• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዓረና ትግራይ ፓርቲ አዲስ ፕሬዚዳንት መረጠ

September 10, 2013 04:46 am by Editor Leave a Comment

ከጳጉሜን 2 እስከ 3 ቀን 2005 ዓ.ም. ሦስተኛ ጉባዔውን በመቐለ ከተማ ያካሄደው ዓረና ትግራይ ለዲሞክራሲና ለሉዓላዊነት (ዓረና ትግራይ) ፓርቲ በቀድሞው የትግራይ ፕሬዚዳንት አቶ ገብሩ አስራት ምትክ፣ የፓርቲውን የቀድሞ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ብርሃኑ በርሄን ፕሬዚዳንት አድርጎ መረጠ፡፡

የሕወሓት መሥራች አቶ አስገደ ገብረ ሥላሴ በፈቃዳቸው ከፓርቲው አመራር መልቀቃቸው ታውቋል፡፡

በአቶ ገብሩ አስራት የቀረበው የፓርቲው የሦስት ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት የተገመገመ ሲሆን፣ በክልልም ሆነ በአገር አቀፍ ደረጃ የአገሪቱ የፖለቲካ ሁኔታ የማያሠራ ቢሆንም በዚሁ ሳይደናቀፍ ዓላማውን እያሳካ መሆኑ ተገልጿል፡፡ በክልሉ ውስጥ በበርካታ ከተሞች በሕገወጥ መንገድ ቤቶች መፍረሳቸውን የተመለከተው ፓርቲው፣ ሕዝቡ በመልካም አስተዳደርና በፖለቲካ ነፃነት ችግር ውስጥ እንደሚገኝ መገምገሙን አስታውቋል፡፡

የፓርቲውን ፕሮግራምና ሕገ ደንብ የገመገሙ ጉባዔተኞች፣ ከተወሰኑ ማሻሻያዎች በስተቀር ከፍተኛ ለውጥ ያላደረጉ መሆኑን ለሪፖርተር የገለጹት የፓርቲው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አምዶም ገብረ ሥላሴ ናቸው፡፡ ውይይት ከተደረገባቸው ጉዳዮች መካከል የአገሪቱ የፖለቲካ ምኅዳርና በተለይ በክልሉ ውስጥ በአባላቱ ላይ እየደረሰ የሚገኘው አፈና ይገኙበታል ብለዋል፡፡ አፈናው ከፍተኛ መሆኑ የተገመገመ ቢሆንም፣ በቀጣይ ፓርቲው አባል የሆነበት መድረክ ወደ ሙሉ ውህደት የሚያመራ በመሆኑ፣ አፈናውን ተቋቁሞ ለውጥ ለማምጣት መወሰኑን አክለው ገልጸዋል፡፡

በዚሁ ሦስተኛው የፓርቲው ጉባዔ የሕግ ባለሙያውና የቀድሞ የሕወሓት አባልና ታጋይ አቶ ብርሃኑ ኃይሉ ፕሬዚዳንት ሆነው ሲመረጡ፣ አቶ ጎይቶም ፀጋይ ለምክትል ፕሬዚዳንትነት ተመርጠዋል፡፡

በማኅበራዊ ድረገጾች በተለይ የሕወሓትና የትግራይ ክልላዊ መንግሥት የፍትሕና የመልካም አስተዳደር ጉድለቶች ናቸው የሚላቸውን በመተቸት የሚታወቀው ወጣት አብርሃ ደስታ፣ ጉባዔውን ከአቶ ገብሩ አስራትና ከወ/ሮ አረጋሽ አዳነ ጋር በመሆን መምራቱንና በመጨረሻም የፓርቲው ሥራ አስፈጻሚ ሆኖ መመረጡ ተገልጿል፡፡

በ2000 ዓ.ም. በትግራይ ክልል የመጀመሪያ ተቃዋሚ ፓርቲ ሆኖ የተመሠረተው ዓረና ትግራይ ፓርቲ ከዚህ በፊት 90 የነበረውን የጠቅላላ ጉባዔ አባላት ቁጥር ወደ 130 ከፍ እንዲል ማድረጉ ታውቋል፡፡ በተጨማሪም የሥራ አስፈጻሚ አባላትን ቁጥር ከዘጠኝ ወደ አሥራ አንድ ከፍ ያደረገ ሲሆን፣ የማዕከላዊ ኮሚቴ ቁጥር ከ21 ወደ 25 ማሳደጉም ተወስቷል፡፡ ከእነዚህ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት መካከል 15 የሚሆኑት አዳዲስ ተመራጮች መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ (ሪፖርተር)

Filed Under: Politics

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

Recent Posts

  • የመካነ ኢየሱስ ሕንጻ የጠራራ ፀሐይ ወግና “የብሌን ሠራዊት” በችሎት ደጃፍ August 5, 2026 02:35 am
  • ለሱዳንና ኤርትራ ሲከራከሩ የነበሩት አበባው ባለመመረጣቸው “በጣም ተድጃለሁ” አሉ June 26, 2026 12:29 am
  • “ትህነግ ወደ ዓለምአቀፍ ወንጀለኛነትና አሸባሪነት እየተምዘገዘገ ነው” June 25, 2026 01:00 am
  • አሜሪካ በሕገወጡ ትህነግ አመራሮች ላይ ጠንካራ የቪዛ እገዳ ጣለ June 18, 2026 10:29 am
  • እንደ ሌሊት ወፏ የሚንቀሳቀሰው ኢህአፓ/ትብብር   June 18, 2026 09:36 am
  • የታርጋ ጫጫታ June 15, 2026 05:16 pm
  • ፋንታኹን ዋቄ ከአሜሪካ የሃይማኖት እልቂት አወጁ June 15, 2026 02:12 am
  • ሕገወጡ ትህነግ ወጣቶችን ለዳግም ዕልቂት እያሰናዳ ለፈረንጆች “ኢትዮጵያን አውግዙልኝ” እያለ ነው June 11, 2026 12:57 am
  • በሐዘንና ግልፅ ደብዳቤ ስም የተሸፈነ የድህረ ምርጫ ሀገር የማተራመስ ስትራቴጂ June 10, 2026 12:19 am
  • የጽምዶ ልክፍት June 9, 2026 12:49 am
  • ገዳዩ ማነው? አስገዳዩስ ማነው? June 5, 2026 02:37 pm
  • ጽንፈኝነት ግን በኢትዮጵያ ምድር ፈጽሞ ቦታ የለውም! June 5, 2026 01:47 pm
  • የትብብሩ “ብናሸንፍም ፓርላማ አንገባም” መግለጫ “ወንበር ስታጡ ነው” የሚል ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ June 4, 2026 12:04 am
  • አዲሱ የትራምፕ የምርጫ መመሪያ፡ የአሜሪካ ዲፕሎማቶችን አፍ ያስዘጋ፤ ተቃዋሚዎች ተስፋ ያስቆረጠ June 3, 2026 08:50 pm
  • “ኢህአፓ ከምርጫው በኋላ ይሰነጠቃል” May 29, 2026 07:07 pm
  • ሪፖርተር፡ “ስውር ተልዕኮ” – በከባድ ወንጀል ሊከሰስ May 6, 2026 11:55 pm
  • የፋኖ ኃይል በደረሰበት ጉዳት ሃምሳ ሺህ የሚጠጋ ትጥቅ ጥሎ ጠፋ April 29, 2026 02:27 pm
  • አዲሱ የቴድሮስ ካሳሁን 888 ኮድ፤ እንደ 666?! April 15, 2026 05:53 am
  • ምኑ ነው ያሳቃችሁ፤ ያስደሰታችሁ? April 2, 2026 10:52 am
  • የጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ማንነት እና የባዕዳን ተልዕኮ April 2, 2026 10:16 am
  • ከግብፅ በዳያስፖራ ትርምስ ጠማቂዎች በኩል ፋኖ ወደ አዲስ አበባ የላከው “ስጦታ” March 27, 2026 09:14 am
  • “ሰላማዊ ታጋዮቹ” እነ ልደቱ ከአራጁ ሸኔ ጋር ተጣምረዋል March 25, 2026 01:04 pm
  • ጸረ-ኢትዮጵያዊ የሆነው የሪፖርተር አዘጋገብ March 19, 2026 11:54 am
  • የአውሬው ሪፖርተር ቀላቢዎች፡ የኦሮሚያ የልማት ድርጅቶች March 18, 2026 10:48 am
Copyright © 2026 · Goolgule