• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዓረና ትግራይ ፓርቲ አዲስ ፕሬዚዳንት መረጠ

September 10, 2013 04:46 am by Editor Leave a Comment

ከጳጉሜን 2 እስከ 3 ቀን 2005 ዓ.ም. ሦስተኛ ጉባዔውን በመቐለ ከተማ ያካሄደው ዓረና ትግራይ ለዲሞክራሲና ለሉዓላዊነት (ዓረና ትግራይ) ፓርቲ በቀድሞው የትግራይ ፕሬዚዳንት አቶ ገብሩ አስራት ምትክ፣ የፓርቲውን የቀድሞ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ብርሃኑ በርሄን ፕሬዚዳንት አድርጎ መረጠ፡፡

የሕወሓት መሥራች አቶ አስገደ ገብረ ሥላሴ በፈቃዳቸው ከፓርቲው አመራር መልቀቃቸው ታውቋል፡፡

በአቶ ገብሩ አስራት የቀረበው የፓርቲው የሦስት ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት የተገመገመ ሲሆን፣ በክልልም ሆነ በአገር አቀፍ ደረጃ የአገሪቱ የፖለቲካ ሁኔታ የማያሠራ ቢሆንም በዚሁ ሳይደናቀፍ ዓላማውን እያሳካ መሆኑ ተገልጿል፡፡ በክልሉ ውስጥ በበርካታ ከተሞች በሕገወጥ መንገድ ቤቶች መፍረሳቸውን የተመለከተው ፓርቲው፣ ሕዝቡ በመልካም አስተዳደርና በፖለቲካ ነፃነት ችግር ውስጥ እንደሚገኝ መገምገሙን አስታውቋል፡፡

የፓርቲውን ፕሮግራምና ሕገ ደንብ የገመገሙ ጉባዔተኞች፣ ከተወሰኑ ማሻሻያዎች በስተቀር ከፍተኛ ለውጥ ያላደረጉ መሆኑን ለሪፖርተር የገለጹት የፓርቲው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አምዶም ገብረ ሥላሴ ናቸው፡፡ ውይይት ከተደረገባቸው ጉዳዮች መካከል የአገሪቱ የፖለቲካ ምኅዳርና በተለይ በክልሉ ውስጥ በአባላቱ ላይ እየደረሰ የሚገኘው አፈና ይገኙበታል ብለዋል፡፡ አፈናው ከፍተኛ መሆኑ የተገመገመ ቢሆንም፣ በቀጣይ ፓርቲው አባል የሆነበት መድረክ ወደ ሙሉ ውህደት የሚያመራ በመሆኑ፣ አፈናውን ተቋቁሞ ለውጥ ለማምጣት መወሰኑን አክለው ገልጸዋል፡፡

በዚሁ ሦስተኛው የፓርቲው ጉባዔ የሕግ ባለሙያውና የቀድሞ የሕወሓት አባልና ታጋይ አቶ ብርሃኑ ኃይሉ ፕሬዚዳንት ሆነው ሲመረጡ፣ አቶ ጎይቶም ፀጋይ ለምክትል ፕሬዚዳንትነት ተመርጠዋል፡፡

በማኅበራዊ ድረገጾች በተለይ የሕወሓትና የትግራይ ክልላዊ መንግሥት የፍትሕና የመልካም አስተዳደር ጉድለቶች ናቸው የሚላቸውን በመተቸት የሚታወቀው ወጣት አብርሃ ደስታ፣ ጉባዔውን ከአቶ ገብሩ አስራትና ከወ/ሮ አረጋሽ አዳነ ጋር በመሆን መምራቱንና በመጨረሻም የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ ሆኖ መመረጡ ተገልጿል፡፡

በ2000 ዓ.ም. በትግራይ ክልል የመጀመሪያ ተቃዋሚ ፓርቲ ሆኖ የተመሠረተው ዓረና ትግራይ ፓርቲ ከዚህ በፊት 90 የነበረውን የጠቅላላ ጉባዔ አባላት ቁጥር ወደ 130 ከፍ እንዲል ማድረጉ ታውቋል፡፡ በተጨማሪም የሥራ አስፈጻሚ አባላትን ቁጥር ከዘጠኝ ወደ አሥራ አንድ ከፍ ያደረገ ሲሆን፣ የማዕከላዊ ኮሚቴ ቁጥር ከ21 ወደ 25 ማሳደጉም ተወስቷል፡፡ ከእነዚህ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት መካከል 15 የሚሆኑት አዳዲስ ተመራጮች መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ (ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email
facebookShare on Facebook
TwitterTweet
FollowFollow us

Filed Under: Politics

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • የእምዬ ምኒልክ አዳራሽ October 30, 2023 10:27 am
  • የኢትዮጵያ መከላከያ መሥራች አጼ ምኒልክ መሆናቸውን ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተናገሩ October 26, 2023 01:30 pm
  • ጥቅምት 15 ለምን? October 26, 2023 01:29 am
  • “በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት” October 26, 2023 12:57 am
  • “ውትድርና ሕይወቴ ነው” October 26, 2023 12:13 am
  • መከላከያ በሁሉም መስክ ኢትዮጵያን የሚመጥን ኃይል እየገነባ ነው October 20, 2023 05:07 pm
  • “ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትምህርት ቤት እኩል ነው በችሎታው ነው እንጂ የሚመዘነው” ፕ/ር ብርሃኑ October 20, 2023 04:47 pm
  • 42 የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አመራሮች እና ሠራተኞች ታሰሩ October 18, 2023 04:29 pm
  • በተማሪዎች ፈተና ውጤት ለታየው ውድቀት ትምህርት ሚ/ር ኃላፊ መሆን አለበት ተባለ October 18, 2023 04:00 pm
  • ቀይ ባሕር እና ዓባይ “የኅልውና ጉዳይ ናቸው”፤ “መተንፈሻ ወደብ ያስፈልገናል” October 13, 2023 10:04 pm
  • ከ3,106 ትምህርት ቤቶች 1,328ቱ (44%) አንድም ተማሪ አላሳለፉም October 10, 2023 01:51 pm
  • “አቋጥሬ” በአማራ ክልል እያጫረሰ ነው፤ ” ኑሮውን መቋቋም አልቻልንም ” ነዋሪዎች October 10, 2023 09:07 am
  • እሸቴ አሸባሪ፤ ቲዲኤፍ/ትሕነግ “ሰማዕት” – የዘመናችን ጉድ! October 7, 2023 06:47 am
  • በወልቃይት 1.1ሚሊዮን ኩንታል ሰሊጥ ለመሰብሰብ ከ1 ሚሊዮን በላይ ሠራተኛ ይፈለጋል September 27, 2023 10:42 am
  • በአማራ ክልል ሰላም ዕጦት ከ90.5 ቢሊዮን ብር በላይ ፕሮጀክቶች ቆመዋል September 27, 2023 08:41 am
  • ወርቁ አይተነው የሸሹት ከዝርፊያ፣ ውንብድናና ዕዳ ጋር በተያያዘ ነው September 21, 2023 02:38 pm
  • ወደ አማራ ክልል ሊተላለፍ የነበረ መሣሪያና ሰነድ ተያዘ September 19, 2023 04:35 pm
  • በትግራይ መርዶ በይፋ ሊታወጅ ነው September 19, 2023 04:22 pm
  • ጃርቶች ለምን ይጮኻሉ? September 19, 2023 04:37 am
  • “ዐቢይ ግድቡን ሸጦታል” ጌታቸው ረዳ September 11, 2023 10:18 am
  • አቶ አገኘሁ መረጃ አሳልፎ በመስጠት ዋጋ እንደሚከፍሉ ተሰማ September 10, 2023 06:52 pm
  • ለዋዜማ ሬዲዮ “ኢትዮጵያን ቋሚ የውሀ ባለ እዳ” ያደርጋል ያላችሁት ረቂቅ ሰነድ የታለ? September 10, 2023 01:58 am
  • ወደር የሌለው የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጀግና! ብርጋዴር ጄኔራል ተስፋዬ ኃብተማርያም September 8, 2023 02:31 pm
  • የትግራይ መፍረስ በርዕሰ መስተዳደሩ አንደበት September 8, 2023 02:49 am

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2023 · Goolgule