እርምጃ ተወሰደ January 16, 2023 08:50 am
  • በሐሰተኛ መታወቂያ የደኅንነት አባል ነን ብለው ሲያጭበረብሩ የነበሩ ተያዙ January 13, 2023 02:03 pm
  • ተሽከርካሪ ወንበር ለትግራይ – “ናይ ኣካል ጉዱኣት ተሽከርካሪ ዘለዎ ወንበር” January 12, 2023 07:17 pm
  • የአማራው ኩራት፣ የኢትዮጵያ ዘብ፣ የትህነግን ቅስም ሰባሪ! January 12, 2023 04:00 pm
  • በኢትዮጵያ ላይ የተጣሉ ማዕቀብ እና ሌሎች አስገዳጅ ሕጎች ሙሉ ለሙሉ ተሰረዙ January 12, 2023 01:52 pm
  • የቻይና ዕዳ ስረዛ “Payday Loan Diplomacy” ወይስ ኢትዮጵያን ያዳነ ተግባር? January 12, 2023 11:00 am
  • የአዲስ አበባ አስተዳደር ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ውሳኔ አስተላለፈ January 12, 2023 10:46 am
  • “አምባሳደሩ” የቀድሞ ጌቶቻቸውን እንዲያቋቁሙ ተሾሙ January 11, 2023 03:47 pm
  • መከላከያ ሸኔን የሚዋጉ ሚሊሻዎችን አሠልጥኖ አስመረቀ January 10, 2023 05:37 pm
  • በሰባት ተጠርጣሪዎች ላይ ከባድ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ January 10, 2023 03:36 pm
  • የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አቅጣጫ January 6, 2023 03:26 pm
  • “ከዕብሪቱ አስተንፍሰነዋል” – ኢሳያስ January 2, 2023 07:29 pm
  • [ኢትዮጵያን] “አስታክኮ ኤርትራን መውጋት ለሚፈልግ ኃይል አንተባበርም” January 2, 2023 07:11 pm
  • የ፰ ወር ሕጻንና ጨቅላ ወንዶች የሚደፈሩባት ትግራይ December 14, 2022 02:49 pm
  • “ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው” የደጎች አውራ የመቄዶኒያው ቢንያም በለጠ December 14, 2022 09:59 am
  • “የሀብት ምዝገባ መረጃው ለሕዝብ ክፍት ይደረግ “ December 13, 2022 10:30 am
  • የኢትዮጵያ ዓለምአቀፋዊ የሌብነት ደረጃ December 13, 2022 09:42 am
  • ለብረት አቅላጮች ለመሸጥ በኤሌክትሪክ የብረት ማማዎች ስርቆት የ100 ሚሊዮን ብር ኪሳራ December 13, 2022 09:26 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule